Get Mystery Box with random crypto!

etv zena

የቴሌግራም ቻናል አርማ etv_zena_57 — etv zena E
የቴሌግራም ቻናል አርማ etv_zena_57 — etv zena
የሰርጥ አድራሻ: @etv_zena_57
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 6.73K
የሰርጥ መግለጫ

For any comment @etv_zena_57_bot

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-04-12 18:54:42
እኛ safe tips ነን

ከ 2K በላይ ተከታይ ያለው

፦በቢቲንግ ብዙ አመት ልምድ ካላቸው Draw FIXED ሰሪዎች ጋር ስምምነት በ መፍጠር ODD Draw FIXED GAME እንሰጣለን።
፦ለ vip ትልቅ ቅናሽ አዘጋጅተናል።
6.1K views15:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-28 22:33:01 Please follow me on tik tok ከሰአታቹ ላይ ትንሽ ሰከንዶች ቢወስድባቹ ነው my link is @footballstuff1738 search for it on tik tok
@footballstuff1738
@footballstuff1738
@footballstuff1738
9.3K views19:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-30 08:27:37
አርቲስት ሃጫሉ መገደሉን ፖሊስ አስታወቀ!

አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ በጥይት ተመትቶ ሆስፒታል ከገባ በኃላ እርዳት ሲደረግለት ቆይቶ ህይወቱ ማለፉን ማረጋገጡን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።

ከግድያው ጋር በተያያዘ የተወሰኑ ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን ፖሊስ ያስታወቀ ሲሆን በአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ የተሳተፉ አካላትን ፖሊስ የማጣራት ስራ በመስራት ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጿል።
15.7K viewsedited  05:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-30 08:27:37
አጭር መረጃ ኮቪድ-19 ኢትዮጵያ ፦

- በ3 ቀናት ብቻ 742 ሰዎች ከኮቪድ-19 በተደረገላቸው ህክምና አገግመዋል።

- በ3 ቀናት ውስጥ ከኮቪድ-19 ጋር በተያያዘ የ14 ሰዎች ሞት ሪፖርት ተደርጓል።

- በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ3 ቀናት 322 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።

- በኢትዮጵያ አሁን ያለው አክቲቭ ኬዝ 3,311 ነው።

- በአማራ ክልል በኮቪድ-19 ከተያዙ ከአጠቃላይ 313 ሰዎች መካከል 226 ሰዎች በምዕ/ጎንደር ዞን የተመዘገቡ ናቸው።

- በኦሮሚያ ክልል በ3 ቀናት ውስጥ 28 ሰዎች ላይ ቫይረሱ የተገኘ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ ሰባቱ (7) ከቡራዩ ናቸው።

- በትግራይ ክልል ሁለተኛው (2) የኮቪድ-19 ሞት ሪፖርት ተደርጓል። በሌላ በኩል አሁን በክልሉ ያለው አክቲቭ ኬዝ 91 ነው፤ ከ212 ሰዎች 121 ሰዎች አገግመዋል።
13.8K viewsedited  05:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-30 08:27:37
'ኤዲ5-ኤንኮቭ' የኮቪድ-19 ክትባት!

በሙከራ ላይ ያለ የኮሮና ቫይረስ ክትባት በቻይና መከላከያ ኃይል ውስጥ ጥቅም ላይ እንዲውል መፈቀዱን #BBC ዘግቧል።

'ኤዲ5-ኤንኮቭ' (Ad5-nCoV) የተባለው ክትባት ፣ አካልን ከሽታውን በማስተዋወቅና እንዲከላከል በማድረግ ፣ የመከላከል አቅምን በመገንባት ሰዎች በቫይረሱ እንዳይያዙ ያደርጋል ወይም አያደርግም የሚለውን ለመፈተሽ እየተሞከሩ ካሉ 150 ክትባቶች መካከል አንዱ ነው።

ክትባቱ በመከላከያ ኃይሉ የሕክምና ሳይንስ አካዳሚ ስር በሲኖ ባዮሎጂክስ የባዮቴክኖሎጂ ተቋም የተሰራ ሲሆን በጎ ፈቃደኛ በሆኑ ሰዎች ላይ እንዲሞከር በሚል ለክልኒክ ሙከራ የገባ የመጀመሪያው ክትባት ነው።

በጥናቱ 108 አዋቂዎች በበጎ ፈቃደኝነት የተሳተፉ ሲሆን ክትባቱ ጉዳት የማያደርስ እንዲሁም የመከላከል አቅምን እንደሚያዳብር መረጋገጡ በሕክምና ጆርናሉ ላንሴት ላይ ተዘግቧል።

ነገር ግን ክትባቱን የወሰዱ ሰዎች ኮሮናቫይርስን እንዳይያዙ የሚያደርግ የመከላከል አቅም ያዳብራሉ ወይ የሚለው ላይ ማረጋገጫ አልተገኘም። ለወታደሮቹ ክትባቱን መስጠት ተመራማሪዎችን እንደሚረዳም ተነግሯል። እስካሁን ድረስ ለሰፊው ሕዝብ የሚያገለግል ክትባት ገና አልተሰራም ሲል #BBC አስነብቧል።
9.3K viewsedited  05:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-29 12:33:44
ፕሬዝዳንት ዩዋን ኦርላዶን ሄርናንዴዝ በኮሮና ቫይረስ ተያዙ!

(በአል አይን - AlAin)

የሁንዱራሱ ፕሬዝዳንት ዩዋን ኦርላንዶን ሄርናንዴዝ በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ተይዘው ሆስፒታል እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡

ፕሬዝዳንቱ ቅዳሜ ዕለት ዶክዩመቶችን እያነበቡ የሚያሳዩ ሁለት ፎቶዎችን በትዊተር ገጻቸው “አሁንም ድረስ ሆስፒታል ውስጥ ነኝ ፤ ነገር ግን ሕዝቤን ለማገልገል ሁልጊዜም እሰራለሁ” ከሚል ጽሁፍ ጋር አስፍረዋል፡፡

በሆስፒታል ሆነው የተለያዩ ህግና ደንቦችን መፈረማቸውንም ፕሬዝዳንት ሄርናንዴዝ ገልጸዋል፡፡

አንድ የመንግስት ቃል አቀባይ ፕሬዝዳንቱ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙና መሻሻል እያሳዩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ሲኤንኤን እንደዘገበው ፕሬዝዳንቱ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው እ.ኤ.አ. ሰኔ 16 ሲሆን ባለቤታቸው እና ሁለት ረዳቶቻቸውም ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል።
6.9K viewsedited  09:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-29 12:33:44
በ @tikvahethmagazine በኩል እነዚህ መረጃዎችን ከነምንጮቻቸው አሰባስበንላችሁ አስቀምጠናል ፦

- በጣሊያን ኤምባሲ ውስጥ ለ29 ዓመታት ለተጠለሉ የቀድሞ የደርግ ከፍተኛ ባለሥልጣናት መንግሥት ምሕረት አድርጎላቸው ቀሪ ሕይወታቸውን ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲያሳልፉ ባልደረቦቻቸው በደብዳቤ ጥያቄ አቀርበዋል።

- የዎላይታ የቀድሞ ክብር ተሰናባች መካላከያ ሰራዊት አባላት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ማደረጋቸው ተገልጿል።

- የመቐለ ዩኒቨርሲቲ (ሞሞና ኤፍ ኤም 96.4) ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው ቤተሰቦች የመጡና ትምህርታቸው በሬድዮ መከታተል ለማይችሉ ተማሬዎች የሬድዮ ሬሲቨሮችና የእጅ ስልኮችን አበርክቷል።

- የጋሞ ሕዝብ በስነ-ልቦና ከሚቀራረባቸው ህዝቦች ጋር አደረጃጀት መፍጠር ካልቻለ ህገ-መንግስታዊ መብቱን ተጠቅሞ የራሱን ክልል የመመስረት ጥያቄውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የጋሞ ዞን አስተዳደር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

- የሲዳማ ህዝብ ልዩ ምልክት የሆነውን 'የሻፌታ ታወር' ግንባታ ስምምነት የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በዛሬው ዕለት ተፈራርሟል፡፡

- የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ የነበሩት እና ምርጫ ያሸነፉት ላዛረስ ቻኩዌራ አዲሱ የማላዊ ፕሬዚዳንት በመሆን ዛሬ ቃለ መሃላ መፈጸማቸው ተገልጿል።
6.3K viewsedited  09:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-28 11:13:10
በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች ከ10 ሚሊዮን አለፉ!

በመላው ዓለም በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር ቁጥር ከ10 ሚሊዮን መብለጡን የworldometers ድረገፅ መረጃ ያሳያል።

ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ የሟቾች ቁጥር 498,952 የደረሰ ሲሆን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች 5,414,648 ደርሰዋል።

ከፍተኛ የሰው ቁጥር በቫይረሱ ከተያዘባቸው የዓለም ሀገራት መካከል አሜሪካ (2.5 ሚሊዮን ሰዎች) ፣ ብራዚል (1.2 ሚሊዮን ሰዎች) እና ሩሲያ (627,627 ሰዎች) በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ።
5.1K viewsedited  08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-28 11:13:10
የሃይድሮክሲክሎሮከዊን እጥረት እያጋጠመ ነው!

ሃይድሮክሲክሎሮከዊን የተባለው መድኃኒትን ለኮሮና ቫይረስ ህክምና እንዲውል የብራዚሉ ፕሬዝዳንት ጃይር ቦልሶናሮ እና የአሜሪካው አቻቸው ዶናልድ ትራምፕ ሲቀሰቅሱ እንደነበረ አይዘነጋም።

በዚህም ሳቢያ ሃይድሮክሲክሎሮከዊን መድኃኒት ፍላጎት በከፍተኛ ደረጃ በመጨመሩ በአቅርቦት ላይ እጥረት ማስከተሉንና የዋጋ ጭማሪ መፈጠሩን #BBC ዘግቧል።

ይህ ሁኔታ ሃይድሮክሲክሎሮከዊን ለተለያዩ ህክምናዎች በሚወስዱ ህሙማን ላይ ቀጥተኛ ጫናን ማስከተሉ BBC አስነብቧል።

በቅርቡ የተደረገ ሙከራ መድኃኒቱ ኮቪድ-19 ለማከም አስተዋጽኦ እንደሌለው ቢያመለክትም ፤ አንዳንድ አገራት ግን መድኃኒቱ ጥቅም እንዳለው ማስተዋወቃቸውን ቀጥለዋል።

የዓለም ጤና ድርጅትም ሃይድሮክሲክሎሮከዊን ለኮቪድ-19 ህሙማን የሚፈይደው ነገር የለም በማለት በመድኃኒቱ ላይ ሲያደርግ የነበረውን ሙከራ ማቆሙን ባለፈው ሳምንት አስታውቋል።
4.8K viewsedited  08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-28 11:13:09
ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የተሰባሰቡ ወቅታዊ መረጃዎችን @tikvahethmagazine ላይ ማግኘት ትችላላችሁ ፦

- የዎላይታ ማህበረሰብ ቴሌቪዥን ከኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን ህጋዊ ፈቃድ ማግኘትቱ ተገልጿል።

- ለነባርና ለአዲስ ሠራተኞች የሙያ ማረጋገጫ ምዘና የሚወስዱበት ሥርዓት መዘጋጀቱ ተገልጻል።

- የቀድሞው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ቢላሉል ሀበሻ ማህበረሰብ ሙዚየምን ጎብኝተዋል።

- የቀድሞው የግንቦት ሰባት ከፍተኛ አመራር የነበሩት አንዳርጋቸው ፅጌ የኢሳት ዋና ስራ አስኪያጅ በመሆን ስራ ጀምረዋል ተብሏል።

- በቦሌ ለሚ ኢንደስትሪ መንደር እና አካባቢው በተፈፀመ የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ስርቆት ለቀናት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የኤክትሪክ ኃይል ከአመሻሽ ጀምሮ ወደስራ ይገባል ተብሏል።

- ደቡብ ሱዳን ለአፍሪካ ህብረት የሚጠበቅባትን የ9 (ዘጠኝ) ሚሊዮን ዶላር አመታዊ መዋጮ መክፈሏ ተነግሯል።

ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮችን የሚመልከቱ ጠቃሚ ናቸው የተባሉ መረጃዎችን (ምንጮቻው ተገልፆ) በ @tikvahethmagazine በኩል ተሰባስበው ማግኘት ትችላላሁ!
4.4K viewsedited  08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ