Get Mystery Box with random crypto!

Freshman and Preparatory Students Channel

የቴሌግራም ቻናል አርማ g12_freshman — Freshman and Preparatory Students Channel F
የቴሌግራም ቻናል አርማ g12_freshman — Freshman and Preparatory Students Channel
የሰርጥ አድራሻ: @g12_freshman
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.97K
የሰርጥ መግለጫ

👇👇👇
https://www.youtube.com/c/atcnews1
Contact us 🔽
@atcads

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-05-12 10:51:46
ከዚህ ዓለም ድካም አረፈች

* ሂሩት በቀለ የ7 ልጆች እናት፣ የ10 ልጆች አያት እና የ7 ልጆች ቅድመ አያት ነበረች። በዘመን ተሻጋሪ ሙዚቃዎቿ የምትታወቀው በብዙ ኢትዮጵያዊያን በዘፈኖቿ የምትወደደው ~ የድሮዋ ዘፋኝ፤ የአሁኗ ዘማሪት ሂሩት በቀለ በ80 አመቷ ከዚህ አለም በሞት ተለየች

ሕይወት እንደሸክላን ጨምሮ በርካታ ድንቅ የሙዚቃ ስራዎችን እንካችሁ ያለችው ድምጻዊት ሂሩት በቀለ፣ በአደረባት ህመም በሃገር ውስጥና በውጭ በህክምና ስትረዳ ቆይታ በዛሬው እለት ግንቦት 04 ቀን 2015 ዓ.ም ህልፈተ-ሕይወቷ ተሰምቷል፡፡

ከ1950 መጀመሪያ እስከ 1980ዎቹ መጨረሻ ድንቅ የሙዚቃ ስራዎችን ያስደመጠችን ሂሩት በቀለ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዘማሪነት/አገልጋይነት ስራዎችን ስትስራ እንደነበር ይታወቃል።

በሰላም እረፊ
1.1K views𝐁ěŕ𝐮ĥ, 07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 22:49:09
#አዲግራት_ዩንቨርስቲ

1. የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች ሆናችሁ ላላፉት ሁለት ዓመታት በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች  ተመድባችሁ የመማር እድል ያላጋጠማችሁ፤

2. በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተከታታይ መርሃ ግብር ተማሪዎች፤

3. በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች በመደበኛነት ስትማሩ ቆይታችሁ፣ ላለፉት ሁለት አመታት አቛርጣችሁ አሁን ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለመመዝገብ የምትፈልጉ ተማሪዎች፤

በዚህ ማስፈንጠሪያ http://197.156.104.178/ በኦንላይን የቅድመ ምዝገባ ቅፅ ከግንቦት 03 አስከ 15/2015 እንድትሞሉ ጥሪ አቅርቦላችኃል።

ዩኒቨርሲቲው ትምህርት የሚጀመርበት ቀን በቅርቡ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።


፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
1.2K viewsMuJa. M, 19:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 19:36:52
ማስታወቂያ
**
ውድ የዲላ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች በሙሉ ።
ዛሬ በጣለው ንፋስ የቀላቀለ ከባድ ዝናብ ምክንያት አብዛኛው የመብራት ፖሎች ስለወደቁ እና አጠቃላይ የመብራት አገልግሎት ስለተቋረጠ ላይበራሪም ሰለማይከፈት ስፔስ ለማንበብ ሳትወጡ ሁሉም ተማሪ በግዜ በየዶርማችሁ በመግባት እንዲሁም እንቅስቃሴያችሁን በመገደብ ራሳችሁን ይሄን አጋጣሚ ተጠቅመው ለመዝረፍና ጥቃት ማድረስ ከሚፈልጉ አካላት እንድትጠብቁ እናሳስባለን።

የዲ/ዩ/ተማ/ህ/ጽ/ቤት

፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
1.2K viewsMuJa. M, 16:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 19:23:23
የ2016 የትምህርት ቤት የክፍያ ጭማሪ ከወላጆች ጋር በቂ መግባባት ላይ ሳይደርስ ወደ ተግባር መግባት እንደማይቻል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታወቀ።

ባለስልጣኑ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር ለሚገኙ የግል እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ትምህርት ቤቶች በጻፈው ደብዳቤ፤ የ2016 የክፍያ ጭማሪ በተመለከተ በቀን 12/08/2015 ከኹሉም ት/ቤት ባለቤቶች ጋር ባደረግነው ውይይት መሠረት፤ የክፍያ ጭማሪው በት/ቤቱ እና በወላጆች ውይይት እና መግባባት መሠረት ያደረገ እንዲሆን በጋራ መሥማማት ላይ መደረሱን አስታውሷል፡፡

ቢሆንም ግን፤ በከተማዋ አንዳንድ ተቋማት የክፍያ ጭማሪውን በተመለከተ ከወላጆች ጋር በቂ ስምምነት ላይ ያልተደረሰ መሆኑን ባለስልጣኑ በውይይቱ ወቅት በአካል ተገኝቶ ባደረገው ምልከታ ማረጋገጡን ገልጿል፡፡

ስለሆነም በ2016 የትምህር ዘመን የክፍያ ጭማሪ ከወላጆች ጋር በቂ መግባባት ላይ ሳይደርስ ወደ ተግባር መግባት እንደማይቻል ያሳሰበው ባለስልጣኑ፤ ባለው አሰራር መሰረት ከተማሪ ወላጅ ተወካዮች እና ከባለስልጣን መ/ቤቱ ጋር ውይይት በማድረግ በሚቀመጠው የጋራ አቅጣጫ መሰረት ብቻ ወደ ተግባር የሚገባ መሆኑን አሳስቧል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አክሎም፤ የ2016 የተማሪዎች ምዝገባ በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የትምህርት ቢሮ በሚያወጣው የትምህርት ካላንደር መሠረት ከሀምሌ 2015 በኋላ ብቻ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፤ ይህንን ውሳኔ ተግባራዊ በማያደርጉ ተቋማት ላይ አስፈላጊውን የእርምት እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል።


፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
976 viewsMuJa. M, 16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 17:09:28
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ 6ኛ እና 8 ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ቀናት ይፋ አደረገ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ የ 8ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 19 እና 20 እንዲሁም የ 6ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 26 እና 27 እንደሚሰጥ ተናግረዋል::


አያይዘውም ቢሮው ከተማ አቀፍ ፈተናዎቹን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመስጠት ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን የተናገሩ ሲሆን ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቹን የበለጠ ማዘጋጀት እንዲችሉ ከከተማና ክፍለ ከተሞች ጋር በጋራ በመሆን የሞዴል ፈተናዎችን እንዲሰጡ አሳስበዋል ::


በ 2015 ዓ. ም 75,100 የ8ኛ እንዲሁም 75,078 የ 6ኛ ክፍል ተማሪዎች ከተማ አቀፍ ፈተናውን እንደሚወስዱ ከስራ ክፍሉ ያገኘነው መረጃ ያሳያል ::


፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
1.0K viewsMuJa. M, 14:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 14:18:28
በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አንድ ተማራ ተገድሎ ተገኘ


ዛሬ ግንቦት 01/2015 በደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ አንድ ተማሪ ተገድሎ መገኘቱን እና በዚህም ምክንያት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ስጋት መፈጠሩን የተቋሙ ተማሪዎች ነግረውናል።

በጉዳዩ ዙሪያ ለቲክቫህ መረጃ የሰጡት የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ድርቧ ደበበ (ዶ/ር)፤ "ፖሊስ ጉዳዩን የያዘው መሆኑንና ምርመራ እያደረገ እንደሚገኝ" ገልጸዋል።

ሟቹ ተማሪ "ቅዳሜ ዕለት የታየ መሆኑን ለሦስት ቀናት ጠፍቶ መቆየቱን" ኃላፊዋ አመልክተዋል።

የተማሪውን ተገድሎ መገኘት ተከትሎ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ አለመረጋጋት መፈጠሩንና የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችም ከፀጥታ አካላት ጋር መጠነኛ ግጭት ውስጥ ገብተው እንደነበር ከተማሪዎቹ ሰምተናል።አሁን ላይ አለመረጋጋቱ በፀጥታ አስከባሪዎች ቁጥጥር ስር እንደሚገኝም ለማወቅ ተችሏል።

ዩኒቨርሲቲው በበኩሉ የተማሪው ማንነትና የግል ማህደር በማጣራት ላይ መሆኑንና በቀጣይ መረጃ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

በዚህ ዓመት ብቻ የተቋሙ ተማሪ ተገድሎ ሲገኝ ይህ የመጀመሪያ አለመሆኑንም ተማሪዎቹ ጨምረው ጠቁመዋል።


፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
1.1K viewsMuJa. M, 11:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 16:22:32
ከ215 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና መመዝገባቸውን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡
ካለፈው ዓመት ጀምሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ከወትሮው በተለየ መልኩ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መሰጠት ተጀምሯል፡፡ በአማራ ክልል የ2015 ዓ.ም ብሔራዊ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ለመውሰድ ከ215 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ አድርገዋል ነው የተባለው፡፡
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ምዝገባ ከመጋቢት 20/2015 ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 15/2015 ዓ.ም ድረስ ተካሂዷል፡፡ የተፈታኞች ምዝገባ በትምሕርት ቤቶች በበይነ መረብ ብቻ እንደተካሄደ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የፈተናና ምዘና ቡድን መሪ አቶ ዝጋለ ማሩ በተለይም ለአሚኮ ገልጸዋል፡፡
በክልሉ ውስጥ 579 2ኛ ደረጃ ትምሕርት ቤቶች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን የተማሪዎች ምዝገባ ያካሄዳሉ ተብሎ ታቅዶ ነበር ያሉት አቶ ዝጋለ 575 ትምህርት ቤቶች ምዝገባውን ማድረግ ችለዋል ነው ያሉት፡፡ ሰሜን ጎንደር እና ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር የሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች በአካባቢው ከተፈጠረው ጦርነት ጋር በተያያዘ የተማሪዎች ምዝገባ ማድረግ አልቻሉም ብለዋል፡፡


መረጃው የአሚኮ ነው።

፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
1.3K viewsMuJa. M, 13:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 20:17:36
#Update

የዲቪ (DV) 2024 አሸናፊዎች ይፋ ተደረጉ።

ባሳለፍነው ጥቅምት እና ህዳር ወራት ላይ በበይነ መረብ አማካኝነት የተሞላው የ2024 ዲቪ (DV) ሎተሪ ይፋ ተደርጓል።

ለዲቪ /DV/ 2024 ማመልከቻ የሞሉ በ https://dvprogram.state.gov/ESC/Default.aspx ብቻ ውጤቱን / ማሸነፍ አለማሸነፋቸውን መመልከት ይችላሉ።

በአ/አ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ "የዲቪ (DV) ሎተሪ አሸንፋችኋል፣ ከአሜሪካ ኢምባሲ ነው እምንደውለው / ኢሜይል / ቴክስት የምንልከው"  በሚል #የሚያጭበረብሩ አካላት ስለሚኖሩ አመልካቾች እንዲጠነቀቁ አደራ ብሏል።

አሜሪካ በየዓመቱ ከአፍሪካ ፣ እስያ ፣ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ፣ ደቡብ አሜሪካ እና አውስትራሊያ 50 ሺህ ሰዎችን በዲቪ (DV) ሎተሪ ወደ ሀገሯ ታስገባለች።


@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
1.6K viewsMuJa. M, 17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 19:18:05
ስለ ውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ከሰሞኑ የወጡ መረጃዎች፦


° ከእስያና ከአውሮፓ ሀገራት ጋር የስምምነት ሥራዎችን ተጀምረዋል።

° የዩኒቨርሲቲ ምሩቃንን ጭምር በማሰልጠን ወደ ውጭ ሀገር ለመላክ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነወ።

° ዜጎች ስራው ካልተመቻቸው መጥፋት ሳያስፈልጋቸው ይቀየርልን የሚሉበትን አሰራር ተዘርግቷል።

° ዜጎች ለፓስፖርት፣ ለጤና ምርመራ ለአሻራ ከሚከፍሉት ውጪ የሚያወጡት ወጪ የለም።

° ባለፉው ዘጠኝ ወራት ስድስት ሚሊዮን ዜጎች በሥራ ፈላጊነት ተመዝግበዋል።

° ህጋዊ ፍቃድ ያላቸውን የውጭ ሃገር የሥራ ስምሪት ኤጀንሲዎች ከሚኒስቴሩ ድረ-ገጽ መመልከት ይቻላል።

° በውጪ ሃገር የሥራ እድል ላይ መመዝገብ የሚቻለው በዲጂታል አማራጭ ብቻ ነው።


፨ክፍያውን ማን ይሸፍናል?

"የትኬት እና የኢንሹራነስ ወጪን የሚከፍሉት የመዳረሻ ሀገር ላይ ያሉ አሰሪዎች ናቸው ከዜጎች የሚጠበቀው የፓስፖርት እና የጤና ምርመራ በተወሰነ ደረጃ የአሻራ ከዛ ውጪ ዜጎች የሚያወጡት ወጪ የለም አንዳንድ ህገወጦች ግን ከ60-80 ሺህ ይቀበላሉ ዜጎች መብታቸውን አውቀው አውቀው ሊጠነቀቁ ይገባል" ሲሉም ገልጸዋል።

ለመመዝገብ ይህን ፎርም ይሙሉ
https://www.lmis.gov.et

ኦንላይን ፎርም አሞላሉን የሚያሳይ የቪዲዮ ማብራሪያ






፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
641 viewsMuJa. M, 16:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 14:08:18

ባሳለፍነው ቅዳሜ ማለትም በቀን #21/08/2015 ከጥዋቱ 1፡50 ላይ በእንጅባራ ዩንቨርሲቲ በተምዶ ኪዳነምህረት መግቢያ በመባል በሚታወቀው በር በኩል የዩንቨርሲቲው የሆቴልና ቱሪዝም ማኔጅመንት ተማሪ የሆነችው ተማሪ ኤደን ገብሩ ከቤተክርስቲያን መልስ የግቢ መታወቂያ ( ID Card ) አለመያዟን ተከትሎ ከዩንቨርሲቲው ተረኛ የጥበቃ ሠራተኞች ጋር በተፈጠረ አለመግባባት በደረሰባት አካላዊ ጥቃት ምክንያት በአሁኑ ሰዓት ተማሪዋ ከባድ ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ በርካታ የእንጅባራ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ጥቆማ አድርሰውናል።

ይህንን ጥቆማ በመቀበል ጉዳዩን ለማረጋገጥ ጉዳት የደረሰባት ተማሪ ጋር እንዲሁም የዩንቨርሲቲው ተማሪዎች ህብረትን አናግረናል።


<ተማሪ ኤደን ገብሩ ጋር በደወልንበት ጊዜ ተማሪዋ በስልክ ለማውራት አቅም ስላጠራት አጠገቧ ከነበሩት ጓደኞቿ ነው መረጃውን ያገኘነው>

ጉዳት በደረሰባት ተማሪ የእጅ ስልክ ደውለን ያገኘነውን መረጃ በአጭሩ ለመግለፅ

[ተማሪዋ ወደ ቤተክርስትያን ስትሄድ የግቢ መታወቂያ ትረሳለች። ወደ ግቢ ስትመለስ የግቢ መታወቂያ እንዳልያዘች በመንገር በመመገቢያ ካርድ ያስገቧት ዘንድ የጥበቃ ሠራተኞችን ስትጠይቅ አንዱ ጥበቃ ይገፈትራታል። አትገፍትረኝ ብላ እጁን ለማስለቀቅ ስትሞክር በጥፊ ይመታታል። ለምን በጥፊ ትመታኛለህ ስትለው በድጋሚ ገፍትሮ ጥሎ ጭኗ አካባቢ ይረግጣታል። ጭኗ አካባቢ የረገጣት ህመም ሲበረታባት ሌሌች ጥበቃዎች ጣልቃ ገብተው ወደ ግቢ እንድትገባ ይፈቅዱላታል። ዶርም ገብታ መታወቂያዋን ይዛ ክስ ለመመስረት ዲሲፕሊን ቢሮ ሄዳ ሰኞ ትመለስ ዘንድ ነግረዋት ከቢሮ ስትወጣ ራሷን ሳተች።አሁን ላይ ማህፀኗ አካባቢ የተቋጠረ ደም እንዳለ እንደተነገራትና ህመሙ ምናልባትም ቀዶ ህክምና ሊያስፈልገው እንደሚችል በእጅ ስልኳ መረጃ የሰጡን ከጎኗ ያሉ ጓደኞቿ ነግረውናል። ጓደኞቿ በተጨማሪ እንደነገሩን ከሆነ ተማሪዋ ሽንት ለመሽናትና ለመንቀሳቀስ እጅጉን እየተቸገረች እንደሆነ ገልፀው ዩንቨርሲቲው ጉዳዩን አለባብሶ ለማለፍ እንዳይሞክር ድምፅ እንሆንላት ዘንድ ጠይቀዋል።]


ይህን ጉዳይ በተመለከተ የእንጅባራ ዩንቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዘዳንት የሰጠን ምላሽ

ዩንቨርሲቲው መረጃው የደረሰው ቢሆንም ጉዳዩ በመጣራት ሂደት ላይ እንዳለ ፕሬዝዳንቱ ነግረውናል።አሁን ላይ ተማሪዋ የህክምና እርዳታ እያገኘች እንዳለ ገልፀው የህመሟን ምክንያት ማለትም ተማሪዋ ያቀረበችውን ምክንያት በተጨማሪም ራሷን ስታ በምትወድቅበት ጊዜ የመታት ነገር መኖር አለመኖሩን የባለሙያ ማረጋገጫ እንደሚያስፈልግና እንደ ፀጥታም መጠየቅ ያለባቸው ነገሮች በመኖራቸው ጉዳዩን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እያጣሩ እንደሚገኙና በሚናፈሱ ወሬዎች ላይ ብቻ ተመስርቶ የግል አስተያየት መስጠት እንደማይገባ ገልፀውልናል።


፨የተማሪ ኤደን ገብሩን ጉዳይ በተመለከተ የሚኖሩ መረጃዎችን ይዘን እንመለሳለን።


፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
460 viewsMuJa. M, 11:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ