Get Mystery Box with random crypto!

የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopian_orthodox — የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopian_orthodox — የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopian_orthodox
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 30.02K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡
ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot
Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-04-28 22:29:42
"ጉድለት የሌለብሽ ምስጋናን የተሞላሽ እመቤቴ ማርያም ሆይ በክብር በጸጋ ከመንፈሳውያን ከመላእክት ነገድ፣ ሥጋን ከለበሰ ከሰው ሁሉ አንቺ ትበልጫለሽ። በማኅበር መካከል የተመሰገንሽ ነሽ። በተሰበሰቡት ፊት ትወደሻለሽ። ክብርሽን የሚመስላት ሌላ ክብር የለም። ሥርዓቷ ሌላ ነው፤ ሕጓም የተለየ ነው። እመቤቴ ሆይ የሰላም ምንጭ መገኛዋ፣ የትንቢት ልምላሜ መውረጃዋም አንቺ ነሽ። ለርኅራኄ ውኃ መገኛ የይቅርታ ምንጪ ጉድጓድም አንቺ ነሽ። ፍቅርሽን እየተከተልሁ አልለቃትም። መከራ፣ የጥፋት ዘመንም ሲመጣ የበደልን፣ የኃጢአትን ሰንሰለት ከእኔ አስወግጂ። ጸሎቴም በፍቅርሽ ገመድ ተነጥቃ በፊትሽ ትድረስ። ዘወትርም በፊትሽ ትገለጥ፡ ለዘለዓለሙ አሜን።"
      -እንዚራ ስብሐት ዘቅዳሜ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
2.8K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, edited  19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 21:55:54
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
1.8K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 18:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 21:55:54 ከትንሣኤ በኋላ ያሉ ዕለታት
እሁድ
ዳግማይ ትንሣኤ

ዳግማይ ትንሣኤ ማለት ጌታችን በተደጋጋሚ ለሐዋርያቱ እና ለተለያዩ ሰዎች በተለያየ ሥፍራ መገለጡን የምናስብበት ሳምንት ነው፡፡
ቤተክርስቲያን ከትንሣኤው እስከ ዳግማይ ትንሣኤው ያለውን ሳምንት እንደ አንድ ቀን ነው የምታየው ክብር ይግባውና የትንሣኤው ጌታ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከትንሣኤው ዕለት ጀምሮ ከመግደላዊት በመጀመር ለልዩ ልዩ ሰዎች ተገልጧል፡፡
፩. ለመግደላዊት ማርያም ተገልጧል፡፡(ዮሐ፳፡፲፩)
፪. ለሴቶች ተገልጧል፡፡(ማቴ፳፰፡፱)
፫. ለሐዋርያው ጴጥሮስ ተገልጧል፡፡(ሉቃ፳፬፡፴፬)
፬. ለኤማውስ መንገደኞች ተገልጧል፡፡(ሉቃ፳፬፡፲፫)
፭. ከሐዋርያው ቶማስ በቀር ለሐዋርያት ተገልጧል፡፡(ዮሐ፳፡፲፱)
፮. ሐዋርያው ቶማስ ባለበት ለደቀ መዛሙርቱ በዝግ ቤት ተገልጧል፡፡(ዮሐ፳፡ ፳፮)
፯. በጥብርያዶስ ለሰባቱ ሐዋርያት ( ጴጥሮስ ቶማስ ናትናኤል ሉቃስ ኒቆዲሞስ ይሁዳ ያዕቆብ ) ተገልጧል፡፡
፰. ለአምስት መቶ ሰዎች ተገልጧል፡፡(፩ቆሮ፲፭፡፮)
፱. ለሐዋርያው ያዕቆብ ተገልጧል፡፡(፩ቆሮ፲፭፡፯)
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተገለጠባቸው በእያንዳንዱ መገለጦች ውስጥ ለሐዋርያቱ ሦስት አደራዎችን ሰጥቷቸዋል፡፡ እነዚህም :-
በመጀመሪያው የትንሣኤ ዕለት የኃጢአት ስርየት የማድረግን ሥልጣን ሰጥቷቸዋል(ዮሐ፳፡፳፫)
በሁለተኛው ደግሞ የማስተማር ጸጋ ሰጥቷቸዋል(ማቴ፳፰፡፲፮-፳)
በሦስተኛው ሕጻናትን ፤ ወጣትን እና ሽማግሌዎችን የመጠበቅና የመምራት ኃላፊነት ሰጥቷቸዋል፡፡(ዮሐ፳፩፡፲፭-፲፰)
በዚህም ሐዋርያዊት ወይም የሐዋርያትን ፍኖት የተከተለች በሐዋርያት በኩል ይህንን ሁሉ ጸጋ ያገኘች ቅድስት ፣ አንዲት ፣ ኩላዊት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እናታችን ቅድስት ቤተክርስቲያን በመንፈስ ቅዱስ ሁሉንም አደራ እና መመሪያ ተግባራዊ እያደረገች ትገኛለች፡፡
ሐዋርያዊት የሆነች ቅድስት ቤተክርስቲያናችን በዚህ ዕለት ልክ ደቀ መዛሙርቱ ከጌታ ጋር በነበሩበት ዘመን ይሰማቸው የነበረውን ደስታ በማሰብ ሥርዓተ አምልኮቷን ትፈጽማለች፡፡
በግጻዌው መሰረት በሁሉም አብያተ ክርስቲያናትም ሆነ ገዳማት የሚዘመረው
መዝሙር "ይትፌሳህ ሰማይ ወትትሐሰይ ምድር" ትርጉም "ሰማይ ይደሰታል ምድርም ሐሴት ታደርጋለች" የሚለው ሲሆን ምስባኩ ደግሞ "ይትነሣእ እግዚአብሔር ወይዘረው ጸሩ ወይጎይዩ ጸላእቱ እምቅድመ ገጽ ከመ የሀልቅ ጢስ ከማሁ የሀልቁ" ትርጉም እግዚአብሔር ይነሳ ጠላቶቹ ይበተኑ የሚጠሉትም ከፊቱ ይሽሹ ጢስ እንደሚበን እንዲሁ ይብነኑ" (መዝ፷፯(፷፰)፩-፪)
ቅዳሴው የዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ሲሆን ወንጌሉ የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ሃያ ከቁጥር አሥራ ዘጠኝ እስከ ፍጻሜ ነው፡፡ በዚህ ወንጌል ላይ ጌታን ባዩ ጊዜ ደስ ያላቸውን ሐዋርያት እናገኛለን፡፡ "ጌታን ባዩ ጊዜ ደስ አላቸው፡፡" (ዮሐ፳፡፳)
ያም ቀን ዕለተ እሑድ ማታ ላይ ነበር፤ የጨለማው መጨለም ፤ የአይሁድ ዛቻና ማስፈራራት ሐዋርያትን እጅጉን አስጨንቋቸዋል ከአሁን አሁን ገደሉን ፤ በቃ ጠፋን፤ይህን እና ይህን ብቻ እያሰቡ በራቸውን እንዳይከፍቱት በጠንካራ ቁልፍ ቆልፈው የጭንቀታቸው መጠን እየጨመረ እየጨመረ... ባለበት በዚህ ጊዜ ምንም እንኳን ከመከራው እና ከጭንቀቱ ብዛት በሩን ዘግተው ሞታቸውን ቢጠባበቁም በሞት ላይ ስልጣን ያለው ተስፋን መቀጠል የሚችል አምላክ "ሰላም ለእናንተ ይሁን" ብሎ መካከላቸው ሲቆም ከመቅጽበት ጌታን ባዩ ጊዜ በሐዘን የጨፈገገው ፊታቸው በደስታ በራ፡፡ ክብር ለአምላካችን ይሁን፡፡ የእኛንም የተዘጋ ቤታችንን ከፍቶ ገብቶ በሐዘን እና በጭንቀት የጨፈገገው ፊታችንን በደስታ አብርቶ ሰላማችንን ይመልስልን፡፡ አሜን!
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
2.0K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 18:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 06:33:42
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
2.3K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 03:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 06:33:42 ከትንሣኤ በኋላ ያሉ ዕለታት
ቅዳሜ
ቅዱሳት አንስት
ይባላል
በወንጌል ተጽፎ እንደምናነበው ፍቅሩን
በማሰብ ጨለማውን ሳይፈሩ ወደ መቃብር ስለመጡት መቅደላዊት ማርያም እና ማርያም ባውፍልያ በስፋት ቤተክርስቲያን እንድናስብ ስለምታስተምረን ቅዱሳት አንስት ተብሏል።
ወንጌሉ ስለዚህ ዕለት እንዲህ ብሎ ይገልጻል :- "ከሳምንቱም በፊተኛው ቀን መግደላዊት ማርያም ገና ጨለማ ሳለ ማለዳ ወደ መቃብር መጣች ድንጋዩም ከመቃብሩ ተፈንቅሎ አየች።
እየሮጠችም ወደ ስምዖን ጴጥሮስና ኢየሱስ ይወደው ወደ ነበረው ወደ ሌላው ደቀ መዝሙር መጥታ፦ ጌታን ከመቃብር ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አናውቅም አለቻቸው።
ስለዚህ ጴጥሮስና ሌላው ደቀ መዝሙር ወጥተው ወደ መቃብሩ ሄዱ። ሁለቱም አብረው ሮጡ፤ ሌላው ደቀ መዝሙርም ከጴጥሮስ ይልቅ ፈጥኖ ወደ ፊት ሮጠና አስቀድሞ ከመቃብሩ ደረሰ፤ ዝቅም ብሎ ቢመለከት የተልባ እግሩን ልብስ ተቀምጦ አየ፥ ነገር ግን አልገባም። ስምዖን ጴጥሮስም ተከትሎት መጣ ወደ መቃብሩም ገባ፤ የተልባ እግሩን ልብስ ተቀምጦ አየ፥ ደግሞም በራሱ የነበረውን ጨርቅ ለብቻው በአንድ ስፍራ ተጠምጥሞ እንደ ነበረ እንጂ ከተልባ እግሩ ልብስ ጋር ተቀምጦ እንዳልነበረ አየ። በዚያን ጊዜ አስቀድሞ ወደ መቃብር የመጣውም ሌላው ደቀ መዝሙር ደግሞ ገባ፥ አየም፥ አመነም፤ ከሙታን ይነሣ ዘንድ እንዲገባው የሚለውን የመጽሐፉን ቃል ገና አላወቁም ነበርና። ደቀ መዛሙርቱም ወደ ቤታቸው ደግሞ ሄዱ።
ማርያም ግን እያለቀሰች ከመቃብሩ በስተ ውጭ ቆማ ነበር። ስታለቅስም ወደ መቃብር ዝቅ ብላ ተመለከተች፤ጨሁለት መላእክትም ነጭ ልብስ ለብሰው የኢየሱስ ሥጋ ተኝቶበት በነበረው አንዱ
በራስጌ ሌላውም በእግርጌ ተቀምጠው አየች።
እነርሱም፦ አንቺ ሴት፥ ስለ ምን ታለቅሻለሽ? አሉአት። እርስዋም፦ ጌታዬን ወስደውታል ወዴትም እንዳኖሩት አላውቅም አለቻቸው።
ይህንም ብላ ወደ ኋላ ዘወር ስትል ኢየሱስን ቆሞ አየችው፤ ኢየሱስም እንደ ሆነ አላወቀችም።
ኢየሱስም፦ አንቺ ሴት፥ ስለ ምን ታለቅሻለሽ? ማንንስ ትፈልጊያለሽ? አላት።
እርስዋም የአትክልት ጠባቂ መስሎአት፦ ጌታ ሆይ፥ አንተ ወስደኸው እንደ ሆንህ ወዴት እንዳኖርኸው ንገረኝ እኔም እወስደዋለሁ አለችው።
ኢየሱስም፦ ማርያም አላት። እርስዋ ዘወር ብላ በዕብራይስጥ፦ ረቡኒ አለችው፤
ትርጓሜውም፦ መምህር ሆይ ማለት ነው።
ኢየሱስም፦ ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና አትንኪኝ፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ፦ እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ ዓርጋለሁ ብለሽ ንገሪአቸው አላት።
መግደላዊት ማርያም መጥታ ጌታን እንዳየች ይህንም እንዳላት ለደቀ መዛሙርቱ ነገረች። (ዮሐ፳:፩-፲፰)
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
2.4K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 03:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 20:51:13 " የጌታ ትንሣኤ "

ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ እና ዘማሪ ዲያቆን ሄኖክ ሞገስ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
3.3K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 20:51:13
ከትንሣኤ በኋላ ያሉ ዕለታት
አርብ
ቅድስት ቤተክርስቲያን/ነፍሳት/
ይባላል
በዚህ ዕለት ቅድስት ቤተክርስቲያን ተብሎ የተሰየመበት ምክንያት በጥቂቱ በቤተክርስቲያን ዙሪያ ሰባት ነገሮችን እንድናስብ ነው፡፡ እነዚህም፡-
፩. ቅድስት ቤተክርስቲያን በሞቱ እና በትንሣኤው መመስረቷን እናስባለን፡፡
፪. አምላካችን ራሱን አሳልፎ እንደሰጣት እናስባለን፡፡
፫. እርሱ ራሷ እርሷ ደግሞ አካሉ እንደሆነች እናስባለን፡፡
፬. ቅድስት ቤተክርስቲያን መሰረቷ የነብያት እና የሐዋርያት ቃል መሆኑን እናስባለን፡፡
፭. በደሙ ስለመታጠቧ እናስባለን።
፮. ከነገድ ከቋንቋ ሁሉ ስለመመረጧ እናስባለን፡፡
፯. ለዘላለም እንዳትናወጽ በእርሱ ላይ ስለመታነጽዋ እናስባለን፡፡ (ሥርዓተ አምልኮ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ገጽ፻፰፯)

ነፍሳት ከሲዖል የወጡበት ጌታችን በዕለተ ዓርብ በመልዕልተ መስቀል ቅዱስ ሥጋውን ቆርሶ ክቡር ደሙን አፍስሶ በአካለ ነፍስ ወደ ሲዖል ወርዶ በሲዖል ያላችሁ ውጡ በጨለማ ያላችሁ ተገለጡ ብሎ ግእዛነ ነፍስን ( የነፍስን ነፃነት ) ሰበከላቸው ሰይጣንን አሰረው ሲዖልን መዘበረው ነፍሳትን ነፃ አወጣቸው ልምላሜ ገነትን አወረሳቸው ይህ ዕለት በቀጣዩ በትንሣኤ ሳምንት ዓርብ እንዲታሰብ ነፍሳት የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል ፡፡

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
3.1K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 06:41:19 "እምይእዜሰ ይኩን ሰላም"

በዘማሪ ብሩክ መኩሪያ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
3.4K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 03:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 06:41:19
ከትንሣኤ በኋላ ያሉ ዕለታት
ሐሙስ
አዳም
ይባላል
ይህ ዕለት አዳም ሐሙስ (አዳም) የተባለበት ምክንያት አምላካችን እግዚአብሔር ለአዳም "ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" ብሎ ቃል የገባበት ዕለት በመሆኑ ይህንን ስያሜ አግኝቷል፡፡(ዘፍ፫፡ ፲፭) ፤ (መጽሐፈ ቀለሜንጦስ አንቀጽ ፰ እና መጽሐፈ አክሲማሮስ ዘዓርብ ቁ. ፲፫) ቤተክርስቲያን በዋናነት ለአዳም የተሰጠውን የተስፋ ቃል አምላካችን መፈጸሙንና የሰው ልጆች ሁሉ በትንሣኤው ከሞት ነጻ እንደወጡ በዚህ ዕለት ታስተምራለች፡፡
በዚህ ዕለት በአባታችን በአዳም በእናታችን በሔዋን አንጻር:-
፩. ከውድቀታችን ይልቅ መነሳታችንን
፪. ከባርነታችን ይልቅ ነጻነታችንን
፫. ከለቅሶአችን ይልቅ መጽናናታችንን
፬. ከሀዘናችን ይልቅ ደስታችንን
፭. ከመሰበራችን ይልቅ መጠገናችንን
፮. ከመታመማችን ይልቅ መፈወሳችንን
፯. ከድካማችን ይልቅ ኃይላችንን
፰. ከመረሳታችን ይልቅ መታወሳችንን
፱. ከጨለማችን ይልቅ ብርሃናነችንን
፲. ከፍርሃታችን ይልቅ ድፍረታችንን
፲፩. ከክህደታችን ይልቅ እምነታችንን
፲፪. ከጥላቻችን ይልቅ ፍቅራችንን
፲፫. ከመታወካችን ይልቅ ሠላማችንን
፲፬. ከሞታችን ይልቅ ሕይወታችንን
፲፭. ከመቃብራችን ይልቅ ትንሣኤአችንን የምናስብበት ዕለት ነው፡፡
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
3.5K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 03:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 20:00:28
"ብርሃን ወጣ ከመስቀሉ የሚያንጸባርቅ"

በሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ

@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
1.0K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 17:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ