Get Mystery Box with random crypto!

Muslim ሙስሊም

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiomuslim_1 — Muslim ሙስሊም M
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiomuslim_1 — Muslim ሙስሊም
የሰርጥ አድራሻ: @ethiomuslim_1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 851

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-04-12 02:30:08 ለይለተልቀድር ለሰጋጆችና መስጂድ ውስጥ ላለ ብቻ አይደለም

የወር አበባ ደም ላይ፣ የወሊድ ደም ላይ ያሉ፣ መንገደኞች...የዚች ለሊት ትሩፋት አይለፋችሁ። በዚክርና መሰል ዒባዳዎች ልትበራቱ ይገባል።በዚያች ለሊት ዱዓእ ማብዛትም አትዘንጉ። ለይለተልቀድር ለሰጋጆችና መስጂድ ላይ ላለ ብቻ አይደለም።

ብዙ ሰው መስጂድ ካልሄደ ይሄን ምንዳ የሚያገኙ አይመስለውም። ይህ ስህተት ነው! ዋናው ከእኛ የሚጠበቀው በኢባዳ ላይ መሆናችን ነው። ለቻለ እና አቅሙ ላለው ሰው ግን የተወዳጁን ነብይ ሙሀመድ(ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሱና(ፈለግ) ለመከተል መስጂድ ላይ ብንሆን ይመረጣል፣ ይወደዳል። ካልቻልን ባለንበት ቦታ ስራ ላይ የሆነም በስራው ላይ እቤቱ የሆነም በቤቱ በኢባዳ ልንበረታ ይገባል!

አላህ ለይለተል ቀድርን ይወፍቀን!
100 viewsAm First, 23:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 02:29:23 https://t.me/ahmedin99/5302
96 viewsAm First, 23:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 01:06:49 የረመዷን ወርቃማ 10 ቀናቶች

T.me/ahmedin99

የወራቶች ሁሉ አለቃ የሆነው ረመዷን የመጨረሻ አስር ቀናቶቹ ደግሞ የወሩ ቀናቶች ቁንጮ ናቸው፡፡በነዚህ ቀናቶች ውስጥ የምትገኘዋ ለይለቱልቀድር ደግሞ የቁንጮዎች ቁንጮ ናት፡፡

አስሩን ቀኖች (ሌሊቶች) በሙሉ ለይለተል-ቀድርን በማሰብ በዒባዳ ያሳለፈ ያለምንም ጥርጥር ለይለተል-ቀድርን ያገኛል።

ቡኻሪይና ሙስሊም ከእናታችን ዓኢሻ
እንደዘገቡት ነቢዩ  ﷺ"የረመዷን 10 ቀኖች ሲገቡ መቀነታቸውን ያጠብቁ ነበር፣ ለሊቱንም በሙሉ በዒባዳ (በሰላት) ያሳልፉ ነበር፣ ባለቤቶቻቸውንም (ለዒባዳ) ይቀሰቅሱ ነበር" ብለዋል፡፡

ጅምርና መነሻ ላይ ሁሉም እኩል ሊሆን ይችላል፡፡ ነገሮች የሚለኩት ግን በፍጻሜያቸው ነው፡፡ እስከመጨረሻው ታግሶ ስራውን አሳምሮ ያጠናቀቀ ይሸለማል፡፡ መጨረሻ ላይ የተሳነፈና ያበላሸ ግን ሽልማቱን በማጣት ወይም ከዛም በከፋ ነገር ሊቀጣ ይችላል፡፡

የረመዷን የመጨረሻ 10 ቀናት ላይ ይበልጥ ኸይር ስራ ላይ ልንተጋና መጨረሻችን ያማረ እንዲሆን ጥረት ልናደርግ እንጂ ልንዘናጋና ልንሰላች በጭራሽ አይገባንም፡፡

ኢብኑል-ጀውዚይ እንደሚሉት"ፈረስ እንኳ የእሽቅድድም ሜዳ ላይ የመጨረሻው ዙር ላይ ሲደርስ ኀይሉን አሟጦ ተጠቅሞ ሌሎች ፈረሶችን በመቅደም ከግቡ ላይ ቀድሞ ለመድረስ ይጥራል" ፣እነሆ ከፈረስ በላይ እንጂ በታች ልንሆን ፈፅሞ አይገባምና እኛም ወደ ጀነት በሮች በመልካም ስራ ልንሽቀዳደም ይገባናል፡፡

የረመዷን የመጀመሪያ አስርቶች ላይ ከነበረን የተሻለ ንቃትና ትጋት ሊኖረን ይገባል።

ሰራተኛ ስራውን ሲያጠናቅቅ የሚያገኘውን ደመወዝ በማሰብ የስራውን ድካም ተቋቁሞ የሚጠበቅበትን ሁሉ እንደሚያደርገው ሁሉ እኛም የአላህን ውዴታና ጀነትን በማሰብ ነፍሲያችንን በማሸነፍ መልካም ስራ ላይ ልንበረታ ይገባናል፡፡ ሁኔታዎች ለመልካም ስራ የማያግዙበት ወቅትና ቦታዎች ላይ ሁሉንም ተቋቁሞ ከእኛ የሚጠበቀውን ማድረግና አላህ እንደሚፈልገው ሆኖ መገኘት ደረጃው ለዲን ብሎ ወደ ነቢዩﷺ የመሰደድ ያክል ነው፡፡

ኢዕቲካፍ በመግባት ከዓለማዊ ጉዳዮች ርቆ፣ ከዱንያ ግርግርና ወሬዎቿ ተነጥሎ፣ ዒባዳ ታስቦ፣ የተለያዩ የአምልኮ ተግባራትን መፈፀም እዚያው ለመዋልና ለማደር ጠቅሎ መስጊድ መግባት ማለት ነው፡፡ የቻለ አሥርቱን ቀናት ኢዕቲካፍ ማድረግ ይችላል፤ ያልቻለ የተመቸዉን ቀን መርጦ ኢዕቲካፍ ማድረግ ይችላል፡፡ ኢዕቲካፍ ነፍስን ያጠራል፣ ዉስጥን ያፀዳል፡፡ አሥርቱን ቀናት ኢዕቲካፍ ማድረግ የፈለገ ሰው ረመዷን 20 ቀን (ምሽቱ 21) ፀሐይ ከመጥለቋ በፊት መስጊድ ይገባና ነገ ዒድ ሲባል ከፀሐይ መጥለቅ በኋላ ይወጣል፡፡

"የሰው ልጅ ሆይ:- የተወለድከው ብቻህን ነው፣የምትሞተውም ብቻህን ነው፣ ቀብርም የምትገባው ለብቻህ ነው፣ ለምርመራ አላህ ፊት የምትቆመውም ለብቻህ ነው፣ጀነትም ይሁን ጀሀነም የምትገባው ለብቻህ ነው!"  ታዲያ ነገ የምትድንበትን ኸይር ስራ ለብቻህ መስራት እንዴት ይከበድሃል?!?

ዛሬ ዱኒያ ላይ መስፈርቱን ያሟላ መልካም ስራ ከሰራን ነገ ኣኺራ ላይ በጀነት ስናርፍ ድካሙን በሙሉ እንረሳዋለን! ከዛም አልፎ የከፈልነውን ዋጋ እንንቃለን!

በወርቃማ አስርቱ ቀናት፣

1/ ኢዕቲካፍ በመግባት

2/ ቁርኣን

3/ ለራሳችንም ለሌሎችም የተለያዩ ዱዓዎችን በማድረግ  በተለይም (አላህ ሆይ አንተ ይቅር ባይ ነህ ይቅር ማለትንም ትወዳለህ ይቅር በለኝ) የሚለውን ዱዓ ማብዛት

4/ ዚክር በማብዛት

5/ ሰደቃ

6/ ለሊቱን ሙሉውን -እስከ ሱሑር- በሰላት ብቻ ማሳለፍ የቻለ ይህን በማድረግ ይህን ያልቻለ ደግሞ ለሊቱን ከፋፍሎ በዚክር፣በዱዓእና በኢስቲግፋር እንዲሁም የቻልነውን ያክል ረዘም ያሉ 2/2 ረክዓ ሱንና ሰላቶችን በመስገድ ልናሳልፍ ይገባናል፡፡

አላህ ያግዘን ለይለቱል-ቀድርንም ይወፍቀን "ኣሚን"
ኡስታዝ አሕመድ አደም
123 viewsAm First, 22:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 14:28:17 70 የረመዳን መልእክቶች- በሸኽ ሙሐመድ ሓሚዲን .mp3
156 viewsAm First, 11:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 02:31:41
188 viewsAm First, 23:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 16:58:51 #የሰላምታ_አሰጣጥ

#ክፍል_3

#ሐዲሥ 132 / 854

ሚቅዳድ ባስተላለፉት ረዥም ሐዲሥ እንዲህ የሚል አውስተዋል፦ ለነቢዩ ከወተት የድርሻቸውን እንሰጣቸው ነበር። በሌሊት ይመጡና የተኛን በማይቀሰቅስና የነቃን በሚያሰማ ድምጽ ሰላምታ ያቀርቡልናል። (አንድ ቀን) እንደዚሁ መጡና ዘወትር እንደሚያቀርቡት ዓይነት ሰላምታ አቀረቡ። (ሙስሊም)

ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር

► ሰዎች በተኙበት ሰላምታ ማቅረብ ይፈቀዳል። ግና የተኛን ላለመቀስቀስና የነቁት ብቻ እንዲሰሙ ለማድረግ ጥንቃቄ ማድረግ ያሻል።
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
69 viewsAm First, 13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 16:58:50
70 viewsAm First, 13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 13:59:45 #ከቡድኖች_ጋር_አትወግን! #ምላስህን_ጠብቅ! #በሸኽ_ሰዒድ_አሕመድ_ሙስጠፋ.mp3
72 viewsAm First, 10:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 20:41:03 #የሰላምታ_አሰጣጥ

#ክፍል_2

ሐዲሥ 132 / 853

አነስ እንዳስተላለፉት፦ “የአላህ መልዕክተኛ አንዳች ነገር ሲናገሩ ለሰዎች ግልጽ ይሆን ዘንድ ሦስት ጊዜ ይደጋግሙት ነበር። ሰዎች ዘንድ በሚመጡበት ጊዜና ሰላምታ በሚያቀርቡ ጊዜም ሦስት ጊዜ ሰላምታ ያቀርባሉ።” (ቡኻሪ)
ይህን የሚያደርጉት ሰው በዝቶ አልሰማ ካለ እንደሆነ መረዳት ይቻላል።

ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች

1/ የአላህ መልዕክተኛ የነበራቸው እዝነት፡፡ ሰዎች መልዕክታቸውን እንዲረዱ ሁሉንም ዓይነት ስልት ይጠቀማሉ።
2/ አንዳች ነገር ሲደጋገም ይገባል።
3/ ሰላምታ አንድ ጊዜ ማድረስ ሱንናውን ከማግኘት አንጻር በቂ ቢሆንም ሁሉም ሰው እንዲሰማው መደጋገም ግን ሰው በዝቶ የማይሰማ ከሆነ ሸሪዓዊ ነው።
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
92 viewsAm First, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 20:40:59
85 viewsAm First, 17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ