Get Mystery Box with random crypto!

Muslim ሙስሊም

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiomuslim_1 — Muslim ሙስሊም M
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiomuslim_1 — Muslim ሙስሊም
የሰርጥ አድራሻ: @ethiomuslim_1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 851

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-03-30 17:36:13 #የሰላምታ_አሰጣጥ

#ክፍል_1

ሰላምታ የሚያቀርበው ሰው ፦ “አሰላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ” (የአላህ ሰላም፣ እዝነትና በረከት በናንተ ላይ ይስፈን) ማለቱ የተወደደ ነው። ሰላምታ የሚቀርብለት ሰው አንድ ቢሆንም እንኳ በዚህ ብዙነትን የሚገልጽ ቃል ይጠቀም። መላሾችም ከመጀመሪያው ላይ “ወ” የሚል ፊደል በመጨመር “ወዐለይኩሙ ሰላም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ” (በናንተም ላይ የአላህ ሰላም፣ እዝነትና በረከት ይስፈን) ይበሉ።

#ሐዲሥ 132 / 851

ዒምራን ኢብኑ አል ሑሰይን رضي الله عنهما እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ አንድ ሰው ወደ ነቢዩ ﷺ መጣ። “አሰላሙ ዐለይኩም” አላቸው። መለሱለትና ተቀመጠ። ነቢዩ ﷺ ፦ “አሥር” አሉት። ቀጥሎ ሌላ ሰው መጣና “አሰላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላህ” በማለት ሰላምታ አቀረበ። መለሱለትና ተቀመጠ። ነቢዩም ﷺ፦ “ሃያ” አሉ። ከዚያም ሌላ ሰው መጣና፦ “አሰላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ” አለ። መለሱለትና ተቀመጠ። “ሠላሳ” አሉ። (አቡዳውድና ቲርሚዚ)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ መልክተኛው “አሥር” “ሃያ” “ሠላሳ” ያሉት ፣ ሰዎች የሚያገኙትን ምንዳ ለመግለጽ ነው። የመጀመሪያ “አሰላሙ ዐለይኩም” ብቻ በማለቱ አሥር ምንዳ አግኝቷል። ሁለተኛው “ወራሕመቱላህ” የሚል ቃል በመጨመሩ ሀያ ምንዳ አግኝቷል። ሦሥተኛው ሁለቱን በልጦ “ወበረካቱሁ” የሚል ቃል በማከሉ ሠላሳ ምንዳ አግኝቷል።
2/ እነዚህ የሰላምታ ዓይነቶች በሐዲሦች የተጠቀሱትን ያህል ምንዳዎች እንደሚያስገኝ ከዚህ ሐዲሥ እንማራለን።

#ሐዲሥ 132 / 852

ዓኢሻ እንዳስተላለፉት፣ የአላህ መልዕክተኛ “እነሆ ጂብሪል ሰላምታ ያቀርብልሻል” አሉኝ። እኔም “በርሱም ላይ የአላህ ሰላም፣ እዝነትና በረከት ይስፈን” በማለት መለስኩ። (ቡኻሪና ሙስሊም)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ የእመት ዓኢሻ ልቅና። የመላኢካ ሰላምታ ደርሷቸዋል።
2/ እገሌ ሰላም ብሎሃል ማለት ሸሪዓዊ ነው። መመለሱም ግዴታ ነው።

ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
107 viewsAm First, 14:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 17:36:11
89 viewsAm First, 14:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 12:23:22 #የሰላምታ_ትሩፋትና #ሰላምታን_ማብዛት_ስለመታዘዙ
#ክፍል_6

#ሐዲሥ 131 / 850

ጡፈይል ኢብኑ ኡበይ ኢብኑ ከዕብ እንዳስተላለፉት፦ ከዐብደላህ ኢብኑ ዑመር ዘንድ ይመጡና ወደ ገበያ አብረው ይሔዱ ነበር። “ገበያ ስንደርስ ዐብደላህ ተራም ሆነ ጥሩ ዕቃዎችን በሚሸጡ ሰዎች፣ በድሃም ሆነ በየትኛውም ሰው አጠገብ ሲያልፉ ሰላምታ ሳይሰጡ አያልፉም። አንድ ቀን ከዐብደላህ ኢብኑ ዑመር ዘንድ መጣሁ። ወደ ገበያ አስከትለውኝ ሔዱ። “ካልተገበያየህ፣ ሸቀጥ ካልጠየቅክ፣ ካልተከራከርክ ወይም ከገበያ መቀመጫዎች ካልተቀመጥክ ገበያ ውስጥ ምን ታደርጋለህ?” አልኳቸው። “እዚህ እንቀመጥና እናውጋ” ስልም ጠየቅኳቸው። “አቡ በጥን ሆይ! በጠዋት የምንወጣው ለሰላምታ ነው። ላገኘነው ሰው ሁሉ ሰላምታ እናቀርባለን።” አሉ። (ማሊክ)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ መንገድ ላይ ኃጢአት እንደማያጋጥመው ያመነ ሰው ጎረቤቱንና ኅብረተሰቡን እየዞረ ሰላም ቢልና ቢጠይቅ ጽድቅ ሥራ ነው። ኃጢአትና መጥፎ ነገር እንደሚያጋጥመው ካወቀ ግን ከቤቱ አርፎ መቀመጡ በላጭ ነው።
2/ ላገኙት ሰው ሁሉ ሰላምታ ማቅረብ ይወደዳል።
3/ “አቡ በጥን” ማለት ሆደ_ትልቅ ማለት ሲሆን፥ ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር ባልንጀራቸውን ጡፈይልን በዚህ ቅጽል መጥራታቸውን አይተናል። ይህም አንድን ተወዳጅ ወይም ባልንጀራ የማይቀየም ከሆነና ከተቀበለው ባለበት አንዳች ነገር ቅጽል አድርጎ መጥራት የተፈቀደ መሆኑን ያሳያል። ለምሳሌ ወፍራሙ፣ ወዘተ. እንደማለት ነው።
ቴሌግራም
ቴሌግራም
https://t.me/ethiomuslim_1
45 viewsAm First, 09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-29 12:23:21
43 viewsAm First, 09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 17:17:59
86 viewsAm First, 14:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-25 20:36:00
#ፆመኛ_ሲያፈጥር #የሚል_ዱዓ
57 viewsAm First, 17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 18:04:02 #የሰላምታ_ትሩፋትና #ሰላምታን_ማብዛት_ስለመታዘዙ
#ክፍል_5
#ሐዲሥ 131 / 849

የአላህ መልዕክተኛ ተከታዩን ሲናገሩ ሰምቻለሁ በማለት አቡ ዩሱፍ ዐብደላህ ኢብኑ ሰላም አስተላልፈዋል፦ “ሰዎች ሆይ! ሰላምታን አብዙ። ምግብንም አብሉ። ዝምድናን ቀጥሉ። ሰዎች ተኝተው ሳለ እናንተ ስገዱ። ጀነትን በሰላም ትገባላችሁ።” (ቲርሚዚ)

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ የሰላምታ ትሩፋት፡፡
2/ ሰዎችን መመገብ ትልቅ ቸርነት ነው። ቁርኣን ቸርነትን ከእምነትና አላህን ከመፍራት ጋር በማስተሳሰር በብዛት አውስቶታል። በተለይም ድሆችንና የቲሞችን መመገብን የመሠረታዊ ዐቂዳ አካል አድርጎታል።
3/ ዝምድናን መቀጠል በኢስላም እጅግ የከበደ ግዴታ ነው።
4/ ሰዎች ተኝተው እያለ እንቅልፍን ትቶ ለአላህ መስገድና መዋደቅ በእርግጥም ትልቅ ደረጃ ነው።
5/ ከላይ የተዘረዘሩትን ተግባራት ማከናወንን ልምዱ ያደረገ ሰው ሽልማቱ ጀነት በሰላም መግባት ይሆናል።
ቴሌግራም
https://t.me/ethiomuslim_1
87 viewsAm First, 15:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 18:04:00
77 viewsAm First, 15:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 12:54:52 አፍጡር ላይ የሚደረግ አዝካር

ذَهَبَ الظَّمَأُ، وَابْتَلَّتِ العُرُوقُ، وَثَبَتَ الأجْرُ
إِنْ شَاءَ اللهُ

ጥማችን ተቆርጧል፡፡ የደም ሥሮቻችን ረጥበዋል፡፡ የአላህ ፈቃድ ከሆነ ምንዳም ተረጋግጦልናል፡፡

ዘሐበዝዘመኡ ወበተልለቲል ዑሩቁ፣ ወሠበተል አጅሩ ኢንሻአልላህ
85 viewsAm First, edited  09:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-22 19:06:32
74 viewsAm First, 16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ