Get Mystery Box with random crypto!

ወኔ እና ቅኔ -(ፈይሠል አሚን)

የቴሌግራም ቻናል አርማ huluezih — ወኔ እና ቅኔ -(ፈይሠል አሚን)
የቴሌግራም ቻናል አርማ huluezih — ወኔ እና ቅኔ -(ፈይሠል አሚን)
የሰርጥ አድራሻ: @huluezih
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 11.06K
የሰርጥ መግለጫ

ሐበሻ ቅኔን ያለ ምክንያት አልፈጠረም፤ በወኔ የማይነገሩ ሐሳቦቹን ሊገልጽበት እንጂ!
.
ዳገት አቀበቱን በወኔው አለፈ፤
ወኔውን ሲነጥቁት ቅኔ ፈለሰፈ!😉

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2022-08-14 19:51:24 ላማ ሰበቅታኒ?
.
(#ፈይሠል_አሚን)

ነፍሴ ከላይ መጣች፣
ከአምላክ የጥበብ ካዝና፤
መኖርን ተሸለምኩ፣
ሕይወትን ያኽል ዝና።
ግን መኖር...ግን መተንፈስ. . .
የተራበን መንፈስ...
ምሉዕ አያደርጉም፤
በንፋስ አንቀልባ፣ እንደታዘለ ጉም፤
ባንቺ እየተሾረ፣የመኖሬ ትርጉም!
.
ታዲያ ለምን ሔድሽ?
ትርጉም አሣጥተሽ
ሁሉን እያወቅሺው...ላማ ሰበቅታኒ?
ያላንቺ ይጠባል...
ሕይወት እንደ ወህኒ!
.
@huluezih
@huluezih
4.2K viewsFa, 16:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-11 16:34:56 #ክባዳም_ትረካዎች
.
ብሶት የወለደው ስንፍና
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
ስንፍናዬ ቅጥ የለውም። ዓለም ዐቀፍ የስንፍና ሽልማት ቢኖር የስንፍና የክብር ዶክትሬት ሽልማት አሸናፊ የምኾነው እኔ ነበርኩ። ግን እጅግ ሰነፍ ስለኾንኩ ሽልማቱን ለመቀበል አልሔድም፣ ሰው እልካለሁ እንጂ!
.
እንደምታውቁት ብቻዬን የምኖር ላጤ ነኝ። ላጤነት ደግሞ ስንፍናን የሚያበረታታ የአኗኗር ዘይቤ ነው። እንደኔ በተፈጥሮ ሰነፍ የኾነ ሰው ላጤ ሲኾን ስንፍናው ድርብ ይኾናል።
.
ምግብ ቤት ውስጥ ለማብሰል ሰንፌ ላጤ ከኾንኩ ከሁለት ዓመታት በ ኋላ "እስከመቼ ድረስ ምግብ ውጪ እበላለሁ?" በሚል ምሬት ለማብሰል የሚጠቅሙ የቤት ዕቃዎችን ለመግዛት ወሰንኩ። ይኼን ውሳኔ ለመወሰን ብዙ "I can do it!" የሚሉ የማነቃቂያ ቪድዮዎችን ዐይቻለሁ። አንድ ቀን ገበያ ወጥቼ ያስፈልጉኛል ያልኳቸውን ሁሉ ሽምቼ መጣሁ። መክተፊያዬን ዘርግቼ፣ እያነባሁ ሽንኩርት ልጬ፣ ቲማቲም ቀቅዬ ገሽልጬ፣ ማብሰያዬን ለኩሼ ሳበቃ ሽንኩርት የሚከተፍበት ቢላ እንዳልገዛሁ አስታወስኩ። ይኼ ሁላ shopping ምን ጥቅም ታዲያ? በጣም በራሴ ተበሳጨሁ። ላለመሸነፍ ምችለውን ሞክሬያለሁ። በረሮ እንደሚገድል ሰው ሽንኩርቱን በጨርቅ ጠቅልዬ በጫማ ቀጥቅጬ ልከታትፍ ሞክሬ አልተሳካም። በንዴት ሽንኩርቱን ወዲያ ጥዬ እንደለመድኩት ውጪ ልበላ ወጣሁ። የስንፍናዬ ጥግ ማሣያው ሽንኩርቱን ገዝቼ ሦስት ወር ቢያልፈውም እስካሁን አለመጣሌ ነው። ፂም እንዳበቀለ፣ ጫንቃው እንደጎበጠ ጥግ ላይ ተቀምጦ ዛሬም ይታዘበኛል።
.
ልጅ እያለሁ የስንፍናዬ መለኪያ የነበረው እንግዳ ሲመጣ እጅ ላለማስታጠብ ሽንት ቤት ገብቼ እደበቅ ነበር። ለእኔ እጅ ማ ስታጠብ ማለት ብርድ ልብስ ከማጠብ ለይቼ የማላየው ከባድ ሥራ ነው።እንግዶች ከታጠቡ በኋላ ምግብ ሲቀርብ ግን አንደኛ የምሰለፈው እኔ ነበርኩ። ችግሩ ምግቡ ከጣፈጠኝና ምግቡ እስኪያልቅ ከተቀመጥኩ "ተነሥ አስታጥብ!" መባሌ አይቀርም። ስለዚህ ምግቡ ግማሽ ላይ ሲደርስ ተነሥቼ መጥፋት ግድ ይለኛል።
.
በዚህ ባሕሪዬ የሚበሳጨው አባቴ ይኼ ስንፍናዬ በዱላ የሚጠፋ መስሎት ከክፍለ ሐገር በልዩ ትዕዛዝ እኔን የሚገርፍበት አለንጋ አስመጣ። በአለንጋ መገረፉ ሲሰለቸኝ አባቴ በሌለበት አሳቻ ሰዓት አለንጋውን ወስጄ ለመጣል ወሰንኩ። ግን ስንፍናዬ የረቀቀ ስለነበረ ሩቅ ቦታ ሔጄ መጣል አልቻልኩም ። እዚያ ከቤታችን ዐሥር እርምጃ ርቆ ካለው ሽንት ቤት ወለል ላይ ጣልኩት። መቼም አባቴም ሰው ነውና ሽንት ቤት ሲገባ ቤት ውስጥ ፈልጎ ያጣውን አለንጋ ወለሉ ላይ ተጋድሞ አገኘው ።የጣልኩትን አለንጋ በሳሙና እና በረኪና ካሳጠበኝ በኋላ እንዳይለመ ደኝ አድርጎ በአዲስ ስታይል ገረፈኝ።(አመዴ ቡን እስኪል ድረስ!)
.
ሰንብቶ አባቴ ስንፍናዬን ለማሻሻል ከቅጣት ይልቅ በሽልማት መሞከር ጀመረ። ዕቃ እንዳጥብ ያዘኝና ካጠብኩ በኋላ ሁለት ብር በሽልማት ሥም ይሠጠኛል ። ሥራውን ባልወደውም ብሩን ብዬ ዕቃ አጥባለሁ። ሁለት ብርም አገኛለሁ። በሁለት ብር የአብራክ ክፋይ የኾንኩ የቤት ሠራተኛ ኾኜ አረፍኩት።
.
ብር እያሣዩ ብዙ ሥራ ያሠሩኝ ጀመር። ችግሩ ብሩን በተቀበልኩ ቁጥር እናቴ "እኔ ላስቀምጥልህና አጠራቅመህ ሳይክል ትገዛለህ!" እያለች የላቤን ገንዘብ ሁሉ ትቀበለኝ ጀመር። ዛሬም ድረስ እናቴ ጋር ያሉኝ ብሮች ሳይክል መግዛት አልቻሉም ይኹን እንጃ ሳይክል አልተገዛልኝም።
.
እየሠሩ ብሩን አለማግኘት ስንፍናዬ ላይ ብሶት ጨመረ። ብሶት የወለደው ሌላ አዲስ ስንፍና ተፀነሰ።በዚህ ብሶት ሳቢያ እኔ ያጠብኳቸው ዕቃዎች ላይ ከሦስት ቀን በፊት ትሪ ላይ የቀሩ የእንጀራ ቁራሾች እንደ ተለጠፉ ሳይታጠቡ ይገኙ ጀመር።እናቴ ስታፌዝብኝ "እኔ ምልህ...ዕቃዎቹን የምታጥበው በእንጀራ ነው እንዴ?" ትለኛለች። ከሽልማት ቅጣት ይሻላል ብሎ አባቴም ይገርፈኝ ቀጠለ።
.
ስንፍናዬን ብሶት የወለደው ይመስለኛል። ልክ እንደ ኢትዮጵያ ሕዝብ። የምንሠራው ሥራ ቅጣትን ፍርሃት እንጂ ስለምንወደው አይደለም። ሕግ የማንጥሰው ጥሰን የሚከተለንን ቅጣት ፈርተን ነው። የምንወደው እና የምሠራው ሥራ በተፃራሪ መንገድ ተለያይተው የተራራቁ ናቸው። ዛሬም አድጌ ስንፍናዬን ይዤ የዘለቅኩት ስንፍናዬን አሽቀንጥሬ ብጥል የምደርስበት የተለየ መድረሻ ስለሌለ ነው። እና ይፈረድብኛል? እናንተስ ይፈረድባችኋል?
.
@huluezih
@huluezih
4.9K viewsFa, 13:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 14:14:37
. . .of the day!
5.0K viewsFa, 11:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 19:32:59 #ክባዳም_ትረካዎች
.
የውሾች አልባሌ እንቅስቃሴ!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
ሰሞኑን የመንደራችን ውሾች የሌላ መንደር ውሾችን እያስከተሉ ከመንደሩ ነዋሪዎች በቁጥር በልጠዋል። በሰፈራችን ውሾች ላይ አንዳንድ አልባሌ እንቅስቃሴዎችን እያስተዋልኩ ነው። ነገሩ የገባኝ የ ዕድራችን ሊቀ-መንበር ጋሽ ጋንዲ "የመራቢያ ጊዜያቸው ነው!" ብለው ካስረዱኝ በኋላ ነው። ይኼን እያወቁ የራሳቸውን ውሻ ግን ግቢ ውስጥ አስረዋት ዘሯን እንዳትተካ ከልክለዋታል።(ሜሪ-ጆይ ኾነውባታል)

"እና ከማንም ጎረምሳ ዘሯን እንድትተካ ላድርግ?!" ብለው ይሞግታሉ። "እኔ በጥንቃቄ ያሳድግኳትን ውሻ ለማንም ጋጠ-ወጥ፣ በየሥጋ ቤቱ ቅንጥብጣቢ ለሚበላ ተራ ውሻ አሳልፌ የምሠጥ ይመስልሃል?!" ሲሉኝ ደንግጬ "ኧረ ይደርሳል! ማንም አባት የአብራኩን ክፋይ መጥፎ ቦታ ላይ አይጥልም!" ብያቸው ስድስት በጎ ፍቃደኛ ገላጋዮች ናቸው ከጋሽ ጋንዲ ዱላ ያስጣሉኝ። የአነጋገራቸው ለዛ ስለ ውሻ ሳይኾን ስለ ወለዱት ልጅ የሚሞግቱ ስለሚመስል ነው "የአብራክ ክፋይ" የሚለውን ቃል የተጠቀምኩት። "አልተግባባቶም" ብለው እንኳ በቀናነት አላለፉኝም።
.
የተፈጥሮ ነገር ግን ይገርማል። ውሾች በፕሮግራም የመራቢያ ጊዜያቸውን ጠብቀው እንደሚራቡ አላውቅም ነበር። ልክ መራቢያ ወቅታቸው ሲደርስ በየሰፈራችን ዐይተናቸው የማናውቃቸው ውሾች እንደ አሸን መፍላት ይጀምራሉ።የፈረንጅ ውሻ፣ የፖሊስ ውሻ፣ የቤት ውሻ፣ የወፍጮ ቤት ውሻ፣ ሥም ያለው ውሻ፣ ሥም የሌለው ውሻ ...ሌላም ሌላም ዓይነት ውሻ ለዓይን እንግዳ መኾናቸው ይቀራል።
.
አንደኛው ከቦሌ፣ አንዱ ከጉለሌ ሌላኛው ከሸጎሌ ድረስ ግንፍሌ ያለችውን ቆንጆ እንስት ውሻ ፍለጋ ይመጣሉ። በሁሉም ፍጡር የወንዶች ባሕሪ መመሳሰሉ አይገርምም? ለማስወለድ እንጂ ለማሳደግ ይኼን ያኽል ተጉዘው አይመጡም!
.
የውሾች መራቢያ ጊዜ ሲደርስ ለምን የወንዶች ቁጥር ብዙ ኾኖ ሴቷ አንድ እንደምትኾን አይገባኝም። ሁሌም አንዲት ቀጠን ያለች ሸንቃጣ ውሻ በሃያ ምናምን ውሾች ትታጀባለች። እሷ ከፊት ከፊት ዘና ብላ ስትሮጥ ያ ሁሉ ጎረምሳ ውሻ ለሀጩን እያዝረከረከ ከኋላ ይከተላል። ከጠዋት ጀምራ ሰፈሩን ስድሳ ጊዜ ስታዞራቸው ትውላለች።
.
ባለፈው ሳምንት ይኼን ክስተት ለመጀመሪያ ጊዜ ስመለከት ውሾች በአትሌቶቻችን ውጤት ተነሳስተው የአትሌቲክስ ልምምድ የጀመሩ መስሎኝ ነበር። "ለመራባት ነው እንዲህ ሰፈሩን የሚዞሩት" ብዬ ለማሰብ ከብዶኝ ነበር።ዙረቱ ግን ምክንያታዊ ነው ማለት ይቻላል። ይኼ ሁሉ ዙረት እንደ ኢንተርቪው ይቆጠራል። ሴቷ የሁሉንም ወንዶች ባሕሪ እያጠናች ይመስለኛል። "ምን አለው? ባሕሪው እንዴት ነው? ጥሩ አባት መኾን ይችላል ወይ?" የሚለውን ነው ምታጠናው።
.
የሚገርመው ወንድ ውሾች ራሳቸውን አሳንሰው አያዩም። የኾነ ጥቁር ድንክ እና ሽማግሌ ውሻ ከዚያ ሁሉ ውሻ ጋር በአቅሙ እየተከተለ አቅሙን ለማሣየት ሲጥር ነበር። የዛሬ ሳምንት በመኪና ተገጭቶ ሁለት የኋላ እግሩ የተሰበረበት ውሻ ራሱ እየተንፏቀቀ ዕድሉን ሞክሯል። አሁን ዕድሉ ቢሠጠው ምን ሊያደርግ ነው? ወደ ሌሎች ውሾች ዞሮ...
"ጓዶች! አንዴ ከፍ ታደርጉኝ?" ሊል ነው?
የጋሽ ጋንዲ ዕድር እንዲህ ላሉ ውሾች ለምን ዊልቸር እንደማያዘጋጅ አይገባኝም።
.
ተፈጥሮ ሚዛናዊ መኾኑን በውሾች ውስጥ ነው የማየው። ውሾች ለዘጠኝ ሳምንታት ብቻ ነው የሚያረግዙት። ቢበዛ እስከ ሦስት ወር ቢደርስ ነው። በፈለጉት ጊዜ ማርገዝ ቢችሉ ምን ሊፈጠር እንደሚችል አስቡት። አንድ ውሻ በዓመት 3 ጊዜ ብታረግዝ በዘጠኝ ወር ውስጥ 3 ጊዜ ትወልዳለች ማለት ነው። ውሾች ደሞ እንደምታውቁት አንድ ልጅ አይደለም የሚወልዱት። በዓመት ቢያንስ በአማካይ 12 ልጅ ቢኖራት...በአራት ዓመት ውስጥ የ48 ልጆች እናት ትኾናለች ማለት ነው። ፈጣሪ ግን ጥበበኛ ስለኾነ የመራቢያ ጊዜ አስቀምጦላቸው ቁጥራቸውን ይመጥነዋል።
.
የሰው ልጅ እንደ ውሻ ቢሆንስ? በአመት አስራ ሁለት ልጅ መውለድ ቢችል? መንግሥት ዐዋጅ አውጥቶ ወንዶችን የማኮላሸት ዘመቻ ሚጀምር አይመስላችሁም?
.
@huluezih
@huluezih
5.1K viewsFa, 16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 06:38:13 የማለዳ ማስታወሻ #139
.
ይቅርታ. . .
ስለ ጥንካሬዬ ደክመሽ፣ ተ ስፋ ልትሠጪኝ ብዙ ከፍለሽ፣ ችዬ በማልገልጸው ሥብራት ደካማ ስለኾንኩ። ራሴን መጠገን፣ ወደፊት ለመሔድ መንገድ ሳይኾን ምክንያት ስላጣሁ።ይቅርታ!
.
ይቅርታ. . .
ከጭላንጭሏ የብርሃን ጨረር የዋጠኝ ጽልመት ስላሸነፈኝ፣ ከነገዬ ይልቅ ትናንቴ ስላማረኝ፣ ዋጋ ከፍዬ የቆምኩበት ከፍታ ምኔም ስለኾነ። ይቅርታ!
.
ይቅርታ. . .
ሙሉ ገጼን ከፍቼ ስላላሣየሁ፣ መድኃኒት ስፈልግ በሽታዬን ስላገኘሁ። ምክንያቴን ማንም እንዲመዝነው ስላልፈቀድኩ፣ ሸንጎ የማያቆም በደል ነፍሴ ላይ ስለጫንኩ። ድካሜ እና ውጤቴ ስለተራራቁ...ይቅርታ!
.
ይቅርታ. . .
"ብዙ እንሔዳለን!" ብዬ የገባሁትን ቃል ስላፈረስኩ፣ በገዛ ጥፋቴ ጥፋተ ኝነት እንዲሰማሽ ስላደረግኩ። አለመቻሌን የማሳብብበት ሰበብ ስላጣሁ።ኢ-ፍትሐዊ በኾነች ዓለም ውስጥ ሚዛኔን ስለሳትኩ። ይቅርታ!
.
ይቅርታ!
ካንተ ውጪ የምጸልይበት፣ ከእጅህ ሌላ እጄን የምዘረጋበት ጽንፍ ስለተነፈግኩ፣ መርጠህ የባረክከውን መንፈስ በዳተኝነት ስላረከስኩ፣ ሥጦታህን ስላቃለልኩ፣ አምላክነትህን ሳልሽር ራሴን ፈላጭ ቆራጭ አድርጌ ስለሾምኩ! ይቅርታ!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
@huluezih
@huluezih
4.8K viewsFa, 03:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 16:00:00
. . .of the day!
4.5K viewsFa, 13:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 21:45:30 .
እንግዲህ አብዛኛውን ጥያቄ መልሻለሁ... በድጋሚ አመሠግናለሁ። በቅርቡ በዩቲዩብ ቻናል ላይ ወጎችን ማንበብ እጀምራለሁ። እስካሁን ወጎችን ስቆጥብ የነበረው በቪድዮ ለመምጣት ነው። ገና አልተነካም።
.
Love you all.
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
@huluezih
@huluezih
4.5K viewsFa, 18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 21:45:30 ለጥያቄዎች መልስ ምንሠጥበት ሰዓት ላይ ነን። በቅድሚያ ለአስተያየቶቻችሁ አመሠግናለሁ ። ጽሑፎቼን ምትከታተሉ፣ምትወዱ እና አስተያየት ሳትሠስቱ በመሥጠት ብርታት የምትኾኑልኝን ሁሉ አከብራችኋለሁ፣እወዳችኋለሁ ። ከምሥጋና ጋር።
.
ተመሳሳይ ዐውድ ያላቸውን ጥያቄዎች አንድ ላይ በማድረግ ልመልስ።
.
1. ለምንድነው እንደበፊቱ ቶሎ ቶሎ የማትለቀው?
.
የመጀመሪያው ምክንያት የበፊት ሁኔታ ላይ አይደለሁም ።በጣም የተጣበበ ጊዜ እና ተደራራቢ ሥራ ስለምወጠር እንደበፊቱ ቶሎ መጻፍ አዳጋች ኾኖብኛል ። ይኼ ቻናል ከተከፈተ ወደ አምስት ዓመታት ገደማ ተጠግቷል። ለነፍስ ሀሴት ግጥሞችን ወጎችን በመጻፍ በተወሰኑ ሰዎች ከመመሥገን ያለፈ ኑሮን የሚያቀና ነገር አይገኝም። ለእንጀራ ሌላ ሥራ ሲኖር የሥነ-ጽሑፍን ሥራ በመቀነስ ወደ ኑሮ ትግል ማምራት ግድ ነው።
.
ሁለተኛው ምክንያት ሥነ-ጽሑፍ የተለየ ባሕሪ ስላለው ነው። እስቲ ልጻፍ ተብሎ አይጻፍም። ነገሮችን በማስተዋል፣ስሜቶችን በመተርጎም ቃላትን ፈልፍሎ አውጥቶ የሚሠራ ነው። እንዲህ ያለው ሥራ አብዛኛው የአዕምሮ መረጋጋትን፣ ልብን የማድመጥ ፋታን ይጠይቃል። ለምሳሌ የማለዳ ማስታወሻ የሚለውን አምድ ከወሰዳችሁ ጠዋት ከእንቅልፌ እንደተነሣሁ ውስጤ የሚመላለስን የመጀመሪያ ሐሳብ የምጽፍበት ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከእንቅልፌ የምነሣው የ ሥራ ሰዓት ላለማርፈድ በሚፈጠር ድንጋጤ ነው። የሚጻፉና ኑሮን የሚደጉሙ ተጨማሪ ሥራዎችን ማታ እየጻፍኩ አምሽቼ ስለምተኛ ጠዋት ለማሰብ ሳይኾን ለመሮጥ ነው ጊዜ ሚኖረኝ።ኾኖም የማለዳ ማ ስታወሻ ይቀጥላል።
.
2. ግጥም እና እኔ...?
.
"መቼ ጀመርክ?" "እንዴት አዳበርክ?" የሚሉ ተመሣሣይ ምላሽ ያላቸውን ጥያቄዎች ልመልስ።
ግጥም መቼ መጻፍ እንደጀመርኩ አላስታውስም። ሦስተኛ ክፍል እያለሁ እንደ ሰውነቴ ደካማ የኾኑ ግጥሞችን መድረክ ላይ ወጥቼ አነብ እንደነበር አስታውሳለሁ። ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ እስከ ሰባተኛ ክፍል ድረስ አንድ ትምህርት ቤት ውስጥ መማሬ የጠቀመኝ ይመስለኛል። ደጃዝማች በቀለ ወያ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ይባላል። ልደታ ለልማት ተብሎ ሳይፈርስ(ሳይሰዋ) በፊት በዚህ ትምህርት ቤት የሚያበረቱኝ መምህራን፣ የሚያደምጡ ኝ ተማሪዎች ግጥምን እንድከተል ያደረጉኝ ይመስለኛል።
.
እኔ ሁለት ዓይነት ገጣሚዎች እንዳሉ አምናለሁ። ተፈጥሯዊ እና ኢ-ተፈጥሯዊ። ተፈጥሯዊ ገጣሚዎች ችሎታቸውን ለማዳበር ብዙ አይለፉም። ትንሽ ንባብ፣ ትንሽ አፈንጋጭነትና ትንሽ ኑሮ በቂያቸው ነው። የነዚህ ገጣሚዎች ስንኞች ቀጥታ ከአንባቢዎች ልብ ጋር ይጣበቃል ። የኛን ሕይወት የሚያወሩ እስኪመስለን። ኢ-ተፈጥሯዊ ገጣሚዎች ከብዕር ጋር ሲገናኙ ብዙ ያምጣሉ። ከሐሳባቸው ይልቅ ቃላቸው ጠጣር ነው ። መልዕክታቸው እንደ ቄጠማ ሁለት ቀን አይሻገርም። ይኼ ጊዜ ይወስዳል እንጂ ምናልባት ይስተካከላል። ግጥም ወዳጅ መኾን በራሱ ጊዜ የሚስተካከል መንገድ ያበጃል። ማዳበር፣ ማሻሻል፣መልመድ ለምትፈልጉ የምመክረው አንብቡ...ኑሩ... መሠረታዊ ዕውቀቱን ያዙ።
.
3. የምትጽፋቸው ነገሮች ከሕይወትህ ጋር ይገናኛሉ?
.
ሁሉም አይገናኝም። ሁሉም አይራራቅም። ግጥም እንደ ሥዕል ነው ይባላል። ለመሳል ማየት ግድ ነው። ግጥምም ላይ ለመግጠም ስሜቱን መጋራት ያስፈልጋል ። በእርጅና ምክንያት መንገድ ላይ የተጣለ፣የተረሳ የተገፋ ፈረስ ዐይቼ ግጥም ጽ ፌያለሁ። የፈረሱ ሕይወት የእኔ ሕይወት ኾኖ አይደለም። ገጣሚ ስለኾንኩ እና ስስ ነፍስ ስላለኝ ነው።(መልሼያለሁ ብዬ አስባለሁ)
.
4. ኢስላማዊ ግጥም. . .
.
እኔ ጥበብ ሐይማኖት የለውም ብዬ አምናለሁ። ሐይማኖት ግን ጥበብን ይጠቀማል። ለሰው ልጅ ነው ምጽፈው። ማንኛውም እምነት ይከተል ከየትም ይምጣ...ስሜት ያለው ሰው ሁሉ ግጥም ልቡን ቢያናግርለት ብዬ እመኛለሁ። "ከኢስላማዊ ወጣ ያለ ነው" ለምትሉ "መቼ ገባ አለ?" የሚል ጥያቄያዊ መልስ አለኝ። የጥበብ ቻናል እንጂ የሐይማኖት ቻናል አልከፈትኩም። አንዳንዴ እምነቴ ግጥሞቼ ላይ ሊታዩ ይችላሉ....መቼም ሰው አይደለሁ...
.
5. መድረክ ላይ ወግ እያቀረብክ ሰዎች ባይሥቁ፣ባይሰሙህ ምን ይሰማሃል..
.
ያለ ቦታዬ እንደተገኘሁ ይሰማኛል። አሁን ላይ መድረክ እየመረጥኩ መሔድ የጀመርኩት እንዲህ ያለ ሁኔታ ገጥሞኝ ነው። እንደ ስሕተት ወስጄ ተምሬበት አልፋለሁ እንጂ የተለየ የማደርገው ነገር የለም።
.
6. Bot ብትከፍትልን...
.
ከዚህ ቀደም Bot ከፍቼ አስተያየቶች እቀበል ነበር። ነገር ግን አንዳንዶች የሚሰነዝሩት አስተያየት መርዛማነት፣ እንደ ሐይማኖት አባት ተመልክተውኝ ከመንፈሳዊ ዓለም የራቀ ሥራ ነው በሚል አሰልቺ ስድብ፣ "ግጥም አስለምደኝ" እና "ገምግምልኝ" የሚል የማልወደው ጥያቄ፣ አዳዲስ ሰዎችን ማወቅ አለመውደዴን እና ሌሎችንም ብዙ ምክንያቶች ጨምሮ Botን ለማጥፋትና ሁሉ እንዲያይ የሚያስችል ግሩፕ ለመክፈት ተገድጄያለሁ። So...No more Bot! ግን አንደንዴ ከአስተያየታቸው አንገብጋቢነት በመነሣት ራሴ የማናግራቸው ሰዎች አሉ..ኩራት እንዳልኾነ ይሰመርልኝ!
.
7.ግጥሞችህ ላይ ሐዘን ይበዛሉ...
.
አዎ...ሐዘን ለግጥም ትልቁ ምንጭ ነው። ሐዘን በቀላሉ ወደ ግጥም የመቀየር ባሕሪ አለው። ገጣሚ በልቡ ያየውን ይጽፋል...ሕይወት ደሞ አሳዛኝ ገጿ ይበዛል። ሰውን ለማነሣሣት የማለዳ ማስታወሻን እመርጣለሁ። ሐዘን ብቻ አልጽፍም። ግን ሐዘንም፣ ዙሪያችን ያንዣበበው ጽልመት በጥበባዊ መንገድ መገለጽ አለባቸው ። ሁላችንም ጋር ህመም እንዳለ ሁላችንም ማወቅ አለብን።
.
8. ከግጥም እና ከወግ?
.
ያለ ማንገራገር ግጥም!!
.
9. አርዓያ..ማበርከት ምትፈልገው፣ አምላክህ ፊት አንድ ግጥም አቅርብ ብትባል...?
.
ማንም አርዓያ አድርጌ አላውቅም። የማደንቃቸው ገጣሚዎች አሉ... አርዓያዎቼ ግን አይደሉም። ገጣሚ አርዓያ ይፈልጋል እንዴ? እናንተ እዚህ ምድር ላይ ለመኖር ማነው አርዓያችሁ? ማንን ዐይታችሁ ትኖራላችሁ? ልክ እንደዚህ ጥያቄ ነው ግራ ሚገባኝ "አርዓያህ ማነው?" ስባል..ግጥም መንገድ ነው..ኑሮ ነው። በመንገድ ለመሔድ የማንንም አረማመድ ማየት አይጠበቅብኝም። እንደ እግሬ ብርታት፣ እንደ ጫማዬ ስፋት እራመድበታለሁ። ለመኖር መተንፈስ መቻል እንጂ የሰው ኑሮና አኗኗርን አላይም።ግጥምም እንደ መንገድና ኑሮ ነው።
.
በሥነ-ጽሑፍ ማበርከት ምፈልገው...የሰዎችን ህመም እንደተካፈልኩ ቢያውቁ፣ አንድ ቀሽም ቀናቸው ላይ አንዲት ቃል ጽፌ ፊታቸው ላይ ፈገግታ መጫር ከቻልኩ፣ ክፋትን ተቃውሜ ክፉን ካሸማቀቅኩ፣ ደጎችን አድንቄ ደግነታቸው እንዳይከስም ከሞከርኩ...ብዙ አበርክቻለሁ ብዬ ማሰብ እጀምራለሁ። ጥበብ ጥቃቅን ነገሮችን መግራት ላይ ነውና ኃይሏ!
.
አምላክ ፊት አልቆምም። መቆም እንደምችል ሳምን ፊቱ ቆሜ የቱን ግጥም እንደማነብ አስብበታለሁ።
.
10. ስለ ሐገር...
.
አስተውላችሁ ከኾነ ብዙ ጊዜ በሴት ውስጥ ሐገርን እና እናትን እስላለሁ። እናት ያለችበት ሁሉ ሐገር ነው። ሐገርህ ላይ ካለህ እናት ባይኖርህም ለነፍሷ ቅርብ ነህ ብዬ አምናለሁ። ለዚያም ነው ራሴን ከሐገሬ አርቄ ማሰብ የሚያዳግተኝ። ግጥሞቼ መሐል ስለ ሴት ፍቅር የሚመስሉ ግን ስለ ሐገር እና እናት የሚያወሩ ግጥሞች አሉ።
4.4K viewsFa, edited  18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 19:24:16 ጥያቄ ያላችሁ መጠየቅ ትችላላችሁ (አስተያየትም ይቻላል)። ጥያቄዎቹን ሰብሰብ አድርጌ አንድ ላይ ለመመለስ ዝግጁ ነኝ። (በናንተ ኢንተርቪው ልደረግ እስቲ!)
4.6K viewsFa, 16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 10:23:50
. . .of the day!
4.9K viewsFa, 07:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ