Get Mystery Box with random crypto!

Muslim ሙስሊም

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiomuslim_1 — Muslim ሙስሊም M
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiomuslim_1 — Muslim ሙስሊም
የሰርጥ አድራሻ: @ethiomuslim_1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 851

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-03-22 19:06:31 #የሰላምታ_ትሩፋትና #ሰላምታን_ማብዛት_ስለመታዘዙ
#ክፍል_4

አላህ እንዲህ ብሏል፦
“ቤቶችንም በገባችሁ ጊዜ፥ ከአላህ ዘንድ የሆነችን የተባረከች መልካም ሰላምታ በነፍሶቻችሁ ላይ ሰላም በሉ።” (አን ኑር፡ 61)

#ሐዲሥ 131 / 848

አቡ ሁረይራ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ “እስካላመናችሁ ድረስ ጀነት አትገቡም። እስካልተዋደዳችሁ ድረስ አታምኑም። ስትሠሩት የምትዋደዱበትን ነገር ላመላክታችሁን? በመካከላችሁ ሰላምታ አብዙ።” (ሙስሊም)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ ጀነት የሚገኘው በእምነት ነው። እምነት ደግሞ ፍቅርን ይሻል። ፍቅርን ከሚያመጡ ነገሮች መካከል ሰላምታን ማብዛት ይገኝበታል።
2/ የሰላምታን ደረጃና ትሩፋት ያሳያል።
3/ ኢስላማዊ ወንድማማችነትና ፍቅር የእምነት መሠረታዊ አካል እንደሆነ ሐዲሡ ያሳያል።
4/ የሐዲሡ መልዕክት “እርስ በርስ ተዋደዱ” ነው። ካልተዋደዳችሁ ጀነትን አታገኙም። ካልተግባባችሁ፣ እርስ በርስ ከተናቆራችሁ፣ ከፊላችሁ ለከፊሉ ክፉ ካሰበ ጀነትን አታገኙም። አንዱ የሌላውን መጥፋትና መውደቅ የሚመኝ ከሆነ፣ ለወንድሙ በጎ ማሰብና መመኘት ካቆመ ጀነትን አታገኙም።
ቴሌግራም
https://t.me/ethiomuslim_1
75 viewsAm First, 16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-22 08:59:28
አላህ ሆይ! ልባችንን ክፈትልን ውዴታህን እንድናገኝ አሚን
81 viewsAm First, 05:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-21 18:32:36 የረመዷን ጨረቃ ዛሬ ባለመታየቷ ነገ ረቡዕ የሸዕባን 30ኛ ቀን ሲሆን የወርሃ ረመዷን ጾም ከነገ በኋላ ሐሙስ የሚጀመር ይሆናል።

ረመዷን ሙባረክ!
101 viewsAm First, 15:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-21 09:18:23 #የሰላምታ_ትሩፋትና #ሰላምታን_ማብዛት_ስለመታዘዙ
#ክፍል_3

አላህ እንዲህ ብሏል፦

“የተከበሩት የኢብራሂም እንግዶች ወሬ መጥቶሃልን? በርሱ ላይ በገቡና ሰላም ባሉ ጊዜ፥ (አስታውስ)፤ ሰላም፤ ያልታወቃችሁ ሕዝቦች ናችሁ፤ አላቸው።” (አዝዛሪያት፡ 24_25)

#ሐዲሥ 131 / 847

አቢ ዑማረህ አልበራእ ኢብን ዓዚብ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ “የአላህ መልዕክተኛ ሰባት ነገሮችን አዘውናል። በሽተኛን እንድንጠይቅ፣ አስክሬንን እንድንከተል፣ ላነጠሰ ሰው የአላህን እዝነት እንድንማጸን፣ ደካማን እንድንረዳ፣ የተበደለን እንድናግዝ፣ ሰላምታን እንድናበዛና የማለን ሰው መሐላ እንድናጸና።” (ቡኻሪና ሙስሊም) ይህ ከቡኻሪ ዘገባዎች አንዱ ነው።

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ የማለን ሰው መሓላ ማጽናት ማለት አንድ ሰው “እንዲህ ይሆናል” ብሎ ከማለ ያን መሐላውን ልናጸድቅለት ይገባል፤ የማለበትን ነገር በመሥራት መሓላውን እውን ልናደርግ ይገባል ማለት ነው።
2/ ከላይ የተጠቀሱት ሰባቱ የአላህ መልዕክተኛ ትእዛዞች እጅግ የሚበረታቱ ናቸው። ምክንያቱም በሙስሊሞች መካከል ያለውን ግንኙነት ያጠነክራሉና። ፍቅርንና አንድነትንም ያመጣሉ። ሰላምንና መረጋጋትን፣ እንዲሁም መግባባትን ያነግሳሉ።
ቴሌግራም
https://t.me/ethiomuslim_1
114 viewsAm First, 06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-21 09:18:18
97 viewsAm First, 06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 08:48:10 #የሰላምታ_ትሩፋትና #ሰላምታን_ማብዛት_ስለመታዘዙ  
#ክፍል_2

አላህ እንዲህ ብሏል፦
“በሰላምታ በተከበራችሁም ጊዜ ይበልጥ ባማረ (ሰላምታ) አክብሩ፤ ወይም (እርሷኑ) መልሷት፡፡” (አን ኒሳእ፡ 86)

#ሐዲሥ 131 / 846

አቡ ሁረይራ እንዳስተላለፉት ነቢዩ እንዲህ ብለዋል፦ “አላህ አደምን በፈጠረ ጊዜ ‘ለነዚያ _ለተቀመጡት መላእክት_ ሰላምታ አቅርብላቸው። ምላሻቸውንም በጥሞና ስማ። ያንተና የዝሪያዎችህ ሰላምታ ነውና’ አለው። ‘አስሰላሙ ዐለይኩም’ አላቸው። ‘አስሰላሙ ዐለይከ ወረሐመቱላሂ’ በማለት <<ወረሕመቱላህ>> የሚል አክለው መለሱለት፡፡” (ቡኻሪና ሙስሊም)

  ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ “አስሰላሙ ዐለይኩም” የሚለው ቃል ኢስላማዊ የሰላምታ አቀራረብ ስልት ነው። አላህ ይህን ቃል አደምን ከፈጠረበት ዕለት አንስቶ ለባሮቹ ሰላምታ አድርጎታል።
2/ ሰላምታ ሲመልሱ በርከት አድርጎ መመለስ በላጭ መሆኑን ሐዲሡ ያሳያል። “አስሰላሙ ዐለይኩም” ላለ “ወዐለይኩሙ ሰላም ወረሕመቱላሂ ወበረካቱሁ” በማለት ማከል በላጭ ነው።
ቴሌግራም
https://t.me/ethiomuslim_1
100 viewsAm First, 05:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 08:48:04
89 viewsAm First, 05:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 09:34:10 #የሰላምታ_ትሩፋትና #ሰላምታን_ማብዛት_ስለመታዘዙ
#ክፍል_1

አላህ እንዲህ ብሏል፦
“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! እስከምታስፈቅዱና በባለቤቶቿ ላይ ሰላምታን እስከምታቀርቡ ድረስ ከቤታችሁ ሌላ የኾኑትን ቤቶች አትግቡ።” (አን ኑር፡ 27)

#ሐዲሥ 131 / 845

ዐብደላህ ኢብኑ ዐምር ኢብኑ አል ዓስ እንዳስተላለፉት አንድ ሰው የአላህን መልዕክተኛ፦ “ከኢስላም (በጎ ሥራዎች) ሁሉ መልካሙ የትኛው ነው?” ሲል ጠየቀ። “ምግብ ማብላትህና ለምታውቀውም ለማታውቀውም ሰላምታ ማቅረብህ ነው” በማለት መለሱለት፡፡ (ቡኻሪና ሙስሊም)
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ ምግብን ማብላት ይወደዳል። ፍቅር ይጨምራል፣ ግንኙነትን ያጠነክራል። የሰየውንም ቸርነት አመላካች ነው።
2/ ሰላምታን ማብዛት ሱንና ነው። ሰላም ማለት ሱንና ሲሆን፥ መመለስ ደግሞ ግዴታ ነው። ከተሰበሰቡ ሰዎች መሐል አንዱ ከመለሰ በሌሎች ላይ ግዴታውን ያነሳላቸዋል።
3/ ሰላምታ ማቅረብ ሰላምታ ከመመለስ የበለጠ ነው።
4/ ምግብ ከማብላት ጋር መወሳቱ ፍቅርን እንደሚያክልና ግንኙነቶችን እንደሚያጠናክር ለማሳየት ነው።
5/ “ደህና አደርክ”፣ “ደህና ነህ” የሚሉና መሰል የሰላምታ ቃላት “አስሰላሙ ዐለይኩም” የሚለውን ቃል አይተኩም።
ቴሌግራም
https://t.me/ethiomuslim_1
111 viewsAm First, 06:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-19 09:34:09
100 viewsAm First, 06:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 18:36:22 #ሕልምና_ከርሱ #ጋር #የተያያዙ_ነገሮች     
#ክፍል_6

#ሐዲሥ 130 / 844

አቡል አስቀዕ ዋሢለት ኢብኑ አል አስቀዕ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ “ከትልልቅ ቅጥፈቶች ውስጥ አንድ ሰው አባቱ ያልሆነውን አባቴ ነው ማለቱ፣ ወይም ዓይኖቹን ያላዩትን ሕልም ማሳየቱ ወይም በአላህ መልዕክተኛ ላይ ያላሉትን ማለቱ ነው።” (ቡኻሪ)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ አባቱ ያልሆነውን አባቴ ነው በማለት ወደርሱ መጠጋት ትልቅ ጥፋት ነው። የዘር መቀላቀልን ይፈጥራል።
2/ በሕልም መዋሸት፣ ያላዩትን አየሁ ማለት ትልቅ ጥፋት ነው። ምክንያቱም በአላህ ላይ መዋሸት ነውና። በእውን መዋሸት በፍጡራን ላይ መዋሸት ነው። እርሱም ቢሆን ትልቅ ወንጀል ቢሆንም በአላህ ላይ መዋሸት ግን ይበልጥ አስከፊ ነው።
3/ በነቢዩ ላይ መዋሸትና እርሳቸው ያላሉትን እንዳሉ አድርጎ ማቅረብም ትልቅ ጥፋት ነው። ምክንያቱም ሰዎችን ወደ ማሳሳት እና ወደ ማጠመም ይመራልና። ወደ ሸሪዓው የርሱ አካል ያልሆነን ነገር ማስጠጋት ነውና።
ቴሌግራም
https://t.me/ethiomuslim_1
126 viewsAm First, 15:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ