2022-08-28 06:40:13
#የመራም_ማስታወሻ
ክፍል ~ ➊➐
ፀሀፊ ☞አሚር ሰይድ
...ቤታችን አብሮኝ እንዲሄድ ብዙ ለመንኩት አሻፈረኝ አለ እሺ ልጆቹን ይዘህ ወዴት ነዉ የምትሄድ?? ስለዉ መሄጃዉን አያቀዉም ብቻ"እግሬ ወደመራኝ ቦታ እሄዳለሁ ቤቴን እንደሆነ ሚስቴ ሽጣ በመጠጥና በጫት ጨርሰዋለች"አለኝ
...ከልቤ አዘንኩ አባቢ ግድ የለም አብረን እንሂድ ከበላነዉ ትበላላቹህ፤ ከምንጠጣዉ ትጠጣላቹህ፤ ደስታቹህ ደስታየ ሀዘናቹህም ሀዘኔ ነዉ።
አንተ የወለድካቸዉ ልጆች ለኔ የሞተዉን ወንድሜን ማስታወሻ እና የሞተችዉ እናቴ ቅሪት ናቸዉ ..ወንድም እና እህቴችን መልሰህ አትንጠቀኝ !!!እናንተ አብራቹህን መኖር ከጀመራቹህ ቤታችን ይደምቃል የሰዉ መድሀኒቱ ሰዉ ነዉ ደሞ እነሪምን አስብ አልናፈቁህም እንዴ???.....አባቢ አብሮኝ ቤት እንዲሄድ በስንት መከራ አሳመንኩት ...ከተወሰነ ደቂቃ ቡሀላ አብደል ከሪም ከአዲስ አበባ በመኪናዉ የምሰራበት ቦታ ደረሰ ... አባቴን አገኘሁት አብደል ከሪም ብየ በደስታ አስተዋዉቄዉ አብረን ወደ ቤት ሄድን
ቤት እንደደረስን የቤቱን በር ስናኳኳ ሪም የአብዲን መምጣት በጉጉት እየጠበቀችኝ መሆኑ ያስታዉቃል ፊቷ በፈገግታ ተዉቦ በሩን ከፈተችልን።
....አባቢ ሪምን ሲያያት ደነገጠ ሪምም ያ ፈገግ ያለ ፊቷ ሆምጣጣ ሎሚ የመጠጠች ይመስል በአንዴ ኩስትርትር ብሎ ቲማቲም መሰለ ደነገጠች "አአአአ... "ምን ብላ ትጥራዉ ??አባቢ ሪምን ይዞ ልቅሶዉን ቀጠለ ጩኸቱን የሰሙ እማማየ በፍጥነት ወደኛ መጡ "ምንድን ነዉ? ምን ተፈጠረ..."አሉን አባቢን ሲያዩ እማማየም ..አልሀምዱሊላህ እንኳን ደህና መጣህ ያልሞተ ሰዉ ይገናኛል ብለዉ እቅፍ አደረጉት
..ከዘም አዩብ መጣ አባቢ በናፍቆት ሪምንና አዩብን አቅፎ የደስታ አይሉት የሀዘን ለቅሶ ያለቅሳል "እማማየ ኑ ወደዉስጥ ግቡ"ስትል ነበር ሪም" ጮክ ብላ ምን እንደተከየለባት አላዉቅም...አንተ ማን ነህ? "ብላ ከአባቢ እቅፍ ወጣች
ሪም አባቢ መሆኑን አላዉቅ ብላ ሳይሆን ይሄን ያህል ጊዜ ስለጨከነብን አባቴ ብሎ ለማለት ከብዷት ነበር ማን ነህ ያለችዉ.....
---->>>>> አባቢ ደነገጠ ምን ይበል "ሪሪሪሪሪ"ስሜን እንዳትጠራዉ ብላ ወደ ቤት እየሮጠች ገባች፡፡ እኔም ተከትያት ከገባሁ ቡላት እያለቀስኩ ሪምየ የኔ ዉድ አባታችን ነዉ አልመቸዉ ብሎ እንጂ በኛ ጨክኖብን አይደለም ያን ያህል ጊዜ ስንሰቃይ አይዟቹህ ያላለን አታይዉም ሰዉነቱን ያግርማ ሞገስ የነበረዉ አባታችን እንዴት እንደሆነ እና ተመችቶት ይመስልሻል ከኛ የራቀዉ??? ደሞ አባት ምንም ቢሆን አባት ነዉ፡፡ እዉጭ ያየሻቸዉ አንድ ወንድ እና ሴቷ ልጆች ወንድምና እህቶቻችን ናቸዉ፡፡ አባቴ ስም ያወጣላቸዉ ፈይሰል እና ለይላ ብሎ ነዉ... አየሽ እህቴ የቤተሰብ ፍቅሩ ልቡ ላይ አለ ግን አላህ ሁን ያለዉ ሁኗል ... በአላህ ሪምየ እኔ አዉፍ ብየዋለሁ አንችም አዉፍ በይዉ....... ብየ በስንት መከራ አሳምኘ ይቅር እንድትለዉ አደረኳት
ሪምና አባቢ አዉፍ ተበባሉ በጣም ደስ አለኝ አዩብም ያለ አባት ፍቅር አድጎ የአባቱን ፍቅር አሀዱ ብሎ እየጀመረ ነዉ .....አንዴ አባቢ ጋር አንዴ አብዱ ጋር
ታናሽ ወንድም እህቶቹ ጋር ሲጫወት ቤቱ የሌለ ፍቅር በፍቅር ሆነ
....በዛሬዋ ቀን አብዱንና አባቢን አገኘሁ ያ!የቀዘቀዘ ቤት በሳቅ ደመቀ ቤተሰባችን ከድሮዉ በጥፍ ጨመረ
.... ለአላህ! ክብር ምስጋና የተገባ ይሁን።
ምንም ነገር ቢሆን እንደነበረ የሚቀጥል የለም ሁሉም በጊዜ ዉስጥ ይቀየራል ያጣዉ ሲያገኝ ያገኘዉ ሲያጣ፤ ከተከፋዉ ሲደስት የተደሰተዉ ሲከፋ፤ የታመመዉ ሲድን የዳነዉ ሲታመም፤ ሂወት ስትመር አንዴ ስትጣፍጥ፤ መወለድ፤ መሞት፤ማግኘት፤ማጣት፤ማልቀስ፤መሳቅ.....በቃ ሂወት እንዲህ ናት ዝብርቅርቅ ብላ ለመግለፅ የማትመች!
አብዱም ግን መራም ልጆች እንደዚህ ሲንጫጩ ደስ አይልሽም? አለኝ
...አዎ በጣም ደስ ይለኛል
........ግን ምን እንደተመኘሁ ታቂያለሽ መራም?
.....ምንድን ነዉ??
...........የኮምቦልቻ ልጅ የነለይላ ቤተሰብ የሆነችዉን ልጅ ጋር በትዳር ተጣምሮ ደስታ የሆነ የትዳር ሂወት መስርቶ መኖር አለኝ
.....እኔም ኢንሻ አላህ ሁን ያለዉ ይሆናል አብዱ አልኩት
አሁን የምንኖርበት ቤት ጠባብ ስለሆነ አብዱ ሀሳብ አመጣ ...ኮምቦልቻ ላይ ቤት ተከራይቶ አባቴ ልጆቹን እንዲያሳድግ አዩብም አባቱ ጋር ከታናሽ ወንድም እህቶች ጋር አብሮ መኖር ጀመረ ...ሶስት ልጆች ነበርን አሁን አምስት ልጆች ሁነናል...የሞተዉ ፋይሰል እና እናቴ አሁን በተወለዱት ወንድምና እህቶች ማስታወሻ አገኘን ....
ሪም እነሱ ጋር እየሄደች መንከባከብ የሷ ስራ ሆነ
...ከተወሰነ ጊዜያት ቡሀላ እኔና አብዱ ለመጋባት ወስነን ደስ በሚል በኒካህ ፕሮግራም አድርገን አልሀምዱሊላህ አብረን የመኖር ጎጆ መሰረትን .. እንደአጋጣሚ ከአብዱ ጋር አላህ አገናኘን ለኔም ለቤተሰቦቼም ከአላህ ቀጥሎ የዱንያየ መከታ የችግሬ መፍቻ መፍትሄ ሆነን ቤታችን በድጋሚ አሸበረቀ
ግን ምን ይደረጋል የኔ ደስታ ሁሌ አትጨምር የተባለ ይመስል እኔና አብዲ ከተጋባን ከአንድ ሳምንት ቡሀላ ሁሉም ነፍስ ሞትን ቀማሽ ናትና እማማየ ሳይታመሙ ድንገት ሞቱብን አለቀስኩ ወደኩ ተነሳሁ... ነገር ግን በኛ ለቅሶ ከሞት የሚመለስ ሰዉ ቢኖሮ በተመለሰ ነበር
..እማማየን እንደናቴ ነበር የማያቸዉ ቤት ስገባ የሚቀመጡበትን ወንበር ሳይ ማልቀስ የሁል ጊዜም ስራየ ሆነ
ከአምስት ወር ቡሀላ አብዲም አዲስ አበባ ነዉ የምንኖረዉ ስላለኝ ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ እየተዘጋጀን ነዉ..የሪም አብሮ አደግ የሰፈር ልጅ የሆነዉ ሀቢብ ሀራም ከመጀመሩ በሀላል ማሸብረቁ የተሻለ ስለሆነ መጥቶ ሀቢብ እህትሽን ዳሪኝ ብሎ ጠየቀኝ...ሀቢብ ሪምን ይወዳታል የእሱ ታናሽ ነች ከልጅነት ጀምሮ አሳድጓታል ግን ለመጥፎ ነገር መቼም ተመኝቷት አያቅም ..እናም ሪምን አማከርኳት
እሷም እኔ የእህቴን አምር አልጥስም ሀቢብም አብሮ አደጌ ነዉ ጥሩ ልጅ ነዉ መርሀባ ተቀብያለሁ አለችኝ
እኔም ሀቢብ ቀጥታ እህቴን ሳያወራት እኔዉ ለእሷ ብዙ ነገር አድርጌ ማሳደጌን ስለሚያቅ እኔን መጠየቁ አስደስቶኝ ሀቢቤ እስከ ዛሬ እኔ ከእናቴ ሀላፊነት ተቀብየ እዚህ ደረጃ አድርሻለሁ መቼም ታቃለህ ..ከዛሬ ጀምሮ እኔ ደግሞ እናቴን የሰጠችኝን ሀላፊነት ለአንተ ሰጥቸሀለሁ አደራ!!!! ሪምን እንደሚስት አርገህ ሳይሆን እንደ እህትህ እንደ እናትህ አድርገህ ተንከባክብልኝ...ሰዉ ነንና ስህተት አይጠፋም..ሪም ካጠፋች አደራ ሽማግሌ አስታራቂ እንዳትጠራ ለምን እኛ ዘመድ የለንም ሪም ሊከፋት ይችላልና ...አንተዉ ወንድም አባት ሁነህ በመመካከር ሀሳባችሁን የተፈጠረዉን ችግር በወያየት ተግባባታችሁ ኑሩ፡፡
በዚህ የማይፈታ ችግር ከገጠመህ ለሌላ ሰዉ ሳታወራ ቀጥታ ደዉለህ ለኔ ንገረኝ እንደዚህ የምልህ ሪም ታጠፋለች ብየ ሳይሆን ሸይጧን በመሀከላችሁ ከገባ ምን እንደሚፈጠር እርግጠኛ መሆን ስለማልችል ነዉ እንጂ እኔ በሪም ከራሴ በላይ እመሰክርላታለሁ
ስለዉ ሀቢብም በደስታ መርሀባ ቃል እገባለሁ መራም ብሎኝ ሪምም ከሀቢብ ጋር አብሮ የመኖር ዋስትና የሆነዉን ኒካህ አሰሩ..አልሀምዱሊላህ
ለአባቴና ለታናሽ ወንድም እህቶቼ ደግሞ አብዱ አላህ ኸይር ስራዉን ይጨምርለት ኮምቦልቻ በርበሬ ወንዝ ሰፈር ቤት ገዝቶ መናሀሪያ
1.4K views03:40