Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja — ETHIO-MEREJA®
ርዕሶች ከሰርጥ:
Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 131.05K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 272

2022-06-07 14:48:21
ግንባታው ተቋርጦ የነበረው የብሔራዊ ቴአትር ህንፃ በድጋሚ በአዲስ መልክ ተጀመረ

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቴአትር ቤትን ለማዘመን በሚል ቴአትር ቤቱ በሚገኝበት ስፍራ ዘመናዊ አዲስ ህንጻ ለመገንባት ታቅዶ ወደ ተግባር ቢገባም የግንባታ ስራውን ለማከናወን ውል ወስዶ የነበረው ተቋራጩ አፍሮ ጺዮን ኮንስትራክሽ አማካይነት ግንባታው ቢጀመርም ከአንድ አመት በፊት ባጋጠመው መጓተት ሊቋረጥ እንደቻለ ተነግሮ ነበር፡፡

በ3 ዓመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል በሚል 1.5 ቢሊዮን ብር ተመድቦለት ሲሰራ የነበረው አፍሮ ጺዮን በድጋሜ ውሉን ማደስ እንደሚፈልግ ሃሳብ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም የቀረበለትን መስፈርት ሊቀበል ባለመቻሉ ጥያቄው ውድቅ መደረጉ ይታወሳል።

በአሁኑ ሰዓት ኦቢድ ኮንስትራክሽን የተሰኘው አዲስ ተቋራጭ የወጣውን ጨረታ በማሸነፍ ግንባታውን እንደጀመረ የፌደራል መንግስት ህንጻዎች ግንባታ ፕሮጀክት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ተክለጻዲቅ ተክለአረጋይ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

ተቋራጩ ከእዚህ ቀደም በነበረው ዲዛይን መሰረት የተቋረጠውን የግንባታ ሂደት በማስቀጠል በሶስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ህንፃውን ገንብቶ ለማጠናቀቅ ውል ማሰሩን ሃላፊው ገልጸዋል፡፡አዲስ የሚገነባው ህንጻ ባለ 12 ወለል እና ከሰባት ሺህ ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፍ ሲሆን ፣1.5 ቢሊዮን ብር ወጪ እንደሚጠይቅ ብስራት ሬድዮ መዘገቡ ይታወሳል፡፡

አዲሱ ህንጻ የቴአትር መስሪያ ቦታዎችን ቁጥር ከመጨመሩም ባለፈ የጊዜውን ዘመናዊነት የሚያሟላና ሙዚየም ጨምሮ የተለያዩ መገልገያዎችን የሚይዝ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል ፡፡
T.me/ethio_mereja
13.6K viewsedited  11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 11:28:57
#የችሎት ውሎ

ፍርድ ቤቱ ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ በአስር ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንድትለቀቅ አዘዘ!

“ሮሃ ሚዲያ” የተሰኘው የዩቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት መዓዛ መሐመድ በአስር ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንድትለቀቅ በፍርድ ቤት ተወሰነ።

የመዓዛን የዋስትና ጥያቄ ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 30 ቀን 2014 የፈቀደው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት መሆኑን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። መዓዛ ከጓደኛዋ መኖሪያ ቤት በፖሊስ የተያዘችው ከአስር ቀናት በፊት ግንቦት 20 ቀን 2014 ነበር።

#በሌላዜና

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እና ጋዜጠኛ ሰለሞን ሹምዬ የ10 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ በፍርድ ቤት ተፈቀደላቸው።

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝና ሰለሞን ሹምዬ እያንዳንዳቸው የ10 ሺ ብር ዋስትና በማስያዝ ከእስር እንዲለቀቁ ትዕዛዝ ሰጠ።

ፍርድ ቤቱ ፤ ፖሊስ በጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ እና በመስከረም አበራ ላይ እያደረገው ለሚገኘው ምርመራ ተጨማሪ ስድስት ቀናት ፈቅዷል። የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ትዕዛዙን ያስተላለፈው ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 30 ነው።
T.me/ethio_mereja
T.me/ethio_mereja
15.5K viewsedited  08:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 11:25:21
ቴሌግራም https://telegram.me/onlineshoppingce
አድራሻችን:- ቦሌ መድሐኔዓለም ቦሌ መሰናዶ ት/ቤት ፊትለፊት አለምነሽ ፕላዛ ሱቅ ቁጥር 05

+251941661030 / +251943190237
14.6K views08:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 11:24:49
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት

Join our telegram

https://t.me/+P7ctetopPExiY2Rk
15.0K views08:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 23:13:18
ፒያሳ ወርቅ ቤቶች ጀርባ በደረሰ የእሳት አደጋ የ15 አባወራ ቤቶች ወደሙ!!

ሶስት ሰዎች ላይ የጭስ መታፈን አደጋ ደርሷል

በአዲስ አበባ በአራዳ ክፍለ ከተማ ፒያሳ ልዩ ስሙ ወርቅ ቤቶች ጀርባ ዛሬ ከቀኑ 9ሰዓት ከ37 ደቂቃ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ የ15 አባወራዎች ቤቶች መውደማቸውን የእሳት አደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቃል፡፡

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት በአደጋው አንድ የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሰራተኛ እና ሁለት ነዋሪዋች ላይ በጭስ በመታፈናቸው ጉዳት ደርሶባቸዋል ብለዋል።

የእሳት አደጋው የደረሰበት ቦታ ከወርቅ ቤቶቹ ጀርባ ሲሆኑ ቤቶቹ እጅግ የተጠጋጉ፣ የኤሌክትሪክ ዝርጋታቸው እና ቤቶቹ የተሰሩበት ግብዐቶች ውድመቱን ከባድ አድርጎታል። በተጨማሪ የቆዩ ነባር ቤቶች በመሆናቸው አደጋው ሰፊ ሆኖ የበርካታ አባወራ ቤቶች እንዲወድሙ እንዳደረገው ተነግሯል።

ወደ ወርቅ ቤቶቹ እሳቱ እንዳይዛመት እና ከፍተኛ የንብረት ውድመት እንዳይደርስ የኮሚሽኑ ሰራተኞች መትጋታቸውን አቶ ንጋቱ ጨምረው ተናግረዋል።አደጋውንም ለመቆጣጠር 75 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች የተሳተፋ ሲሆን አስር የእሳት አደጋ ተሽከርካሪዋች 83ሺ ሊትር ውሃ አንድ ውሃ ጫኝ ተሽከርካሪ ከመንገዶች ባለስልጣን ጥቅም ላይ ውለዋል።እሳቱን ለመቆጣጠር አንድ ሰዓት ከሰላሳ ደቂቃ ፈጅታል።
T.me/ethio_mereja
19.5K viewsedited  20:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 15:49:51
በአዲስአበባ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ የሚዲ-ባስ እና ሚኒ-ባስ ተሸከርካሪዎች የታሪፍ ማሻሻያ ይፋ ሊደረግ ነው!!

በመዲናዋ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ የሚዲ-ባስ እና ሚኒ-ባስ ተሽከርካሪዎች አዲስ የታሪፍ ማሻሻያ ይፋ ሊደረግ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል፡፡

ለህብረተሰቡ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ የሚዲ-ባስና ሚኒ-ባስ ተሽከርካሪዎች አዲስ የትራንስፖርት ታሪፍ ማሻሻያ ነገ እለተ ማክሰኞ ከቀኑ 8፡30 ላይ ለሚዲያ ተቋማት ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡

የታሪፍ ማሻሻያው ከሰኔ 01 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን አፈፃፀሙ በተገቢው እንዲከወን የህግ አስከባሪ አካላት ሚና የጎላ በመሆኑ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ቢሮው አሳስቧል፡፡ህብረተሰቡም የሚወጣውን ትክክለኛ ታሪፍ አውቆ በመክፈልና ከታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ አሽከርካሪዎችን በማጋለጥ በኩል ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ቢሮው መልዕክት አስተላልፏል፡፡
T.me/ethio_mereja
21.7K viewsedited  12:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 13:37:21
ኢትዮጵያ ቢትኮይንን መሰል የዲጂታል መገበያያ ገንዘቦችን አገደች!!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ እንዳሳወቀው "ምናባዊ ንብረትን ወይም ዲጂታል መገበያያ ገንዘብ" ለግብይት ወይም ለክፍያ መጠቀም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዕውቅና ያልተሰጠው ድርጊት በመሆኑ ህብረተሰቡ ከእንደዚህ አይነት ሕገ-ወጥ ተግባር እራሱን እንዲጠብቅ አሳስቧል፡፡

የኢትዮጵያ የገንዘብ መደብ ብር እንደሆነና በብሔራዊ ባንክ በሌላ አኳኋን ካልተፈቀደ በስተቀር በሀገሪቱ የሚከናወኑ ማናቸውም የገንዘብ ግንኙነቶች ሁሉ የሚከፈሉት በብር እንደሚሆን የብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 591/2000 በግልጽ ይደነግጋል።

በተጨማሪም በክፍያ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 718/2003 መሠረት በየትኛውም የክፍያ መፈጸሚያ ሰነድም ሆነ ሥርዓት ያለ ብሔራዊ ባንክ ፍቃድ የገንዘብ ዝውውርም ሆነ ገንዘብ ነክ አገልግሎት መስጠት አይቻልም ብሏል ተቋሙ በመግለጫው፡፡ባንኩ ከጥናት ተረድቻለሁ እንዳለው በአሁኑ ወቅት ከህግ እውቅና ውጪ የክሪፕቶ ከረንሲ፣ እንደ ቢትኮይን እና የመሳሰሉት የዲጂታል መገበያያ ገንዘብ አገልግሎት በኢትዮጵያ እየተስፋፋ መጥቷል።

በተጨማሪም ይህ ተግባር ከብሔራዊ ባንክ እውቅና ውጪ ከፍተኛ የገንዘብ ዝውውር የሚደረግበት እና በተለይ በወንጀል የተገኘን ገንዘብ ለማሸሽ ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ እንደሆነ ለመረዳት ተችሏል ብሏል።እየተስተዋለ ያለው የዲጂታል መገበያያ ገንዘብን ለግብይት ወይም ለክፍያ መጠቀም ዕውቅና ያልተሰጠው ድርጊት እንደሆነ ብሔራዊ ባንክ በመግለጫው አስታውቋል፡፡

በመሆኑም ህብረተሰቡ ከእንደዚህ አይነት ሕገ-ወጥ ተግባር እራሱን እንዲጠብቅ ያሳሰበው ተቋሙ ይህን ፈጽመው በሚገኙ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጿል፡፡
T.me/ethio_mereja
21.3K viewsedited  10:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 13:14:40
ቴሌግራም https://telegram.me/onlineshoppingce
አድራሻችን:- ቦሌ መድሐኔዓለም ቦሌ መሰናዶ ት/ቤት ፊትለፊት አለምነሽ ፕላዛ ሱቅ ቁጥር 05

+251941661030 / +251943190237
19.6K views10:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-05 20:08:24
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ መንግሥት ኢ ሰብዓዊ አያያዝ እንዲያቆም ጥሪ አቀረበ።

ኢሰመጉ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ "በታሰረበት ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ በፖሊሶች ድብደባ እንደተፈጸመበት" ማረጋገጡን አስታውቋል። ግንቦት 18 ቀን 2014 በቁጥጥር ሥር የዋለው ተመስገን በተፈጸመበት ድብደባ "በአይኑ እና በጎድን አጥንቱ ላይ ጉዳት እንደደረሰበት" የገለጸው ኢሰመጉ "የፖሊስ ጣቢያው ሀኪም በውጪ እንዲታከም የጻፉለት ቢሆንም ሊታከም እንዳልቻለ" ገልጿል።

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ባወጣው መግለጫ "የኢሰመጉ መርማሪ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን በታሰረበት ፖሊስ ጣቢያ ለመጎብኘት ሙከራ ባደረገበት ወቅት ተጨማሪ መረጃዎችን መሰብሰብ እንዳይችል የፖሊስ ጣቢያው ፖሊሶች ለመተባበር ፈቃደኞች አልነበሩም" ሲል ነቅፏል። የኢትዮጵያ መንግሥት "ለጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እንዲሁም በእስር ላይ ለሚገኙ በርካታ ጋዜጠኞች ህጋዊ አካሄዶችን በመከተል ፈጣን ፍትህ እንዲሰጥ" ኢሰመጉ በዛሬው መግለጫ ጥሪ አቅርቧል።

ጋዜጠኛውን የደበደቡ የፖሊስ አባላት በአስቸኳይ ተጠያቂ እንዲሆኑ የጠየቀው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ "ፖሊስ ጣቢያዎች በእስር ላይ ያሉ ሰዎች ያሏቸውን መብቶች በአግባቡ እንዲያከብሩ እንዲሁም የእስረኞች ሁኔታን መከታተል ይችሉ ዘንድ ለሰብዓዊ መብት ተቋማት ተባባሪ እንዲሆኑ" ጥሪ አቅርቧል።
T.me/ethio_mereja
9.0K viewsedited  17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-05 20:04:59
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት

Join our telegram

https://t.me/+P7ctetopPExiY2Rk
8.3K views17:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ