Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Enterance Preparation

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_entrance_preparation_exam — Ethio Enterance Preparation E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_entrance_preparation_exam — Ethio Enterance Preparation
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_entrance_preparation_exam
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 398
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopia Enterance Preparation

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-04-12 15:56:43
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቀጣይ ዓመት ራስ ገዝ ለመሆን የሚያስችሉትን ቅድመ ዝግጅቶች ማጠናቀቁን አስታወቀ
....................................................

ሚያዝያ 04/2015ዓ.ም.(የትምህርት ሚኒስቴር) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቀጣይ ዓመት ራስ ገዝ ለመሆን የሚያስችሉትን ቅድመ ዝግጅቶች ማጠናቀቁን አስታውቋል ።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና የዩኒቨርሲቲው ራስ-ገዝ መሆን የአካዳሚ፣ የአስተዳደር፣ የፋይናንስ እና የሰው ሀብት አስተዳደራ ላይ የመወሰን ነጻነት የሚሰጥ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ደግሞ ለቀጣይ የዩኒቨርሲቲው ሁለተናዊ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን ገልጸዋል።

ፕሮፌሰር ጣሰው ዩኒቨርሲቲው ሲመሰረት ከራስ-ገዝነት ሥልጣኑ ጋር መሆኑን ጠቅሰው ነገር ግን ከጊዜያት በኋላ በተለያዩ መንግሥታት ቀስ በቀስ የራስ-ገዝነት ሥልጣኑን እያጣ መጥቶ አሁን ያለበት ደረጃ ላይ መድረሱን ተጠቁመዋል ።

ፕሮፌሰር ጣሰው ዩኒቨርሲቲው ከረዥም ዓመታት በኋላ ከቀጣይ አመት ጀምሮ የራስ-ገዝነት ሥልጣኑን ልያስመልሱለት የሚችሉ ውስጣዊ ቅድመ ዝግጅቶችን ላለፉት ሁለት አመታት ሲያደርግ መቆየቱንና በአሁኑ ወቅት ማጠናቀቁን ጠቅሰው ለአብነት ያክልም የዩኒቨርሲቲው የፋይናንስና የሰው ኃይል አደረጃጀት መመሪያ መዘጋጀቱን፣ በመመሪያ ላይ ከሠራተኞች ጋር ውይይት መደረጉንና በቀጣይ ለቦርድ ውሳኔ የሚቀርብ መሆኑንም ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት በ14 ካምፓሶች 70 የቅድመ-ምረቃ እና 293 የድህረ-ምረቃ የትምህርት ፕሮግራሞችን እየሰጠ ይገኛል።

ምንጭ፡- ኢዜአ
4.0K views12:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 14:26:09 የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ዝግጁ እንዲሆኑ አስፈላጊው ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን የመንግስት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ገለጹ
....................................................
ሚያዝያ 04/2015 ዓ.ም .(የትምህርት ሚኒስቴር) የትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ዓመት የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና እንደሚሰጥ ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

መውጫ ፈተናው ተማሪዎች በሰለጠኑባቸው የሙያ ዘርፎች ብቁ መሆናቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው ፡፡

የመውጫ ፈተና በኦንላይን ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የሚሰጥ ሲሆን ኢዜአ ያነጋገራቸው የመንግስት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር መውጫ ፈተናውን ለመስጠት ተዘጋጅተዋል፡፡

የጅማ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል አባፊጣ መውጫ ፈተና ተማሪዎች በዩኒቨርስቲ ቆይታቸው የሚጠቀሙባቸውን እውቀት ክህሎትና አመለካከት በብቃት መያዛቸውን መለኪያ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ይህም ብቻ ሳይሆን ዩኒቨርስቲዎች በትምህርት አሰጣጥ ላይ ያሉበትን ሁኔታ በማሳየት የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ሚናው የጎላ መሆኑን አስረድተዋል ፡፡

የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ የመውጫ ፈተናውን በሚመለከት የግንዛቤ ማስጨበጫ መሰጠቱንና አስፈላጊውን ግብዓት የማሟላት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ከዚህ ጎን ለጎንም ተፈታኞችን በእውቀትና በስነልቦና የማዘጋጀት ስራ መሰራቱንም ጠቅሰዋል፡፡

የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ፍሬው ተገኝ በበኩላቸው የመውጫ ፈተና ውጤት ፍትሀዊነትን የሚመልስ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የመውጫ ፈተናው የመጀመሪያው እንደመሆኑ መጠን ለተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫና ድጋፍ ለሚፈልጉ ተማሪዎች ድጋፍ የማድረግ ስራ እየተሰራ ስለመሆኑን ተናግረዋል፡፡

ፈተናው የሚሰጥባቸውን የትኩረት መስኮች በመለየት የማጠናከሪያ ፕሮግራም እየተሰጠ ነው ያሉት ደግሞ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ዳምጠው ደርዛ ናቸው፡፡

ጎን ለጎንም ለሴቶችና ልዩ ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች በልዩ ሁኔታ ተኩረት ተሰጥቶ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል ፕሬዚዳንቱ፡፡

የከፍተኛ ትምህርት አገራዊ ቅድመ ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና በአግባቡ ለመምራትና ለማስተዳደር የተዘጋጀው የፈተና ማስፈጸሚያ መመሪያ ባለፈው ዓመት ነሀሴ ወር ላይ መጽደቁ ይታወሳል፡፡
3.8K views11:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 21:07:54
በአገር አቀፍ ደረጃ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻል ሥራ በቅርቡ ይጀመራል-ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
................................................................................

ሚያዝያ 3/2015(የትምህርት ሚኒስቴር)፦ በአገር አቀፍ ደረጃ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻል ሥራ በቅርቡ የሚጀመር መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።

የአዲስ ወግ “የመደመር ትውልድን መቅረጽ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ በተደረገው መድረክ የውይይት መነሻ ሃሳብ ያቀረቡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ መንግሥት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በሁሉም አካባቢዎች ምቹ የትምህርት ቤት ከባቢ መፍጠር፣ የትምህርት ቤት አመራር ሥልጠና፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ማሻሻል ከዋና ዋና ሥራዎች መካከል መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በአገር አቀፍ ደረጃ ከ47ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን የተናገሩት ሚኒስትሩ ከእነዚህም መካከል አብዛኛዎቹ ተገቢውን መስፈርት ባሟላ መልኩ የተገነቡ አለመሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም በአገር አቀፍ ደረጃ ሕብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ የማሻሻል ዘመቻ ለማከናወን ዕቅድ ተዘጋጅቷል ብለዋል ሚኒስትሩ።

ዘመቻውም በቅርቡ ይፋ ተደርጎ ወደ ተግባር እንደሚገባ ጠቅሰው የትምህርት ቤት አመራሮችን ብቁ ማድረግ የሚያስችል ሥልጠና እንደሚከናወን ገልጸዋል።
5.8K views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 13:30:23 During the discussion, the participants forwarded their appreciation and pledged to support the center for One Health. And all stakeholders were urged to play a vital role in supporting and working with JU-COH, in research capacity building and improving laboratory infrastructure to optimize the health of people, animals, and ecosystems. JU-COH kindly invites all possible local, national, and global organizations to collaborate and work together for the advancement of human, animal, and environmental well-being through the One Health approach.

We are in the Community!
5.3K views10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 13:30:23 Jimma University (JU) in collaboration with Africa One Health University Network (AFROHUN-Ethiopia) launched the Center for One Health Research, Training, and Outreach (JU-COH) at Jimma University on April 6, 2023.
**********
Jimma University and AFROHUN Ethiopia supported by USAID fund, have been working together for the last 13 years to implement and advocate the One Health approach; an integrated, unifying approach that aims to balance and optimize the health of people, animals, and ecosystems.

Jimma University hosted the inaugural workshop of the Center for One Health Research, Training, and Outreach (JU-COH) at Jimma University (JU) which was established to institutionalize One Health approach and collaborate with similar centers in the world. The workshop was attended by key stakeholders and partners, including Dr. Feyesa Regassa (the Chairperson of National One Health Steering Committee (NOHSC) and the representative of MoH), Dr. Sandhya Sukumaran (USAID Ethiopia's Global Health Security Advisor), Dr. Berihu Gebrekidan (AFROHUN-Ethiopia's Country Manager), Prof. Netsanet Workneh (Jimma University Vice President for Research and community services), and delegates from Mekelle, Gondar, Wollo, Bule Hora Universities, representatives from Jimma zone administration, JU senate members and JU community.

The launching workshop started with a welcome and keynote address by Prof. Netsanet Workneh, Vice President of Jimma University. She addressed the importance of the One Health (OH) approach in alleviating global health threats including global climate change, food safety and security, antimicrobial resistance (AMR) and other challenges, which requires a collaborative, multisectoral, and trans-disciplinary approach, if optimal health outcomes for people, animals, and ecosystems are to be achieved. Prof. Netsanet also appreciated the support from AFROHUN Ethiopia, and thanked all the stakeholders for collaborating with JU in relation to One Health.

The chairperson of the NOHSC, Dr. Feyesa Regassa, delivered an opening speech, emphasizing the importance of adopting a mandatory OH approach to address emerging and re-emerging zoonotic disease and AMR problems. This is particularly needed as the world navigates the COVID-19 pandemic, Monkeypox, and other emerging health threats that have, and will seriously impact wellbeing of humans all over the world. Representing his office, he also appreciated the efforts of Jimma University and AFROHUN Ethiopia for establishing the center that will definitely contribute and support the national One Health activities.

Global Health Security Technical Advisor at USAID Ethiopia, Dr. Sandhya Sukumaran, also addressed the role of USAID Ethiopia in strengthening the existence of a public health system capable of preventing, detecting, and responding to infectious disease threats, through a commitment in developing a One Health workforce as an integral component of building national health security. Appreciating AFROHUN Ethiopia and Jimma University for taking One Health to high level in the country, she promised that USAID will continue to support and collaborate with AFROHUN, the new center for One Health in JU and similar initiatives in other universities in Ethiopia.

There were presentations on, ‘’Status of One Health activities and One Health Coordination in Ethiopia’; by Dr. Feyesa Regassa,; ‘’AFROHUN Ethiopia: Priority areas, Implemented and Planned Activities’’ by Dr. Berihu Gebrekidan, Country Manager. Dr Berihu, highlighted the genesis and evolution of OH and AFROHUN, and then presented AFROHUN’s vision relating to the OH advocacy, training, and research in the region. Moreover, JU- COH Director, Prof. Seid Tiku, gave a brief presentation on the vision, mission, goals and thematic areas in which the center envisions to be the nation's leading center of excellence in One Health research and academics for the advancement of human, animal, and environmental wellbeing.
4.6K views10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 13:30:05
3.5K views10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 08:32:13 የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ረቂቅ አዋጁ   ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች እንዲያካትት ተደርጎ መዘጋጀት አለበት
፦የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ
...............................................................................

ሚያዚያ 6/2015 ዓ.ም.(የትምህርት ሚኒስቴር)፣   በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በትናንትና ውሎው የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ረቂቅ አዋጁ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች እንዲያካትት ተደርጎ በጥንቃቄ መዘጋጀት እንዳለበት አሳስቧል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) እንዳሉት ረቂቅ አዋጁ የዩኒቨርሲቲዎችን አካዳሚክ ነፃነት የሚያጎናፅፍ ቢሆንም ከመንግሥትም ሆነ ከግል ዩኒቨርሲቲዎች የሚመረቁ ተማሪዎች ላይ ቅሬታ እንዳይፈጥር የዩኒቨርሲቲዎችን ፍላጎት ብቻ ሳይሆን የኅብረተሰቡን ፍላጎትም ያካተቱ መሆን አለባቸው ብለዋል፡፡

የተከበሩ ዶክተር ነገሪ አክለውም የቦርድ አባላት፣ ፕሬዚዳንቶች፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶና ሌሎች የዩኒቨርሲቲዎቹ አመራሮች ስብጥር ፆታዊ ብቻ ሳይሆን ሕብረ-ብሔራዊነትን እንዲያካትቱም በረቂቅ አዋጁ መመላከት እንዳለበት ጠቁመዋል፡፡

በየዩኒቨርሲቲዎቹ የሚሠሩ የአስተዳደር ሠራተኞች ትኩረት እንደማይሰጣቸው በየጊዜው ቅሬታ ስለሚያነሱ ረቂቅ አዋጁ ለአካዳሚክ ሠራተኞች የሚሰጠውን ትኩረት ለአስተዳደር ሠራተኞችም መስጠት እንዳለበት ዶክተር ነገሪ አስታውሰው፤ የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች የገንዘብ አቅም ያላቸውን ብቻ እንዲያስተምሩ ተደርገው የሚቋቋሙ ከሆነ የፍትሐዊነት ጥያቄ ስለሚያስነሳ ረቂቅ አዋጁ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች በፍትሐዊነት እንዲያስተናግድ ተደርጎ መዘጋጀት እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡

ረቂቅ አዋጁ መስማት የተሳናቸውን ብቻ ሳይሆን ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ሌሎች ተማሪዎችንም እንዲያካትት ተደረጎ መዘጋጀት እንዳለበት የተከበሩ ዶክተር ነገሪ ጨምረው ጠቁመዋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ ዶክተር ቤተልሔም ላቀውም በበኩላቸው የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ኃብት ከማመንጨት ባሻገር ለትምህርት ጥራት ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ እና የመማሪያ ሆስፒታሎች ላሏቸው ዩኒቨርሲቲዎች ረቂቅ አዋጁ ትኩረት እንዲሰጣቸው የተከበሩ ዶክተር ቤተልሔም ጨምረው አመላክተዋል፡፡

የምክር ቤት አባላትም በበኩላቸው የሚቋቋሙት ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች የግዥና ንብረት የማስተዳደር ሥርዓታቸውን በግዥ ሥርዓትና የንብረት አስተዳደር ሕግ መሠረት እንዲያደርጉና የኦዲት አደራረግ ሥርዓትን እንዲያመላክት ተደርጎ በረቂቅ አዋጁ መካተት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በበኩላቸው የሚቋቋሙት የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ምቹ የአመራርና የአስተዳደር ሥርዓት እና የአካዳሚክ ነፃነት እንዲኖራቸው በማድረግ የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ከዓለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ተወዳዳሪ ለማድረግ ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ ረቂቅ አዋጁ መዘጋጀቱን ጠቁመው፤ ረቂቅ አዋጁም ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች በፍትሐዊነት እንዲያገልግል ተደርጎ የተዘጋጀ ነው ብለዋል፡፡

ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች መስፈርቱን ሲያሟሉ ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ እንደሚሆኑ ጠቁመው፤ በአንፃራዊነት የረጅም ዓመታት ልምድና የተሻለ ኃብት ባለው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጀመር በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ደግሞ ስምንት ዩኒቨርሲቲዎችን የራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች በምልክት ቋንቋ ትምህርት ለመስጠት በረቂቅ አዋጁ የተመላከተ ቢሆንም ልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች ግን በሚወጡት መመሪያዎች የሚካተቱ መሆኑን አመላክተው፤ ረቂቅ አዋጁ የሕዝብን፣ የመንግሥትንና የዩኒቨርሲቲዎችን ጥቅም አካቶ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ምንጭ:- የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

https://t.me/+5UtUmeE0OYAwOGU8
https://t.me/+5UtUmeE0OYAwOGU8
4.3K views05:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 08:31:44
3.9K views05:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 22:30:26 Exit Exam

Department :- Plant Science

MODULE

Join AND share our channel
https://t.me/+5UtUmeE0OYAwOGU8
https://t.me/+5UtUmeE0OYAwOGU8
1.1K views19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 22:30:24 Exit Exam modules for plant science
864 views19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ