ሂዱ ንገሩ አውሩ ለዓለም: ተነስቷል በዚህ የለም(2): መድኃኔዓለም ሞት የማይችለው የበረታ: ኃያል ነው ማይረታ ማኅተሙን የፈታ: የትንሳኤው ጌታ። *አዝ* ገዳዩ ሞት በእርሱ ድል መንሳት ተዋጠና: ሰንሰለቴን ቀንበሬን ተካው በበገና: ሞት ሆይ መውጊያህ የታል እያልን ምንዘምረው: መስቀልህ ጦር ስምህ ጋሻችን ሆኖልን ነው : ዳንን የምንልው። *አዝ* ተሻግረናል ስላሻገርከን ለዘለዓለም: በመቃብር ሞት ይይዝህ ዘንድ ከቶ አልቻለም: ኃይለኛውን በኃይል አስረኸው ላይፈታ: ዘመርንልህ አሸናፊ ነህ የእኛ ጌታ: ከፍ በል በእልልታ። *አዝ* ሞቶ ማዳን ለማን ተችሏል ካንተ በቀር: ጌትነትህ ሥራህ ይኖራል ሲመሰከር: ወዳጄ ሆይ ውበትህ ውብ ነው የሚያበራ: ተጨነቀ ተንቀጠቀጠ ጠላት ፈራ: ዕፁብ ያንተ ሥራ። *አዝ* መስክሩለት የምስራች ነው ታላቅ ዜና: መላዕክቱ ነጭ ለብሰዋል ድል ነውና: ከተማዋ አንዳች ሆናለች በለሊቱ: በዝማሬ ተንቀጠቀጠ ወኅኒ ቤቱ: ከበሮውን ምቱ። በዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox 1.9K viewsℍ𝖆𝕭𝖎𝖗, 12:49