Get Mystery Box with random crypto!

ሰበር ዜና ET🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ et_seber_zena — ሰበር ዜና ET🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ et_seber_zena — ሰበር ዜና ET🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @et_seber_zena
ምድቦች: መዝናኛዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.66K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎች በትኩሱ ና ሳይዉሉ እንዲሁም ሳያድሩ በቻናሉ በኩል ይደርሳሉ
ለአስተያየት እና ለማስታወቂያ ስራዎች 👇👇

@Akiyas21bot
የyoutube ቻናላችን ይቀላቀሉ👇👇

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2023-04-18 11:43:32 በሱዳኑ ግጭት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 144 መድረሱን ኮሚቴው ገለጸ

የሱዳን ዶክተሮች ኮሚቴ፣ በሱዳን በተቀሰቀሰው ግጭት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 144 ከፍ ማለቱን ገልጿል።

ኮሚቴው የቆሰሉ ሰዎች ቁጥር 1409 መድረሱንም ጠቅሷል።

ነገርግን ተመድ የሟቾችን ቁጥር ወደ 185 ከፍ አድርጎታል።

በሱዳን ጦር እና በጀነራል ሀምዳን ዳጋሎ በሚመራው የፈጥኖ ደራሽ(አርኤስኤፍ) መካከል ባለፈው ቅዳሜ የተቀሰቀሰው ጦርነት አሁንም እንደቀጠለ ነው።

አሜሪካን ጨምሮ በርካታ ሀገራት ሁለቱ ተፋላሚ ወገኖች ግጭት እንዲያቆሙ እየጠየቁ ነው።
ተመድ አሁን ላይ ድርድር ለመጀመር በሁለቱም ወገኖች በኩል ፍቃደኝነት የለም ብሏል(AlAin)።
@ET_SEBER_ZENA
@ET_SEBER_ZENA
2.9K viewsedited  08:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 08:57:13 የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከጠላት ጋር መተባበርን ጨምሮ ሕወሃት በጦርነቱ ወቅት ባወጣቸው 30 ክልከላዎች የታሠሩ ግለሰቦችን ለመፍታት መወሰኑን ቪኦኤ ዘግቧል። ውሳኔው ምርመራ ላይ የሚገኙ፣ በክስ ሂደት ያሉና በፍርድ ቤት ውሳኔ የታሠሩ ግለሰቦችን እንደሚመለከት ቢሮው መናገሩን የገለጠው ዘገባው፣ ሰው የገደሉ፣ ጾታዊ ጥቃት ያደረሱ ወይም ከኤርትራ ጋር የተባበሩ ግን ውሳኔው አይመለከታቸውም መባሉን ዘገባው ጠቅሷል። በውሳኔው መሠረት የሚፈተት እስረኞች ብዛት ስንት እንደኾነ ግን ቢሮው አልተገለጠም ተብሏል። የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር እስረኞችን ለመፍታት የወሰነው የሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ በእስር ላይ መቆየታቸው አስፈላጊ ስላልኾነ መኾኑን ቢሮው መግለጡን ዘገባው ጨምሮ አመልክቷል።
@ET_SEBER_ZENA
@ET_SEBER_ZENA
276 viewsedited  05:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 08:50:38 "ለበዓል ልብስ አልተገዛልኝም" በሚል ምክንያት ያኮረፈዉ ወጣት እራሱን አጠፋ
በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ደቡብ አሪ ወረዳ ለበዓል ልብስ አልተገዛልኝም በሚል ከቤተሰቦቹ ተጨቃጭቆ መግባባት ያልቻለዉ ወጣት በገመድ እራሱን ሰቅሎ ሕይወቱን ማጥፋቱ የክልሉ ፖሊስ አስታወቀ።

በደቡብ አሪ ወረዳ ባላመር ቀበሌ ነዋሪ የሆነዉ ወጣቱ ለ2015 የትንሳኤ በዓል ልብስ እንዲገዛለት ለወላጆቹ ጥያቄ ማቅረቡ ተከትሎ፤ ወላጆቹ ቀደም ሲል የሚለብሳቸዉን ልቦሶች አጽድቶ በመልበስ የዘንድሮዉን በዓል አክብሮ እንዲዉልና በሱ ጥያቂነት ሳይሆን አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ቤተሰብ አልባሳት ይገዛልሀል የሚል ተስፋ አስቆራጭ ምላሽ ይሰጠዋል።

ወጣቱ በወላጆቹ እምቢታ ተናዶ እራሱን እንደሚያጠፋ ዝቶ ከቤተሰቦቹ ጋር ከስምምነት ሳይደርስ መለያየቱን ከፖሊስ በደረሰን መረጃ ለመረዳት ተችሏል።

ወጣቱ እራሱን ለማጥፋት ቢዝትም ቤተሰብ እንዲህ አይነቱ እኩይ ተግባር ሊፈፅም ይችላል የሚል ጥርጣሬ እንዳልነበረው ተገልጿል። ነገር ግን ሚያዝያ 08 ቀን 2015 ከቀኑ 12:00 ሰዓት ላይ ወጣቱ እራሱን በገመድ ሰቅሎ በድን ገላዉ ዛፍ ላይ ተንጠልጥሎ እንደተገኘና የወጣቱ አድራጎት ቤተሰቡን በእጅጉ ያስደነገጠና ያሳዘነ ሆኖ ማለፉን ነዉ ፖሊስ ያስታወቀዉ።

ኹለት ወራትን በፆም በፀሎት የከረሙት የሟች ቤተሰቦች የፋሲካን በዓል ለማክበር ያልታደሉ ሆነዉ ድንኳን ቀስተዉ የልጃቸዉ ሀዘን ለመቀመጥ ተገደዋል።

ወላጆች ልጆቻቸዉ ለሚያቀርቡላቸዉ ጥያቄዎች በተግባር ምላሽ መስጠት የማይችሉ ከሆነ እንዲህ አይነቱ ዉጤት በማያስከትል መልኩ በበጀት እጥረት ምክንያት የአቅም ዉስንነት ይሁን ሌሎችንም ምክንያቶች በመጥቀስ በፍቅር ልጆችን የማሳመን ሥራ መስራት እንጂ፤ ከልጆች ጋር እልህ ተጋብቶ እነሱን በኃይል በመጫን አይደረግልህም የሚል አቋም መያዝ ስህተት መሆኑ ማመን እንደሚያስፈልግም የደቡብ ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል።
ሚያዝያ 10/2015 ዓ.ም
=======≠========
ለተጨማሪ መረጃዎች ቻናላችንን join ያድርጉ፣መረጃ ለሚፈልጉ ለሌሎች ጋብዙ
@ET_SEBER_ZENA
@ET_SEBER_ZENA
392 views05:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 08:50:21 #sudan_news
በሱዳን የሚገኘው የአሜሪካ ኢምባሲ ተደበደበ
በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ብረት ለበስ ተሽከርካሪው " ሆን ተብሎ " በጥይት መደብደቡን ኢምባሲው ያስታወቀ ሲሆን ድርጊቱን የፈፀመው ሄሜቲ የሚመሩት RSF ቡድን መሆኑን ኤምባሲው ለአል አረቢያ ገልጿል።

ኤምባሲው ተሽከርካሪው በ100 ጥይት መደብደቡን ገልጾ ድብደባው ያደረሰው ምንም ጉዳት የለም ብሏል።

በሌላ በኩል ፤ የአሜሪካ መንግሥት ጦርነት ውስጥ ካለችው ሱዳን ዜጎቹን የማስወጣት እቅድ እንደሌለው ዋይትሃውስ አሳውቋል።

በተያያዘ ዜና በሱዳን ካርቱም ሚገኙት የአውሮፓ ህብረት (EU) አምባሳደር በመኖሪያ ቤታቸው ጥቃት እንደተፈፀመባቸው ተሰምቷል ።

አምባሳደሩ ጥቃት እንደተፈፀመባቸው ያሳወቁት የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ዲፕሎማት ጆሴፕ ቦሬል ናቸው (በትዊተር ገፃቸው)።

ቦሬል ስለ ጥቃቱ ምንም አይነት ዝርዝር ነገር ባይገልጹም አምባሳደሩ ግን " ደህና ናቸው " ብለዋል።

የዲፕሎማቲክ ቦታዎችን እና ሰራተኞችን ደህንነት ማስጠበቅ የሱዳን ባለስልጣናት ቀዳሚ ኃላፊነት ነውም ሲሉ ገልጸዋል።

ምንም እንኳን ቦሬል ፤ በሱዳን የአውሮፓ ህብረት አምባሳደርን ስም ባይፅፉም ስማቸው አይዳን ኦሃራ የሚባሉ ሲሆን የ #አየርላንድ ዲፕሎማት ናቸው።

ቦሬል ካርቱም ውስጥ የተፈፀመው ጥቃት ፤ በሌሎች ሀገራት የሚሰሩ ዲፕሎማቶች ጥበቃን የሚደነግገውን የተመድ ስምምነት የ " ቪይና ኮንቬንሽን " በእጅጉ የጣሰ ነው ብለዋል።

በሌላ በኩል ፥ የአውሮፓ ህብረት ቃል አቀባይ ናቢላ ማስራሊ ለAFP በሰጡት ቃል " የሰራተኞች ደህንነት ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው " ብለዋል፤ የተፈፀመውን ጥቃት ተከትሎ የአውሮፓ ህብረት ልዑካን ቡድን ከካርቱም እንዲወጣ እንዳልተደረገ ተናግረዋል።
ቃል አቀባይዋ ፤ በሱዳን ያለው የፀጥታ እና ደህንነት ሁኔታ እየተገመገመ ነው ብለዋል።
@ET_SEBER_ZENA
@ET_SEBER_ZENA
358 views05:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 08:50:21
348 views05:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 20:50:30 በናይጄሪያ የአየር መንገድ ሠራተኞች አድማ መቱ
በናይጄሪያ የአውሮፕላን ጣቢያ ሠራተኞች የሁለት ቀናት የሥራ ማቆም አድማ ላይ በመሆናቸው፣ አየር መንገዶች በረራቸውን ሲሰርዙ፣ በሺሕ የሚቆተሩ መንገደኞች መጉላላት ደርሶባቸዋል፡፡

ሰባት የሚሆኑ የአውሮላን ጣቢያ ሠራተኞች ማኅበራት አድማውን የጠሩት መንግሥት ስምምነት ላይ በተደረሰው መሠረት የአውሮፕላን ጣቢያ የሥራ ሁኔታን የሚያሳየውና በቅርቡ የተጠናቀረው ሪፖትርት ይፋ ባለመሆኑ እና በናይጄሪያ ዝቅተኛ የክፍያ መጠን የሆነውን በወር 65 ዶላር መንግሥት ሊከፍል ባለመቻሉ ነው ተብሏል፡፡
ሚያዝያ 9/2015 ዓ.ም
=======≠========
ለተጨማሪ መረጃዎች ቻናላችንን join ያድርጉ፣መረጃ ለሚፈልጉ ለሌሎች ጋብዙ
@ET_SEBER_ZENA
2.3K views17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 20:50:20
500ሺ ኢትዮያውያን ወደ ሳውዲ
የኢትዮጵያ መንግሥት በሳዑዲ ዓረቢያ በቤት ሠራተኛነት ቀጥረው የሚሠሩ ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 40 የሚኾኑ 500 ሺህ ሠራተኞችን እየመለመለ መኾኑን አልጀዚራ ዘግቧል።

አማራ ክልል ብቻ 150 ሺህ አመልካቾችን እንዲመዘግብ በመንግሥት መታዘዙን መናገሩን ዘገባው አመልክቷል።

ተቀጣሪ ሠራተኞች ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ በመንግሥት ወጪ እንደሚጓዙና ወርሃዊ ደመወዛቸው 1 ሺህ የሳዑዲ ሪያል ወይም 266 የአሜሪካ ዶላር እንደሚኾን ዘገባው አመልክቷል።መንግሥት አመልካቾች እንዲመዘገቡ በተለያዩ ከተሞች ጥሪ ሲያደርግ እንደነበር ይታወሳል(ዋዜማ)።
ሚያዝያ 9/2015 ዓ.ም
=======≠========
ለተጨማሪ መረጃዎች ቻናላችንን join ያድርጉ፣መረጃ ለሚፈልጉ ለሌሎች ጋብዙ
@ET_SEBER_ZENA
2.3K views17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 17:22:49 በጌዴኦ ዞን የኮሌራ ወረርሽኝ  መከሰቱ ተገልጿል

በዚህ መሰረት በዞኑ የተከሰተውን የኮሌራ በሽታ ለመከላከልና ጊዜያዊ የኮሌራ ህክምና ማዕከል መቋቋሙ ተገልጿል

በዲላ ከተማ ኦዳያኦ ጤና ጣቢያ ግቢ በማቋቋም ወደሥራ  መግባቱን በውይይቱ ገምግሟል።

መምሪያው የህብረተሰብ ጤና ስጋቶች መከላከል በተከናወኑ ተግባራት፣ ባጋጠሙ ተግዳሮቶችና በቀጣይ መከናወን ስላለባቸው ጉዳዮች ትኩረት ሰጥቶ መክሮባቸዋል ከነዚህም መካከል የወቅቱን ዝናብ መነሻ በማድረግ የኮሌራ ወረርሽኝ  ተግባራት በትኩረት ተችሯቸዋል ።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በጤናው ዘርፍ በማንኛውም ወቅት ለሚከሠቱ የህብረተሰብ ጤና ስጋቶችና ክስተቶች አፋጣኝ መልስ መስጠት የሚያስችል አቅም የመገንባትና ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ መቀጠል የተከሰተው ወረርሽኝ እንዳይስፍፍህብረተሰቡ  የመጸዳ ቤቶችን በንፅህና መጠቀም ፣ በአከባቢው የሚገኝን ውሃ አፍልቶ በማቀዝቀዝ መጠቀም ፣ ከገበያ የሚገዙ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን በንፅህና አጥቦ መጠቀም ፣ እጅን በውሃና በሳሙና አዘውትሮ መታጠብ ፣ የበሽታው ምልክት የታየባቸው ግለሰቦችን በፍጥነት ወደ ጤና ተቋም ማድረስ እንዳለባቸው ገልጿል።
ምንጭ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ
የደ/ብ/ብ/ህ/ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ
@ET_SEBER_ZENA
@ET_SEBER_ZENA
2.7K viewsedited  14:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 14:55:26 ስጋ ከድመት ለማስጣል የሞከረችው የ18 ዓመት ወጣት ለሞት ተዳረገች
በአዲስ አበባ ከተማ በአቃቂ ቃሊት ክፍለ ከተማ አለም ባንክ አካባቢ ስጋ ይዛ ጣራ ላይ የወጣችን ድመት ለማውረድ የሞከረችው የ18 አመት እድሜ የሆናት ሴት በደረሰባት የኤልክትሪክ አደጋ ህይወቷ ማለፉ ታውቋል፡፡
ወጣቷ በድመት የተወሰደባትን ስጋ ለማስጣል በሞከረችበት ጊዜ ነው በኤልክትሪክ ምክንያት ህይወቷ ያለፈው ተብሏል፡፡

በአጠቃላይ በበአሉ ቀን እና በዋዜማው እለት የሶስት ሰዎች ህይወት ማለፉ የነገረ ሲሆን ከትራፊክ አደጋ ጋር በተያያዘም በዋዜማው ሁለት የሞት አደጋ መድረሳቸው ተነግሯል፡፡
ከበአሉ ጋር በተያያዘ የከፋ የጸጥታ ችግር ባያጋጥምም በጸም ምክንያት ግን የአንድ ሰው ህይወት ማለፉን በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሆኑት ምክትል ኮማንደር  ማርቆስ ታደሰ ተናግረዋል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግኑኝነት ሃላፊ ም/ኮምማንደር ማርቆስ ታደሰ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ባልደራስ አካባቢ በተከሰተ አለመግባባት የአንድ ሰው ህይወት አልፋል ብለዋል፡፡
ከዚህ ግድያ ጋር በተያያዘም የተጠረጠሩ እስካሁን ድረስ 8 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ነው የተገለጸው፡፡
ፖሊስ አሁንም ከግድያው ጋር በተያያዘ ምርምራ እያካሄደ እንደሚገኝም ጨምረው  ገልጸዋል፡፡
በሔኖክ ወ/ገብርኤል
ሚያዝያ 9/2015 ዓ.ም
=======≠========
ለተጨማሪ መረጃዎች ቻናላችንን join ያድርጉ፣መረጃ ለሚፈልጉ ለሌሎች ጋብዙ
@ET_SEBER_ZENA
@ET_SEBER_ZENA
2.9K views11:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 12:41:49
ጋዜጠኛ ገነት አስማማው በ10ሺ ብር ዋስትና እንድትለቀቅ ፍ/ቤቱ ወስኗል።

@ET_SEBER_ZENA
@ET_SEBER_ZENA
1.0K views09:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ