Get Mystery Box with random crypto!

🇪🇹 E.Z መረጃ 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ ezmerejaet — 🇪🇹 E.Z መረጃ 🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ ezmerejaet — 🇪🇹 E.Z መረጃ 🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @ezmerejaet
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4
የሰርጥ መግለጫ

እንዴት አደርሽ ኢትዮጵያዬ ! 🇪🇹

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2022-11-05 21:02:25 ፈጣን ወቅታዊ ተአማኒ አሁናዊ መረጃዎችን የጋዜጠኝነት ሙያዊ ስነምግባር በጠበቀ መልኩ የሚቀርብበትን ቻናል እንጠቁማችሁ
@faste_merjanet
@faste_merjanet
@faste_merjanet
2.6K viewsedited  18:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-05 20:26:18
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ዋና ሃላፊ አቶ ተመስገን ጥሩነህ የ2 ወራት የግንባር ቆይታቸውን አጠናቀው ወደ ቢሯቸው ተመልሰዋል::

@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
3.2K views17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-05 20:03:51 የህወሓት ታጣቂዎች ትጥቅ በሚፈቱበት ሁኔታ ላይ ለመወያየት የሁለቱ ወታደራዊ አመራሮች የፊታችን ሰኞ በኬኒያ ሊገኛኙ ነዉ

በደቡብ አፍሪካዋ ፕሪቶሪያ በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን አስታወቁ።

አምባሳደሩ ሬድዋን ሁሴን የስምምነት ሂደቱን አስመልክቶ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ ሲል አል አይን ዘግቧል።

በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል በደቡብ አፍሪካ ሲካሄድ የነበረው የድርድር ውጤት በሳለፍነው ረቡዕ ምሽት ይፋ መደረጉ የሚታወስ ሲሆን፤ በድርድሩ ስምምነት ከተደረሰባቸው ጉዳዮች ውስጥም ግጭትን በዘላቂነት ማቆም፣ ሰብዓዊ እርዳታን ያለገደብ ማድረስ፣ በሀገሪቱ ህገ መንግስት መሰረት ህግና ስርዓትን ማስከበር አንዲሁም የህወሓት ታጣቂዎችን ትጥቅ ማስፈታትየሚሉት ተጠቃሾች ናቸው።

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በማብራሪያቸው ፤  በስምምነቱ መሠረት የህወሓት ታጣቂዎች ትጥቅ በሚፈቱበት ሁኔታ ላይ ለመወያየት የሁለቱ ወታደራዊ አመራሮች የስልክ ልውውጥ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

በዚህም የሁለቱ ወታደራዊ አመራሮች የፊታችን ሰኞ በኬንያ ናይሮቢ እንደሚገናኙ እና ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ ውይይት እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል።

በኢትዮጵያ መንግስት በኩል የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የደህንነት ጉዳዮች አማካሪ የሆኑት አምባሳደር ሬድዋን እና በህወሓት በኩል ቃል አቀባዩ አቶ ጌታቸው ረዳ 10 ገፆችና 15 አንቀፆች ባሉት የሰላም ስምምነት ሰነድ ላይ ፊርማቸውን አኑረዋል፡፡ የህወሓቱ ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ የተደረሰው ስምምነት ትልቅ ብስራት ነው ማለታቸዉ ይታወሳል።

የሰላም ስምምነቱን ቀዳሚ የሆነዉን ህወሓት ትጥቅ በሚፈታበት ዙሪያ ለመናገገር እና ተግባራዊ ለማድረግ የሁለቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች የፊታችን ሰኞ በኬኒያ ሊገናኙ መሆኑ ተገልጿል።


@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
3.6K views17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-05 19:29:36 አርበኛ ዘመነ ካሴ የክስ መጥሪያ ደርሶታል፤ ለጥቅምት 28/2015 በባህር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይቀርባል።

የአርበኛ ዘመነ ካሴ ጠበቃ ህሩይ ባዩ የሚከተለውን መረጃ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጹ አጋርቷል:_

አርበኛ ዘመነ ካሴን በተመለከተ በ25/02/2015 ከመሸ የሃሰት ክሱ መጥሪያ ደርሶታል ቀጠሮውም በ28/02/2015 በባህር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከጥዋቱ 3:00 ነው በዚሁ ችሎት የሚቀርብ በመሆኑና አርበኛው በግልፅ ችሎት የመዳኘት መብት ስላለው ችሎት ትከታተሉ ዘንድ መልዕክት አስተላልፎላችኋል።

@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
3.7K viewsedited  16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-05 19:01:21
በኢፊድሪ መንግስት እና በህወሓት መካከል የተፈረመውን የተኩስ አቁም እና ስምምነት አስመልክቶ ከኦፌኮ የተሰጠ መግለጫ


@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
4.0K viewsedited  16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-05 17:06:39
በሚቀጡልት 3 እና 4 ሳምንታት እራሱን TDF ብሎ የሚጠራው የህወሓት ታጣቂና ሚሊሻ ልዩ ሀይል ትጥቁን ይፈታል:: ትጥቁን የፈታው ታጣቂ ወደ ተሃድሶ የሚገባው ይገባል ወደ ህብረተሰቡ የሚቀላቀለው ይቀላቀላል መከላክያ ሰራዊት ሙሉ በሙሉ መቀሌ በመግባት ኩያ የተባለው ሰሜን ዕዝ የነበረበት ካፕን ይረከባል::

የተደራጁ የፌደራል ፓሊስ አባላት የመንግስት ተቋማትና ተረክበው ጥበቃ ያደርጋሉ በየ ከተማው በመግባት ህዝቡ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲያደርግ በኮማንድ ፓስት የሚመራ ልዩ ሃይል ባለ ቀይ መለዮ ኮማንዶዎች ግዚያዊ የጸጥታን ማስከበር ስራዎችን በትግራይ ይሰራሉ::

@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
4.7K viewsedited  14:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-05 11:36:04
ሩሲያ ስንዴዋን ለድሃ የአፍሪካ ሀገራት በነጻ ልትሰጥ እንደሆነ ተገለጸ።

የቱርክ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ኤርዶሃን ከሩሲያ አቻቸው ቭለድሚር ፑቲን ጋር በስልክ ባደረጉት ውይይት ሩሲያ በነጻ ስንዴዋን ወደ ድሃ ሀገራት ለማጓጓዝ መስማማቷ ተገልጿል።

የሩሲያን ስንዴ በነጻ ከሚሰጣቸው ሀገራት መካከልም ሶማሊያ፣ ጅቡቲ እና ሱዳን የተጠቀሱ ሲሆን ሀገራቱ የምግብ ችግር እንዳለባቸውም በዘገባው ላይ ተጠቅሷል። በተመድ እና ቱርክ አደራዳሪነት በጥቁር ባህር የጉዞ እና የንግድ መስመር ላይ ከ10 ሚሊዮን በላይ ቶን ስንዴ መጓጓዙ ተገልጿል።

via - Alain

@Ezmerejaet
@Ezmerejaet
5.5K viewsedited  08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-05 11:31:54 በጠንካራ የጋዜጠኝነት ሙያዊ ስነምግባር በተላበሰ ሚዛናዊ አዘጋገብ የተመሠረተዉ ሀገራችን ዉስጥ አሉ ከሚባሉ ትልልቅ ሚዲያዎች ዉስጥ ግንባር ቀደም የሆነዉን ቻናል እንጋብዛችሁ
https://t.me/+0j24gRc38Gg2OGVk
5.3K views08:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-05 08:01:37
መረጃ

የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና የህወሓት ታጣቂዎች አዛዥ ታደሰ ወረደ ሰለ ሠላም ስምምነቱ አፈፃፀም በስልክ ተነጋግረዋል።

በቀጣዩቹ ጥቂት ቀናት ውስጥም የህወሓት ታጣቂዎች ትጥቅ ስለሚፈቱበት ዝርዝር አፈፃፀም ዙሪያ በአካል ለመነጋገር ቀጠሮ መያዛቸውን ምንጮች ገልፀዋል።
1.8K views05:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-04 20:11:06 በነ አቶ ምትኩ ካሳ የሙስና የክስ መዝገብ በቁጥጥር ስር ሳይውሉ የቀሩ ተከሳሾች የመኖሪያ አድራሻን ዓቃቢህግ በክሱ ላይ አለመግለጹ ውዝግብ አስነሳ።

በተለያዩ ጊዜያት በአማራ፣ አፋር፣ ኦሮሚያ፣ ደቡብ ክልሎች እና በሌሎችም አካባቢዎች በሚገኙ የግብረሰናይ ድርጅቱ ማዕከላት የተፈናቃይ ተረጂዎችን ቁጥር በማጋነን ምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ እህልና ቁሳቁሶችን ከብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን መጋዘን በማውጣት ለተረጂዎች ሳይደርስ ለዱቄት ፋብሪካዎችና ለሌሎች ግለሰቦች በሚሊዮን ብሮች በመሸጥ እንዲሁም ብድርና ድጋፍ በሚል ሰበብ በህገወጥ መንገድ ከብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በመቶ ሚሊየን የሚገመት ገንዘብ ለእርዳታ ድርጅቱ ሲሰጥ ነበር በማለት ዓቃቢህግ በነሃሴ 20 ቀን 2014 ዓ/ም አቶ ምትኩ ካሳን ጨምሮ በአጠቃላይ በ13 ተከሳሾች ላይ በየደረጃው የሙስና ወንጀል ክስ መመስረቱ ይታወሳል።

አቶ ምትኩና 11ኛ ተከሳሽ አቶ ዩሀንስ በላይ ከማረሚያ ቤት እና ቀደም ሲል በዋስ ወቶ በውጭ ሆኖ ጉዳዩን የሚከታተለው እያሱ ምትኩ እንዲሁም በወንጀል የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረትን ህጋዊ አድርጎ መጠቀም ወንጀል የተከሰሱበት አንቀጽ ዋስትና ስለማያስከለክል በጥቅምት 8 ቀን በነበረ ቀጠሮ በ50 ሺህ ብር ዋስ ከስር ተፈተው በውጭ እንዲከታተሉ የተፈቀደላቸው አቶ ምትኩ ካሳ ባለቤት ወ/ሮ ሶፊያ ጀማል : ልጃቸው ወ/ሮ ሚልካ ምትኩ እና ያልተያዘው የ12 ኛ ተከሳሽ ባለቤት 13ኛ ተከሳሽ ወ/ሮ ህይወት ከበደ በዛሬው ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 5ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በባለፈው ቀጠሮ የተከሳሽ ጠበቆች ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ ላይ የዓቃቢህግ መልስን ለመጠባበቅና በቁጥጥር ስር ያልዋሉ 7 ተከሳሾችን ፖሊስ አፈላልጎ እንዲያቀርባቸው የሰጠውን ትዛዝ ውጤት ለመጠባበቅ ተሰይሟል።

ከሳሽ ዓቃቢህግ በሰዓቷ አለመገኘቷን ተከትሎ ችሎቱ ለ 10 ደቂቃ ገደማ ዓቃቢህግን ለመጠበቅ ተገዷል።

ስልክ ከተደወለ በኋላ ዓቃቢህጓ በችሎት የተሰየመች ሲሆን
የችሎቱ ሰብሳቢ ዳኛ ለሌላ ጊዜ በቀጠሮ ሰዓት ከ3:30 ጀምሮ እንዲገኙ ማሳሰቢያ ሰተዋል።

ይሁንና በዛሬው ቀጠሮ በቁጥጥር ስር ያልዋሉ 7 ተሳሾች ዛሬም ሳይቀርቡ ቀርተዋል።

ፖሊስ በዛሬው ቀጠሮ ተከሳሾቹን በአድራሻቸው አፈላልጓ ለማቅረብ እንዲያስችለው እረጅም ቀጠሮ እንዲሰጠው በጽሁፍ ጠይቋል።

የተከሳሽ ጠበቆች በበኩላቸው ለፖሊስ መጥሪያ እንዲያደርስ ሁለት ጊዜ ቀጠሮ ተሰቶት ተከሳሾቹን ሳያቀርብ መቅረቱን አስታውሰዋል።

ጠበቆቹ አቶ ምትኩካሳ እና 11 ኛ ተከሳሽ ዩሀንስ በላይ ዋስትና ተከልክለው በማረሚያ ቤት የሚገኙ መሆናቸውን ጠቅሰው የነዚህ ተከሳሾች የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብታቸውን በጠበቀ መልኩ ፍርድ ቤቱ ሊመለከትላቸው እንደሚገባ ጠይቀዋል።

በተጨማሪም ጠበቆቹ ለፖሊስ ተጨማሪ ጊዜ ሊሰጥ አይገባም ሲሉ ተከራክረዋል።

ከሳሽ ዓቃቢህግ በበኩሏ የሌሉ ተከሳሾች መቅረብ ስላለባቸው ፖሊስ በሚሰሩበት መስሪያ ቤት የመኖሪያ አድራሻቸው ጠይቆ እንዲያቀርባቸው ለማስቻልና ካላቀረበም ማረጋገጪያ እንዲያመጣ ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጥ ጠይቃለች።

ሆኖም በክሱ የተከሳሾች አድራሻ ባለመጠቀሱና የመኖሪያ አድራሻ ፖሊስ ከሚሰሩበት መስሪያ ቤት ጠይቆ ማቅረብ እንዲችል ያላቀረበበትን ማረጋገጪያ እንዲያቀርብ የሚለው የዓቃቢህጓ አስተያየት ተከትሎ በችሎቱ ውዝግብ አስተስቷል።

''በቁጥጥር ስር ሳይውሉ ተከሳሾችን መጀመሪያ ክስ ስትመሰርቱ ለምን የመኖሪያ አድራሻን አላካተታችሁም''? የሚል ጥያቄ በችሎቱ ዳኞች ለዓቃቢህ ቀርቧል።

ዓቃቂህጓ ''የመኖሪያ አድራሻቸው በመርማሪ ስላልተገኘ ነው በክሱ ያልተካተተው '' ስትል ምላሽ ሰታለች።

የችሎቱ ዳኞች ሌላ ጥያቄ አስከትለው ማለትም '' የተከሳሾችን መስሪያ ቤት ካወቃችሁ ታድያ ለምን እራሳችሁ ከመስሪያ ቤታቸው የመኖሪያ አድሪሻቸውን ጠይቃችሁ በክሱ ለምንአሟልታችሁ አላቀረባችሁም ''?የሚል ጥያቄ ዓቃቢህጓ ተጠይቃለች።

መዝገቡን ከፖሊስ የተረከብነው ስትል መልስ ሰታለች።

በጠበቆች በኩል የተከሳሶች የመኖሪያ አድራሻ በክሱ ላይ ባልተገለጸበት ሁኔታ በአድራሻቸው ፖሊስ አፈላልጎ ያቅርብ መባሉ አግባብ አለመሆኑ የተገለጸ ሲሆን አድራሻቸው በሌለበት ሁኔታ እንዴት ማረጋገጫ ለማቅረብ ተለዋጭ ቀጠሮ ይጠየቃል የሚሉ መከራከሪያ ነጥቦች ተነስተዋል።

ክርክሩን የተከታተለው ፍርድ ቤቱ ያልተያዙ ተከሳሾች ማለትም 2ኛ ተከሳሽ የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽ የፋይናንስ ዳሪክተር አቶ አረጋው ለማ : 3ኛ የኤልሻዳይ ሪሊፍ ኤንድ ዴቭሎፕመንት አሶሴሸን ዋና ዳይሬክተር የማነ ወ/ማሪያም 4ኛ ተከሳሽ ዶ/ር ዮናስ ወ/ትንሳኤ : 5ኛ በኤልሻዳይ ድርጅት የፋይናንስ ዘርፍ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ደሞዝ ሀይሉ 9ኛ ተከሳሽ የኤልሻዳይ ድርጅት የመጋዘን ንብረት መዝጋቢ አቶ መብራቱ አሰፋ ወ/ማርያም :10ኛ የኤልሻዳይ ድርጅት ስቶር ኦፊሰርና የመጋዘን ንብረት ክፍል ሰራተኛ የሆነው አቶ ገ/ሚካኤል አብርሐ እና በግል ስራ የሚተዳደሩት 12 ኛ ተከሳሽ ጌቱ አስራትን በሚመለከት ለፖሊስ ትዛዝ መሰጠት አለበት ወይስ ትዛዝ መሰጠት የለበትም የሚለውን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለፊታችን ማክሰኞ ለጥቅምት 29 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰቷል።
4.5K views17:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ