Get Mystery Box with random crypto!

Freshman and Preparatory Students Channel

የቴሌግራም ቻናል አርማ g12_freshman — Freshman and Preparatory Students Channel F
የቴሌግራም ቻናል አርማ g12_freshman — Freshman and Preparatory Students Channel
የሰርጥ አድራሻ: @g12_freshman
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.97K
የሰርጥ መግለጫ

👇👇👇
https://www.youtube.com/c/atcnews1
Contact us 🔽
@atcads

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-06-09 19:24:11
የገንዘብ ሚንስትር አሕመድ ሽዴ መንግሥት በቀጣዩ በጀት ዓመት አዲስ የመንግሥት ሠራተኞች ቅጥር እንደማይፈጽም አስታውቀዋል።
ሚኒስትሩ ይህን የገለጡት፣ የቀጣዩን ዓመት በጀት ትናንት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት ነው። አንዳንድ የምክር ቤቱ አባላት ግን፣ መንግሥት አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር አዳዲስ ሠራተኞችን የማይቀጥር ከኾነ፣ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚመረቁ ምሩቃን እጣ ፋንታቸው አስቸጋሪ እንደሚኾን ስጋታቸውን ገልጸዋል። አሕመድ በበከላቸው፣ መንግሥት አዲስ የሲቪል ሰርቪስ መዋቅር ተግባራዊ እንደሚደረግና የመንግሥት መስሪያ ቤቶች አንዳንድ ነባር የሥራ ዘርፎቻቸውን እንዲያጥፉ እንደሚደረግ ተናግረዋል።


፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
2.0K viewsMuJa. M, edited  16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-08 08:29:07
ለወሎ ዩኒቨርሲቲ ኮምቦልቻ ካምፓስ remedial ተማሪዎች በሙሉ

ጉዳዩ፦ በ2015 ዓ.ም የሚሰጠውን የRemedial ተማሬዎች ውጤት ይመለከታል

አሳይመንት ከ30%፣አጋማሽ ፈተና ከ30%፣እንዲሁም የማጠቃልያ ፈተና ከ40% እንዲያዝ ተወስኖ #የነበረ ቢሆንም በ 28/09/2015 የተሰበሰበው የ Academic Standard and Curriculum Review Committee ከዚህ በፊት የነበረውን የውጤት አያያዝ እንደገና በመከለስ፡

፨አሳይመንት 50%፣
፨አጋማሽ ፈተና 20% እንዲሁም
፨የማጠቃልያ ፈተና ከ30% እንዲያዝ ተወስኗል።

     

፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
2.2K viewsMuJa. M, 05:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 13:03:23 የክልል የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሀሰተኛ የትምህርትና ሲኦሲ ማስረጃዎች መበራከታቸው ተገለጸ፡፡

በሀገሪቱ ከክልል የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚመጡ የድፕሎማ የትምህርት እና ሲኦሲ ማስረጃዎች ሀሰተኝነት አብዛኛዉን ቁጥር መያዙን የተናገሩት በኢፌድሪ ትምህርት እና ስልጠና ባለ ስልጣን የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ እና አቻ ግመታ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ገብረ መድህን ናቸው፡፡
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ እንደቆየና ጉድለቶች እየታዩ በተለይም ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን በተመለከተ የተለያዩ እርምጃዎች ሲዎሰድ እንደቆየ ጠቁመዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማስረጃዎችም ሊፈተሹ የሚገባቸዉ በመሆኑ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ወደ ተግባር ለመግባት ዝግጅቶችን እንዳጠናቀቀ ነው የተናገሩት፡፡
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የተማሪዎቻቸዉን መረጃ አሟልተዉ እንዲልኩ የተጠየቁ የግል ከፍተኛ ትምህርተ ተቋማት አብዛኞቹ አጠናቀዉ ማስገባታቸዉን እና ቀሪዎቹም በቅርብ ጊዜ ውስጥ አጠናቀዉ እንደሚያስገቡ ይጠበቃል ሲሉ ለአሀዱ ገልጸዋል፡፡

የግልም ሆኑ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርተ ተቋማት ተማሪዎች በዘንደሮዉ አመት የሚሰጠዉን የመዉጫ ፈተና በአግባቡ እንዲዎስዱና ከሀሰተኛ መረጃ እራሳቸዉን እንዲጠብቁም መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

ምንጭ፡አሀዱ ሬድዮ

፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
2.0K viewsMuJa. M, 10:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 23:03:50
#Update

ራያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በአካል ቀርበው እንዲመዘገቡ ጥሪ አቀረበ።

ራያ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛና ተከታታይ ትምህርት መርሐ ግብር ትምህርታቸውን ለመከታተል ቀደም ሲል ዩኒቨርሲቲዉ ባወጣዉ ማስታወቅያ መሰረት የተመዘገቡ (የዩኒቨርሲቲዉና ከሌሎች ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያመለከቱ) ተማሪዎች ሰኔ 6 እና 7 / 2015 ዓ.ም በራያ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት በአካል በመገኘት እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።


፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
2.0K viewsMuJa. M, 20:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 13:43:02 “በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ምረቃ መርሐግብር ላይ መሳተፍ የሚችሉት የመዉጫ ፈተናዉን ያለፉ ተማሪዎች ብቻ ናቸዉ“- የትምህርት ሚኒስቴር

በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ምረቃ መርሐግብር ላይ መሳተፍ የሚችሉት የመዉጫ ፈተናዉን ያለፉ ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።ሚኒስቴሩ ከፈተና አስተዳደር እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ፤ ለኹሉም የመንግሥት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲሁም የክልል ትምህርት ቢሮዎች በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ግንቦት 23/2015 የተፈረመ ደብዳቤ ልኳል።

በደብዳቤውም ሚኒስቴሩ የፈተና ቀናትን ያሳወቀ ሲሆን፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምረቃ መርሐ ግብር ቀናቸዉንም ወስኗል። በዚህም መሰረት ተቋማቱ የተማሪዎቻቸዉን የምረቃ መርሐግብር ከ ሐምሌ 11 እስከ 16 ባሉት ቀናት ማከናወን እንዳለባቸዉ አሳስቧል።በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይም መሳተፍ የሚችሉት የመዉጫ ፈተናዉን ያለፉ ተማሪዎች ብቻ መሆናቸዉን ጠቅሷል።

በሌላ በኩል፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የ12ኛ ክፍል ሬሚዲያል መርሐግብር ተማሪዎቻቸዉን ዉጤት እና ለመጀመሪያ አመት የዩኒቨርስቲ ተማሪነት መብቃታቸዉን እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲያሳዉቁኝ ብሏል።የ2015 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ከ ሐምሌ 19 እስከ 30/2015 መመዘኛዉን የሚወስዱ እንደመሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ዝግጅታቸዉን ከሐምሌ 16 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ለፈተናዉ ብቻ መሆን እንዳለበት ገልጿል።

በ2015 የመዉጫ ፈተና ለመዉሰድ የተመዘገቡ እጩ ምሩቃን እና ባለፉት ዓመታት የህግ ትምህርት የመዉጫ ፈተና ወስደዉ ማለፊያ ዉጤት ያላስመዘገቡ ተማሪዎች ከ ሐምሌ 3 እስከ 8 ባሉት ቀናት በመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች እንዲፈተኑ እና ሐምሌ 10 ቀንም ዉጤታቸዉ የሚታወቅበት መሆኑንም ሚኒስቴሩ ጨምሮ አስታዉቋል።

[Addis Maleda]

፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
1.8K viewsMuJa. M, 10:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 10:55:48
#MoE

አገር አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡባቸው እና የምረቃ ቀናት እንዲሁም የሬሜዲያ ፈተና ወጤት አያያዝ ላይ ቅያሪ ተደርጓል።

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ግንቦት 9 ቀን 2015 ዓ/ም ያስተላለፈውን ሴርኩላር በተመለከተ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከክልል ት/ቢሮ አመራሮች ጋር በድጋሚ ግንቦት 22 ቀን 2015 በበይነ-መረብ ውይይት አድርጓል።

በውይይቱ መሰረትም ፦

- ፈተናዎች የሚሰጡባቸው ቀናት፣

- የተማሪዎች ምረቃ በዓል፣

- የሪሜዲያል ፈተና ውጤት አያያዝ በተመለከተ ቅያሪ መደረጉን ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች፣ ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ለሁሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች በፃፈው ደብዳቤ ገልጿል።

- በ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ ፤ ተቋማት ፊተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለፅና በ2016 ፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 30 ከመቶ፣ #በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና 70 ከመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደት እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲጠናቀቅ ትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስቀምጧል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ምስል ያንብቡ

፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
1.6K viewsMuJa. M, 07:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 20:04:18 #AASTU



የ2015ዓ.ም ዲፖርትመንት ምደባ ተከትሎ አንዳንድ ተማሪዎች በደረሳቸው ምደባ ላይ ቅሬታ ማቅረባቸው ይታወሳል። በመሆኑም የቅሬታችሁን አግባብነት ለማወቅ ያክል የአ.አ.ሳ.ቴ.ዩ ግቢ ለምደባ የተጠቀማቸው 5 መስፈርቶች ይሄን ይመስላሉ:-


1. የዲፖርትመንት ተማሪዎች መቀበል አቅም: እያንዱ ዲፖርትመንት በየአመቱ አጠቃላይ  200 ተማሪዎችን የመቀበል አቅም አለው። ይሁን እንጂ በ3 ዲፓርትመንቶች ማለትም በኤሌክትሪካል፣ በሲቪል እና በኤሌክትሮ ሜካኒካል የተመዘገበው ተማሪ ብዛት እሄን ይመስል ነበር:-

Electrical engineering: 535
Civil engineering: 201
Electro-mechanical engineering:209

ያለውን የተማሪ ቁጥር ታሳቢ በማድረግ  ዲፓርትመንቶች የመቀበል አቅማቸውን ወደ 250 ተማሪ ከፍ አድርገዋል። ነገር ግን ኤሌክትሪካል ዲፓርትመንት ላይ የተፈጠረውን የተማሪ ብዛትና የመቀበያ ቦታ አለመጣጣም በሚቀጥሉት የመለያ  መስፈረቶች መሰረት አወዳድሮ  285 ተማሪዎችን ለመጣል ተገዷል።


2.የተማሪ ፍላጐት: ተማሪዎች የመረጡት ዲፓርትመንት የመቀበል አቅም ያለው እንደሆነ፣ የመጀመሪያ ምሩጫቸው የተጠበቀ ይሆናል። ነገር ግን ዲፓርትመንቱ ቦታ የሌለው እንደሄነ፣ ተማሪዎች እታች ባሉት መለያ መስፈርት መሰረት ተማሪዎች ቦታ ባላቸው ዲፓርትመንቶች ውስጥ ባስገቡት ምርጫ ቅደም ተከተል መሰረት ይመደባሉ።

3. ውጤት ( cumulative) : ቦታ እጥረት እና ፍላጐት ተከትሎ፣ ተማሪዎች ባገኙት የትምህርት ውጤት ይወዳደራሉ። ፉክክር የነበረባቸው  3 ዲፓርትመንት መቀበያ ዝቅተኛ ነጥብ እንደሚከተለው ነበር

Electrical engineering
Male: 3.28        female: 2.8
Civil engineering
2.28 both
Electro mechanical engineering
3.15 both


4. በሁሉም ዲፓርትመንት 25% ለሴት ተማሪዎች የተቀመጠ ነው(affirmative action(


5. Emerging regions ወይም እያደጉ ካሉ ክልላት የመጡ ተማሪዎች ምርጫቸው 100% እንደተጠበቀ ነው የሚሆነው።


የተማሪዎች ሕብረት የአካዳሚክስ ዘርፍ ተጠሪ


@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
1.3K viewsMuJa. M, 17:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 11:00:58
የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ፈተና ማጠናቀቂያ ጊዜ   ተገለፀ።

በ2014ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው በልዩ ሁኔታ በሪሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ የሆኑ  ተማሪዎች ፈተናና ተዘጋጅቶ እንዲላክና አጠቃላይ ሂደቱ  እስከ ሰኔ 30/2015ዓ.ም ድረስ እንዲጠናቀቅ በትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ ተቀምጧል።

ፈተናውም በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው በተሰጠው ትምህርት መሠረት ከማዕከል በጋራ ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ  ተብሏል ።

በዚህም መሰረት በሴሚስተሩ በተሰጠው ትምህርት የተቋማት የውስጥ ፈተና ውጤት 50 ከመቶ እንዲሁም በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና ውጤት 50 ከመቶ  ይይዛል ተብሏል።

ተማሪዎችም በ2016 ዓ.ም ትምህርታቸውን ለመከታተል ብቁ ሆነው ለመገኘት የሁለቱ ድምር አማካይ 50 ከመቶና በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋልም ተብሏል።

ዩኒቨርሲቲዎችም ፈተናውን በማስተዳደርና ውጤት በመግለጽ በ2016 የፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ የሆኑ ተማሪዎችን  ለይተው እስከ ሰኔ 30/2015ዓም እንዲያጠናቅቁ ተገልጿል።

ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን ስራ በማጠናቀቅ የ2016 የትምህርት ካሌንደር የተስተካከለ እንዲሆን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ  ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

ትምህርት ሚኒስቴር

፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
1.1K viewsMuJa. M, 08:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-18 20:56:05
ወላይታ ሶዶ ዩንቨርሲቲ ለመደበኛ የቅድመ ምረቃ፣የድህረ ምረቃ፣የሬሚድያል እና ለክረምት ተማሪዎቹ ከትምህርት ሚኒስቴር በተላከው መርሃ-ግብር መሰረት አካዳሚክ ካሌንደሩ ላይ ለውጥ አድርጓል።


፨የግቢው ተማሪዎች ከላይ ያሉትን ምስሎች ይመልከቱ


፨ለጥቆማ
@atc_newsbot
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@atc_news @atc_news
@atc_news @atc_news
21.9K viewsMuJa. M, 17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-18 19:37:02
ሀረማያ ዩንቨርሲቲ
1.4K viewsMuJa. M, 16:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ