Get Mystery Box with random crypto!

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopian_orthodox — የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopian_orthodox — የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopian_orthodox
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 29.97K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡
ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot
Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-04-18 20:00:02
ከትንሳኤ በኋላ ያሉ ዕለታት
ረቡዕ
አልዓዛር
ይባላል
በዚህች ዕለት አምላካችን ትንሣኤ እና ሕይወት መሆኑን በተግባር በታላቅ ተአምራቱ ማሳየቱን የምናስብበት በመሆኑ ስያሜው አልዓዛር ተብሏል፡፡
የአራት ቀን ሬሳን ሕይወት ይዘራበት ዘንድ የፍቅር አምላካችን በሞት በሚፈልጉት በጠላቶቹ ሰፈር ተመላለሰ ፤ የደቀ መዛሙርቱን ክልከላ አልሰማም ፤ የመንገዱ ርቀት አላዘለውም ግን በፍቅር ስለ ፍቅር ሰው ሁሉ ተስፋ የቆረጠበትን ወዳጁ አልዓዛርን ከሞት ሊያስነሳ ወደ ቢታኒያ በፍቅር ተጓዘ ፤ እውነት ነው ሞት ለታወጀብን ለእኛ ለመመላለሱ ምሳሌ ነው ፤ ሞት ድል ያላደረገው የትንሣኤውን ጌታ አምላካችንን በእውነት እንደተነሳ እንድናስብ ቤተክርስቲያን በዚህ ዕለት በአልዓዛር አንጻር ትንሣኤ እና ሕይወት እርሱ እንደሆነ ታስተምረናለች፡፡

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
1.1K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 17:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 22:19:53 "እዩና እመኑ ሰዎች......ኢየሱስ ተነስቷል"

በሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
888 viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 22:19:30
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
901 viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 22:19:30 ከትንሳኤ በኋላ ያሉ ዕለታት
ማክሰኞ
ቶማስ
ይባላል
እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ሲፈጥረው የሚያንቀላፋና የሚነቃ አድርጎ ፈጥሮታል፡፡
ማንቀላፋቱ የሞት ፤ መንቃቱ ደግሞ የትንሣኤ ምሳሌ መሆኑን ስናስብ ሁሌም ይደንቃል፡፡ አባቶቻችን የትንሣኤውን ምሥጢር በአበው እና በስነፍጥረትም ይመስሉታል፤ አቤል ከሞተ በኋላ በደሙ መናገሩ እና የሔኖክ ሳይሞት በእግዚአብሔር መሰወሩ የትንሣኤ ምሣሌ ናቸው፡፡ በተፈጥሮ ፀሐይ መውጣቷ የመወለዱ ፤ መጥለቋ የሞቱ እና ዳግመኛ መውጣቷ የትንሣኤው ምሣሌ ነው፡፡
አምላካችን ክብር ይግባውና በእርሱ ያመንን ሁላችን እንደምንነሳ የእርሱ ከሙታን መካከል በሥልጣኑ መነሳት ለሁላችን መነሳት በኩር መሆንና ማረጋገጫም እንደሆነ በቃሉም በተግባሩም ያስተማረን የትንሣኤ ጌታ ነው፡፡
በቃሉ "በመቃብር ያሉት ሁሉ ድምጹን የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣል ፤ መልካም
ያደረጉ ለሕይወት ትንሣኤ ፤ ክፉም ያደረጉ ለፍርድ ትንሣኤ ይወጣሉና በዚህ አታድንቁ " (ዮሐ፭፡፳፱) እንዲሁም በተግባር የአራት ቀን ሬሳ አልዓዛርን አስነስቷል፡፡(ዮሐ፲፩፡፵፫)
የትንሣኤው ምሥጢር ሁላችን አምላክ የሆንበት ፤ በሁሉ ላይ ሥልጣን ያገኘንበት ፤ነጻ ወጥተን ነጻ አውጪ የሆንበት ፤ ከማይጠፋ ዘር እንደተወለድን ያረጋገጥንበት ፤ ሞትን የተዘባበትንበት ፤ ጨለማን የረታንበት ከዓለም እና ከዲያብሎስ እስራት ነጻ የወጣንበት ልዩ ክብር ኃይል እና ጸጋን ያገኘንበት ምሥጢር ነው፡፡

ይህቺ ዕለትም ይህንኑ ምሥጢር ነው የምትገልጥልን ሐዋርያው #ቶማስ ተብሎ ለምን ተሰየመ የሚለውን ከማየታችን በፊት ማነው የሚለውን ማየት ነገርን ከስሩ እንድንረዳው ይረዳናልና እውነት ሐዋርያው ቶማስ ማነው?
ሐዋርያው ቶማስ
ሐዋርያው ቶማስ የስሙ ትርጓሜ ፀሐይ ማለት ሲሆን የቀድሞ ስሙ ዲዲሞስ ይባላል ትርጉሙም ጨለማ ማለት ነው፡፡ ቁጥሩ ከ፲፪ ሐዋርያት ነው፡፡ (ማቴ፲፡፫)
(መዝገበ ታሪክ ክፍል ሁለት ገጽ፹፱) ፤ ሐዋርያ ማለት ደጅ አዝማች ፤ ቀላጤ ፤ ምጥው ፤ ፍንው ፤ ሂያጅ ማለት ነው፡፡(ወንጌል ቅዱስ ገጽ፻፶፱)
ሐዋርያው ቶማስ አልዓዛር በሞተ ጊዜ ጌታችን ወደ ኢየሩሳሌም አቅራቢያ ወደነበረው መቃብሩ ለመሄድ በተነሳ ጊዜ አይሁድ ሊገሉት ስለሚፈልጉ ሌሎቹ ሐዋርያት ክርስቶስ እንዳይሄድ ቢፈልጉም ቶማሰ ሌሎቹን ሐዋርያት በድፍረት እኛም ከእርሱ ጋር እንሞት ዘንድ አብረን እንሂድ ያለ የእምነት ሐዋርያ ነው፡፡ (ዮሐ፲፩፲፮)
ሐዋርያው ቶማስ ጌታችንን በእውነት እስከ ሞት ድረስ ያመነው ከሙታን ተለይቶ ከተነሳ በኋላ በ8ኛው ቀን እሁድ ሲሆን ሐዋርያት የነገሩትን ካላየው አላምንም ብሎ የተወጋ ጎኑን ከዳሰሰ በኋላ ነው፡፡ የእምነት ምስክርነቱም ጌታዬ አምላኬም ብሎ የገለጠው፡፡(ዮሐ፳፡፳፬)
ሐዋርያው ቶማስ መንፈስ ቅዱስን ከሐዋርያት ጋር ከተቀበለ በኋላ በ፵፮ ዓ.ም ገደማ በፋርስና በሕንድ እንዳስተማረ የተለያዩ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ይገልጣሉ፡፡ ከእነዚህም መካከል ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ ፤ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ፤ ቅዱስ አምብሮስ ተጠቃሾች ናቸው፡፡በመጨረሻም ብዙ ተአምራት እና ድንቅን አድርጓል፡፡ የሐዋርያው ቶማስ ተአምር እና አገልግሎት ብዙ ተአምራትን ቢያደርግም ለአሁኑ አንዱን ብቻ እናያለን፡፡ የኸውም የሉክዮስ አገልጋይ ሆኖ በሕንጻ ማነጽ እና በሐውልት መስራት ተቀጥሮ በሚሰራበት ወቅት የሉክዮስን ሚስት ከእነ ልጆቿ እና አገልጋዮቿ አሳምኖ ያጠመቀ ሐዋርያ ነው፡፡
ሐዋርያው ቶማስ ለሕንጻ እና ለሐውልት ማሰሪያ ከሉክዮስ የተቀበለውን ገንዘብና ወርቅ ሁሉ ለነዳያን በመመጽወቱ ንጉሡ እጅና እግሩን አሥሮ ቆዳውን አስገፍፎ ስልቻ አሰፍቶ በአሸዋ ሞልቶ አሸክሞት ገበያ ለገበያ ሲያዞረው የሉክዮስ ሚስቱ አርሶንዋ ተመልክታ በድንጋጤ ሞታለች፡፡ ንጉሡም ለሚስቴ መሞት ምክንያት አንተ ነህ ካዳንካት እኔም በአምላክህ አምናለው ሲለው ጌታችን ቁስሉን እንደ ውኃ አቀዝቅዞለት ካለችበት ሄዶ ስልቻውን ቢያስነካት ተነስታለች በዚህም ሉክያኖስ አምኖ ተጠምቋል፡፡
ሐዋርያው ቶማስ በራሱ ቆዳ በተሰራ ስልቻ እየተዘዋወረ ሙት አስነስቷል ፤ ድውያንን ፈውሷል አሕዛብን አሳምኖ አጥምቋል ፤ በቀንጦፍያ አንድ ሽማግሌ ሰባት ልጆቹን ገድለውበት ሰባቱንም ከሞት አስነስቷል ፤ በኢናስም በቃሉ ትምህርት እና በእጁ ተአምራቱ ብዙዎችን አሳምኖ አጥምቋል፡፡
የሐዋርያው ቶማስ ሰማእትነት
በሕንድ የነበሩት የብራሕማን እምነት ተከታዮች የቶማስ ትምህርት የእነርሱን እምነት የሚጻረር እና የሚያጠፋ መሆኑን ተገንዝበው ተነሱበትና በብዙ ስቃይ አሠቃይተው በ፸፪ዓ.ም በሰማዕትነት አርፏል፡፡ በሶርያ ትውፊት መሠረት የሐዋርያው የቶማስ አጽም በአንድ የሶርያ ነጋዴ ተወስዶ በኤዴሳ በክብር አርፏል፡፡ (የእግዚአብሔር መንግሥት ታሪክ በምድር ላይ አንደኛ መጽሐፍ ገጽ ፺፪)
ሐዋርያው ቶማስ ለምን ሰምቶ አላመነም?
እንደ ወንጌል ትርጓሜ ሐዋርያው ቶማስ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዝግ ቤት ገብቶ ሰላም ለእናንተ ይሁን ባለ ጊዜ አልነበረም ፤ በነገሩት ጊዜም አላመነም ያለማመኑ ምክንያት ሰዱቃዊ ስለነበር እና ሐዋርያቱ አይተው እርሱ ሰማው ብሎ ከሚያስተምር ማየት ወዶ ነው፡፡

"ጌታዬ አምላኬም" (ዮሐ፳:፳፰)

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
909 viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 08:03:18
"ሞታችንን ሻረ"

በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን




@Ethiopian_Orthodox
845 viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 05:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 08:03:18
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
843 viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 05:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 08:03:18 ከትንሣኤ በኋላ ያሉ ዕለታት
ሰኞ
ሰኑይ ማእዶት
ይባላል
እንደ ቤተክርስቲያን ይትባሕል ከትንሣኤ እስከ ዳግማዊ ትንሣኤ ያለውን ሳምንት እንደ አንድ እሁድ እናከብራለን። ለዚህም ነው ዕለታቱን እንደ ሰንበት እናከብራቸው ዘንድ በፍትሐ ነገሥት ላይ አባቶቻችን ትእዛዝ የቀረጹልን።
ማእዶት ማለት መሻገር ማለት ነው። አደወ ማለት ተሻገረ ማለት ሲሆን ማእዶት መሸጋገሪያ ማለት ሊሆን ነው።
ማእዶት የትንሣኤ እሑድ ማግስት ጌታ ክርስቶስ በትንሣኤው ምዕመናንን ከሞት ወደ ሕይወት ያሻገረበት ቀን የትንሣኤው ማሳሰቢያ ነው። (ከሣቴ ብርሃን ተሰማ የአማርኛ መዝገበ ቃላት ገጽ ፻፶)
መሻገር በዕብራይስጥ ፓሳሕ ከሚባለው ቃል ይመሳሰላል ትርጉሙም ፋሲካ መሻገር ማለፍ የሚል ትርጉም ይሰጣል። ሁላችን እንደምናውቀው እስራኤላውያን ከሚያክብሯቸው አበይት በዓላት አንዱም ፋሲካ ነው። ምክንያታቸው ደግሞ እግዚአብሔር ከሞተ በኩር ያሳለፋቸውን ዕለት ያስቡበታል።
ቤተክርስቲያናችንም ይህንን በዓለ ትንሣኤን የፋሲካ በዓል የማክበሯ ምሥጢር ወይም የትንሣኤው ምሥጢር ነፍሳት በአምላካችን ትንሣኤ ከሞት ወደ ሕይወት ፣ ከአሳር ወደ ክብር ፣ ከሲዖል ወደ ገነት መሻገራቸውን በማሰብ አማናዊው ፋሲካ ወይም አሸጋጋሪው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ብላ ታምናለች። እናምናለን።
ቅዱስ ጳውሎስ በብሉይ ኪዳን በታረደው የፋሲካ በግ (ዘዳ፲፮:፮) ምትክ አማናዊው ክርስቶስ እንደታረደልን እና ሞት ላያገኘን በሕይወት ለሕይወት እንዳሸጋገረን ሲገልጥ እንዲህ ብሏል:-"" እንግዲህ ያለ እርሾ እንዳላችሁ
አዲሱን ሊጥ ትሆኑ ዘንድ አሮጌውን እርሾ አስወግዱ። ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአልና፤" (፩ ቆሮ ፭:፯)
ቅዱስ ጳውሎስ ስለ እርሾም ሆነ ስለ አዲሱ ሊጥ በምሳሌ የሚነግረን እስራኤላውያን የእግዚአብሔርን ፋሲካ ሲያከብሩ ያደርጉት የነበረ ስርዓትን ነው።
ይኸውም ፋሲካን ያከበሩት ገና ከነጻነት በፊት ነው። ምክንያቱ ደግሞ ከላይ እንዳየነው ከሞተ በኩር መቅሰፍት ለመዳን እና ከእግዚአብሔር ፍርድ ለመዳን ነበር።
በአዲስ ኪዳንም ያለን ክርስቲያኖች በተለይ ይህንን ዕለት ወይም ማእዶትን ስናስብ አምላካችን ከሞት ወደ ሕይወት እንዳሻገረን ፣ ከአሳር ወደ ክብር እንዳሳለፈን ፣ ከድካም ወደ ኃይል እንዳሻገረን ፣ ሁላችን ወደ መንግሥተ
ሰማያት ፋሲካችን በሆነው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደተሸጋገርን በማመን ሊሆን ይገባል።
የፋሲካው ጌታ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሞት ላይ እንድንዘባበትበት ሞትን ፣ ፍርሃትን ፣ ጭንቀትን ፣ ተስፋ መቁረጥን ፣ ሐዘንን ፣ ለቅሶን ፣ ትካዜን ፣ ድካምን ፣ ሥጋትን እና መቃብርን ሁሉ አጥፍቶ አሻግሮናል። ክብር ማዕዶታችን
ለሆነ ለእርሱ ይሁን። አሜን ክብር ይግባውና አምላካችን የሰው ልጅ ሞትን እንዲሻገር ሁለት ነገሮች(እምነት እና ምግባር ) እንደሚያስፈልጉት በመዋለ ስብከቱ እንዲህ ሲል አስተምሮናል:-
"እውነት እውነት እላችኋለሁ ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።
እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ሙታን የእግዚአብሔርን ልጅ ድምፅ የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣል እርሱም አሁን ነው፤ የሚሰሙትም በሕይወት ይኖራሉ።" (ዮሐ፭:፳፬-፳፭)
ሊቁ ቅዱስ ያሬድም ዕለቷ ፋሲካ እንደሆነችና እንደሰትባት ዘንድ የተገባች እንደሆነች እንዲህ ሲል በመዝሙሩ አዚሞታል:- " ፋሲካ ዛቲ ዕለት ቅድስት ይእቲ (ይህቺ የፋሲካ ዕለት ልዩ ናት) ፣ ዛቲ ዕለት ንትፈሳሕ በቲ (በዚህ ዕለት ሐሴት እናድርግባት)..."

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
782 viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 05:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 15:49:41 ሂዱ ንገሩ አውሩ ለዓለም:
ተነስቷል በዚህ የለም(2):
መድኃኔዓለም
ሞት የማይችለው የበረታ:
ኃያል ነው ማይረታ ማኅተሙን የፈታ:
የትንሳኤው ጌታ።
*አዝ*
ገዳዩ ሞት በእርሱ ድል መንሳት ተዋጠና:
ሰንሰለቴን ቀንበሬን ተካው በበገና:
ሞት ሆይ መውጊያህ የታል እያልን ምንዘምረው:
መስቀልህ ጦር ስምህ ጋሻችን ሆኖልን ነው :
ዳንን የምንልው።
*አዝ*
ተሻግረናል ስላሻገርከን ለዘለዓለም:
በመቃብር ሞት ይይዝህ ዘንድ ከቶ አልቻለም:
ኃይለኛውን በኃይል አስረኸው ላይፈታ:
ዘመርንልህ አሸናፊ ነህ የእኛ ጌታ:
ከፍ በል በእልልታ።
*አዝ*
ሞቶ ማዳን ለማን ተችሏል ካንተ በቀር:
ጌትነትህ ሥራህ ይኖራል ሲመሰከር:
ወዳጄ ሆይ ውበትህ ውብ ነው የሚያበራ:
ተጨነቀ ተንቀጠቀጠ ጠላት ፈራ:
ዕፁብ ያንተ ሥራ።
*አዝ*
መስክሩለት የምስራች ነው ታላቅ ዜና:
መላዕክቱ ነጭ ለብሰዋል ድል ነውና:
ከተማዋ አንዳች ሆናለች በለሊቱ:
በዝማሬ ተንቀጠቀጠ ወኅኒ ቤቱ:
ከበሮውን ምቱ።

በዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
1.9K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 12:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 15:49:41 "ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን!"

ይህ ሰላምታ ለሃምሳ ቀናት ይዘልቃል። የዚህ ሰላምታ ልውውጥ ታሪክ የሚጀምረው ከመጀመሪያዋ ምዕተ ዓመት ከነበረችው ከጥንት ክርስቲያኖች ጀምሮ ሲሆን ለትንሳኤ በዓል ብቻ ሳይሆን ሁሌም ሲገናኙ አይሁዳውያን "ሻሎም" ወይም ሰላም ብለው ሰላምታ እንደሚለዋወጡት ሁሉ ክርስቲያኖቹም "ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ክርስቶስ ከሙታን ተነስቷል" ብለው ሰላምታ ሲሰጡ መላሹ ደግሞ "በአማን ተንስአ እሙታን ፤በእውነት ከሙታን ተለይቶ ተነስቷል" በማለት ይመልሳል።

ይህ ሰላምታ በሁሉም በምስራቁም በምዕራቡም ኦርቶዶክሳውያን ብሎም በአንግሊካንም ቤተክርስቲያን ከትንሳኤው ጋር የፋሲካ ሰሞን ሰላምታ እንደሆነ ቆይቷል። አሁንም የሚተገበር ሰላምታ ነው። ነገር ግን መቼ እንደሆነ ባይታወቅም ሰላምታው ከዘወትር ሰላምታ ወደ ዘመነ ፋሲካ ብቻ ሰላምታ ተለወጠ።

በምዕራቦቹ ክርስቲያኖች ሰላምታ ሰጪው Christ is Risen!" ክርስቶስ ተንስአ እሙታን ወይም "The Lord is Risen!" እግዚእ ተንስአ እሙታን ሲል ሰላምታ መላሹም "Truly, He is Risen," በአማን ተንስአ፤በእውነት ተነስቷል "Indeed, He is Risen," ወይም በእርግጥ ተነስቷል "He is Risen Indeed እርግጥ ነው ከሙታን ተነስቷል ይላል።
Christ is Risen!" or "The Lord is Risen!", and the response is "Truly, He is Risen," "Indeed, He is Risen," or "He is Risen Indeed.

ይህ ሰላምታ ከሌሎቹ አብያተ ክርስቲያናት የእኛ ቤተክርስቲያን የሚለየው ረዘም ብሎ "ክርስቶስ ተንስአ እሙታን፤ በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤ አሰሮ ለሰይጣን፤ ዓግአዞ ለአዳም፤ ሰላም፤ እምይእዜሰ፤ ኮነ ፍሰሀ ወሰላም በማለት በጥልቅ ሚስጢር ሰላምታ ላይ ይውላል።

በዚህም የሀገርኛ ነገረ ክርስቶስ ትምህርት (Ethiopic Christology)እድገትን አንድ ማሳያም አድርገን መውሰድ እንችላለን። የጌታ ሞትና ትንሳኤ በቤተክርስቲያን ታሪክም ይሁን በነገረ መለኮት አስተምህሮ እድገት(Development of theological teachings) ትልቁን ስፍራ ይይዛል። በስልታዊ ነገረ መለኮት (Systematic Theology) ትምህርት ውስጥ "ዶግማ አይቀየርም ነገር ግን ያድጋል" የሚባለው ለዚህ ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ቅዱስ አትናቴዎስ የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ በ367 ዓ.ም በዛሬዋ የትንሣኤን በዓል ምክንያት በማድረግ ባስተላለፈው ቃለ ምዕዳን (ልፋፈ ጽድቅ) በ45ኛ ደብዳቤው የኦርቶዶስክ ቤተክርስቲያን በቀኖና የምትቀበላቸውን በዝርዝር 27 የሐዲስ ኪዳን መጻህፍትን መሆኑን ያወጀበት ቀን ነው። ከዚያም ወደ ሁሉም መንበረ ፕትርክናዎች (Patriarchate) ልኳል።

Priest : Christ is risen from the dead!
ካህን : ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን!
People : By the highest power and authority!
ሕዝብ : በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን!
Priest : He chained Satan!
ካህን : አሰሮ ለሰይጣን!
People : Freed Adam!
ሕዝብ : አግዐዞ ለአዳም!
Priest : Peace!
ካህን : ሰላም!
People : Henceforth!
ሕዝብ : እምይእዜሰ!
Priest : Is!
ካህን : ኮነ!
People : Joy and Peace!
ሕዝብ : ፍስሐ ወሰላም

መልካም በዓል!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
1.7K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, edited  12:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 12:32:36 "ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ"

በሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ

እንኳን አደረሳችሁ!

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
1.9K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 09:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ