2023-04-27 21:54:19
በመጀመሪያ ደረጃ በአቶ ግርማ የሽጥላ ሕልፈት የተሰማኝን ኀዘን መግለጽ እፈልጋለሁ። ለቤተሰቦቹም መጽናናትን እመኛለሁ።
ከዚህ ባለፈ ግን በመስቀል አደባባይ የድጋፍ ሰልፍ ላይ በተወረወረው ቦንብ ዙሪያ በቂ ማጣራት ሳይደረግ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አንደበት "የቀን ጅቦች ናቸው የወረወሩት" ተብሎ በተነገረው መሠረት ምንም የማያውቁ ወገኖች ላይ የማሳደድ ሥራ እንደተሠራው ሁሉ... ዛሬም ግድያው በተፈጸመ ቅጽበት ያለምንም ምርመራ "ጽንፈኞች" የሚል ተመሳሳይ ፍረጃ ውስጥ በመዘፈቅ የፖለቲካ ቁማር ማሰናዳት ተገቢ አይደለም እላለሁ። መላው የአማራ ሕዝብም አንድነቱንና ሕብረቱን አጠናክሮ ክልሉንና እራሱን መጠበቅ ይገባዋል እላለሁ።
7.4K viewsAssaye Derbie, 18:54