Get Mystery Box with random crypto!

የኤማሁስ መንገደኞች........ channel )

የቴሌግራም ቻናል አርማ emmausmengdgnch — የኤማሁስ መንገደኞች........ channel )
የቴሌግራም ቻናል አርማ emmausmengdgnch — የኤማሁስ መንገደኞች........ channel )
የሰርጥ አድራሻ: @emmausmengdgnch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 316

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-06-30 23:01:22
##አሁን በሚሆንባችሁ እና እያለፋችሁበት ባለው ህይወታችሁ ተስፋ አትቁረጡ!
##ጌታ ቀን አለው
##በምንም ተስፋ አልቆርጥም ተስፋ አትቁረጡ
##የጊዜው ድምጽ ለጊዜው ነው ሁኔታዎች ይለወጣሉ በፍጹም አይቀጥሉም አስቀድማችሁ የሰማችሁት ነው ትክክል እሱ ደግሞ የጊዜ ጉዳይ እንጂ ይሆናል
##ለሁሉም ጊዜ አለው
በሁኔታዎች ጊዜ ዳዊት የበግ እረኛ ነበር !
## በእግዚአብሔር ቀን ንጉስ ሆነ ።
በሁኔታዎች ጊዜ ሩት ከሰው እርሻ ቃርሚያ ለቃሚ ነበረች!
##በእግዚአብሔር ቀን የእርሻው ባለቤት ሆነች ።
በሁኔታዎች ጊዜ መርዲክዎስ ቤተመንግስት በራፍ ለማኝ ነበር!
##በእግዚአብሔር ቀን የቤተመንግስት ውስጥ አማካሪ ሆነ ።
እግዚአብሔር ቀን አለው እኛ የምናመልከው እግዚአብሔር በዙሪያችን ያለው ሁኔታ ቀይሮ የሁኔታዎች ባለቤት የሚያደርግ ነው
በሁኔታዎች ተስፋ ይቆረጥ ይሆናል ግን በእግዚአብሔር ከቶ አይቆረጥም እመነኝ ቀን አለው እንዳለቀስክ አትቀርም!
https://t.me/Emmausmengdgnch
https://t.me/Emmausmengdgnch
141 views🇩aኒ Revival , edited  20:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 10:28:21 አሜሪካዊው ቢሊዬነር ስቲቭ ጆብስ በህይወቱ መጨረሻ ሰዓት ላይ ያስተላለፈው አስደናቂ መልዕክት

ስቲቭ ጆብስ በ56 አመቱ ያረፈ አሜሪካዊ ቢሊዬነር ሲሆን ህይወቱ ያለፈው በካንሰር በሽታ ነው::

በንግዱ አለም ውስጥ የመጨረሻ ከፍታ ጫፍ የሚባለው ቦታ ደርሻለሁ፣ ይሁን እንጂ ከዚህ ሁሉ ሀብት ደስታን ማግኘት አልቻልኩም። በልፋቴ ካከማቸሁት ሃብት ያገኘሁት ደስታ እዚህ ግባ የማይባል ነው፣
,
አሁን፣በህይወቴ የመጨረሻው ሰዓት አካባቢ፣አልጋ ላይ ሆኜ ያሳለፍኩትን ነገር ሁሉ ወደሗላ ሳስበው ፣ እኮራበት የነበረው ሀብቴና ዝናዬ ከንቱ እና ትርጉም አልባ እንደሆነ ተረድቻለሁ፥፥
,
,,አንድን ሰው መኪና እንዲነዳልህ ወይም ሰርቶ ገንዘብ እንዲያስገባልህ ልትቀጥረው ትችላለህ፣ እየተሰቃየህበት ያለውን ህመም እንዲሸከምልህ ግን ልትቀጥረው አትችልም፥
,
,, ምድራዊ የሆኑ ቁሳቁሶች ሁሉ ሊጠፉ ፣ዳግም ሊገኙም ይችላሉ፥ አንድ ጊዜ ካመለጠ ደግመህ ልታገኘው የማትችለው አንድ ነገር ግን አለ… እርሱም #ህይወትህ ነው፥
,
አንድ ሰው የቀዶ ጥገና ወደሚደረግለት ክፍል ሲገባ አንብቦ ያልጨረሰው አንድ መጽሃፍ ትዝ ቢለው የመጽሐፉ ርዕስ "ጤናማ ህይወት የመኖር ሚስጥር" የሚል ሊሆን እንደሚችል ጥርጥር የለውም፣
,
; በየትኛውም የህይወት ከፍታ ላይ ብንሆን የህይወታችን መጋረጃ የሚዘጋበትን ቅጽበት ፊት ለፊት የምንጋፈጥበት አንድ ቀን መምጣቱ አይቀርም፣
,
, ለቤተሰብህ፣ለትዳር አጋርህ እና ለጏደኞችህ የፍቅርን ውርስ አስቀምጥላቸው፣
,
, ራስህን ተንከባከብ ፣ ከሌሎች ጋር መልካም ግንኙነት ይኑርህ
,
, እያደግን ስንሄድና የህይወት ትርጉሙ ሲገባን ውድ ሰዓትም አሰርን ርካሽ ሰዓት ፣ ሁለቱም የሚነግሩን ጊዜ እኩል መሆኑ ይገባናል
,
, በኪሳችን ውድ ቦርሳም ያዝን ርካሽ ቦርሳ ፣በውስጡ የሚኖረውን የገንዘብ መጠን አይቀይረውም ፣
,
, የኣንድ ሚሊዮን ብር መኪናም ነዳን የሶስት መቶ ሺህ ብር መኪና ፣የመንገዱ ርዝመት አይቀየርም፣ አቅጣጫውም ያው አንድ ነው፥፥የምንደርሰውም ያው እዚያው ቦታ ነው ፣
,
, ውድ መጠጥም ጠጣን ርካሽ መጠጥ፣ ስካሩና አድሮ የሚያመጣው ራስ ምታት ለውጥ የለውም፣
,
, ሰፊ ግቢ ውስጥ ኖርንም ጠባብ ቤት፣ ብቸኝነቱ ያው እኩል ነው፣
,
…የውስጥ ደስታ በቁሳቁስ እንደማይገኝ ያን ጊዜ ይገባሃል
,
,አውሮፕላን ላይ የክብር ቦታም ተቀመጥክ ወይም ተራ ቦታ ፣አውሮፕላኑ ከተከሰከሰ እኩል ቁልቁል ትወርዳለህ፣
,
እውነተኛው ደስታ የሚገኘው ከቤተሰብህ፣ከጓደኞችህ፣ ከዘመዶችህ ጋር በሚኖርህ ውብ ጊዜኣት ብቻ ነው፥፥
ከእነርሱ ጋር በምታሳልፈው ጊዜ ፣በምትጫወተው ጨዋታ፣ በምትዘምረው መዝሙር፣ በምትስቀው ሳቅ እውነተኛ ደስታን ታገኛለህ ፣
,
5 ሊካዱ የማይችሉ የህይወት እውነታዎች አሉ …
,; ልጆችህ ሀብታም እንዲሆኑ አታስተምራቸው፥፥ ይልቅ እንዴት ደስተኛ መሆን እንደሚችሉ አስተምራቸው፥፥ ሲያድጉ የነገሮች ዋጋ ሳይሆን ጥቅማቸው ይገባቸዋል፣
,
; ምግብህን እንደ መድሃኒት ውሰድ ካልሆነ መድሃኒት እንደምግብ ትወስዳልህ ፣
,
; የሚወድህ ሰው በቀላሉ አይለይህም፣ ከኣንተ ለመለየት 99 ምክንያት ቢኖረው እንኳ መለየት በማይችልባት አንዲት ነገር ላይ ፀንቶ ይቆማል፣
,
;"ሰው ሆኖ በመፈጠር"ና "ሰው በመሆን" መካከል ትልቅ ልዩነት አለ፥፥ ይህ የሚገባቸው ጥቂት ሰዎች ናቸው፥
,
;ስትወለድ ውድ ነበርክ፣ ስትሞትም ውድ ትሆናለህ፣ በመካከል ያለውን ማስተካከል ያንተ ፋንታ ነው፣
,
;በፍጥነት ለመሄድ ከፈለክ ብቻህን ሂድ፣ሩቅ ለመድረስ ከፈለግህ ግን ከሌሎች ጋር አብረህ ተጓዝ ፣
,
;በዓለም ላይ ያሉ ስድስቱ ፈዋሽ ነገሮች የሚከተሉት ናቸው…
የፀሃይ ብርሃን
እረፍት
ስፖርት
ጥሩ ምግብ
በራስ መተማመን እና
ጓደኛ
እነዚህን አጥብቀህ ያዝ፥፥ ደስተኛ ህይወትን አጣጥም!!
https://t.me/Emmausmengdgnch
https://t.me/Emmausmengdgnch
87 views🇩aኒ Revival , edited  07:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 22:21:23 #እኔ_የአለም_ብርሃን_ነኝ
===============================
ዮሐንስ 8 (John)
12፤ ደግሞም ኢየሱስ፡— እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም፡ ብሎ ተናገራቸው።
ወደ ፍጥረት መጀመሪያ ስንሄድ በዘፍጥረት 1:2-3" እግዚአብሔር በቃሉ ይሁን ብሎ የፈጠረው ምድር በአንዳች ምክንያት ይበላሻል (በሰይጣን መውደቅ ምከንያት) ምድርም ባዶ፣ቅርጽ አልባና #በጨለማ ተውጣ ነበር። የእግዚአብሔርም መንፈስ በውሆች ላይ ሰፍፎ ነበር።
እግዚአብሔርም ብርሀን ይሁን ሲል መንፈስ ቅዱስ የተበላሸውን ነገር ማስተካከል መስመር ማስያዝ ምድርን ማስዋብ ከጨለማ ማውጣት ጀመረ።
ይህ በዘፍጥረት 1:3 ላይ የተገለጠው ብርሀን ያልተፈጠረ ፥ የነበረ ፥ መፍጠርና ማስተካከል የሚችል ነገር ሳይሆን ማንነት(person) የሆነ ነው። እግዚአብሔር የሚፈጥረውም ፍጥረት ሲበላሽ የሚያስተካክለውም በዚህ ማንነት በሆነ ብርሃን (በኢየሱስ ክርስቶስ) ነው።
ፍጥረት ሲበላሽ የሚስተካከለው በተፈጠረበት መንገድ ነው።
ይሁን ተብሎ የተፈጠረ ፍጥረት ሲበላሽ የሚስተካከለው ይሁን በማለት ነወ።
እኛም በኀጢአት ምክንያት ማንነታችን ተበላሽቶ ነበር መልክና ምሳሌአችን ተበላሽቶ በእግዚአብሔር መልክ ሳይሆን ኃጥያተኛ በሆነው በአዳም መልክና ምሳሌ ነው የተወለድነው። ሲቀጥል በአየር ላይ በምድር ላይ በውሀ ውስጥ የሚንቀሳቀሰውን ግዛ ተብሎ ስልጣን ተሰቶት ነበር በኃጢአት ምክንያት ስልጣኑን ለሰይጣን አሳልፎ ሰጥቶ ባዶ አደረገን በመጨረሻም ብርሀን ከሆነው አምላክ ርቆ ከሰይጣን ጋር ተባብሮአልና የሰው ልጆች ሁሉ ጨለማ ነበርን ይላል መጽሐፍ ቅዱስ።
ኤፌሶን 5 (Ephesians)
8፤ ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፥ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ፤
ፍጥረት ሲበላሽ የሚስተካከለው በተፈጠረበት መንገድ ነው።
ይሁን ተብሎ የተፈጠረ ምድር ሲበላሽ የሚስተካከለው ይሁን በማለት ነው።ለዛም እግዚአብሔር ብርሃን ይሁን ብሎ አስተካክሏል የሰው ልጅ ግን ይሁን ተብሎ አልተፈጠረምና ይሁን ተብሎ ሊስተካከል አይችልም።
እግዚአብሔር ሰውን ከምድር አፈር ወርዶ አበጀው ይላል ወርዶ የሰራው ፍጥረት ሲበላሽ ወርዶ ነው የሚያስተካክለው ለዛም ነው ይህ ብርሃን የሆነ ጌታ እኛን ለማዳን በባህሪው አምላክ ሆኖ ሳለ መተካከልን እንደመቀማት ሳይቆጥር የባሪያን መልክ ይዞ በኀጢአተኞች መካከል የተገኘው።ስሙ ይባረክ። ሳይጸየፈን ወደ እኛ የመጣ፥ በጨለማችን ላይ ብርሃን ሆኖ የተገለጠ ፥ጨለማችንን ገፎ የህይወት ብርሃን የሆነልን፥ ከጨለማ ወደሚደነቀው ብርሃኑ ያመጣን ፥ዘላለማችንን በድምቀቱ ያስዋበ ፥የማይጨልመው የህይወት ብርሃናችንን የናዝሬቱ ኢየሱስ ነው
ዮሐንስ 1 (John)
4፤ በእርሱ ሕይወት ነበረች፥ ሕይወትም የሰው ብርሃን ነበረች።
5፤ ብርሃንም በጨለማ ይበራል፥ ጨለማም አላሸነፈውም።
ዮሐንስ 1 (John)
9፤ ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሃን ወደ ዓለም ይመጣ ነበር።
ዮሐንስ 8 (John)
12፤ ደግሞም ኢየሱስ፡— እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም፡ ብሎ ተናገራቸው።
ማቴዎስ 5 (Matthew)
14፤ እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም።
ዮሐንስ 12 (John)
46፤ በእኔ የሚያምን ሁሉ በጨለማ እንዳይኖር እኔ ብርሃን ሆኜ ወደ ዓለም መጥቻለሁ።
ኤፌሶን 5 (Ephesians)
8፤ ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፥ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ፤
“በክርስቶስ ፊት እግዚአብሔር የክብሩን ዕውቀት ብርሃን ይሰጠን ዘንድ፣ “በጨለማ ብርሃን ይብራ” ያለው እግዚአብሔር ብርሃኑን በልባችን አብርቶአልና።”
— 2ኛ ቆሮንቶስ 4፥6 (አዲሱ መ.ት).
ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለሁላችንም ይሁን።
የወንጌል እውነት ቤተክርስቲያን ጅማ
https://t.me/Emmausmengdgnch
78 views🇩aኒ Revival , 19:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-18 04:33:05 #ነገአችሁ #በእግዚአብሔር #ተቀድሟል
በዚህ ስዓት ነገ ምን እሆናለሁ
ምን ይገጥመኝ ይሁን
አሁን ከያዘኝ በሽታ እሞት ይሁን
አሁን እየሰራው ያለው ቢዝነስ ነገ ላይ ያከስረኝ ይሁን
ቤተሰቤ ነገ ላይ ይበተን ይሁን .......ወዘተ እያላችሁ ላላችሁ ጌታ እንዲህ ይላል ነገአችሁን እኔ ቀድመሃለሁ ......
“እስከ ሽምግልናችሁ፣ እስከ ሽበትም፣ የምሸከማችሁ እኔ ነኝ፤ እኔው ነኝ። ሠርቻችኋለሁ፤ እሸከማችኋለሁ፤ እደግፋችኋለሁ፤ አድናችኋለሁ።”
— ኢሳይያስ 46፥4 (አዲሱ መ.ት)
አይደለም ነገአችሁን ዘላለማችሁን እሱ አምላካችሁ ይዘዋል
ነገ አትቀጥልም የምለው ሰይጣን ጠላት ነው አትስማው ጌታ አምላክህ ያለውን ብቻ ስማ ነገአችሁ በጌታ ተቀድሟል.....
112 views🇩aኒ Revival , edited  01:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-09 11:06:56 ለምን ይሆን?
አንተ በውድ ሆስፒታል ተወልደህ ይሆናል፣ እኔ በቤት ውስጥ ተወልጄአለሁ፤ ሁለታችንም በህይወት እየኖርን ነው።
አንተ በግል ትምህርት ቤት ተምረህ ይሆናል፣ እኔ በመንግስት ትምህርት ቤት ተምሬአለሁ፤ ሁለታችንም በአንድ ዩንቨርስቲ ጨርሰናል።
አንተ ከምቹ አልጋ ላይ ከእንቅልፍህ ነቅተህ ይሆናል፣ እኔ ከመሬት ላይ፤ ሁለታችንም የሰላም ሌሊት አሳልፈናል።
አንተ የለበስካቸው ልብሶች ውብና ውድ ይሆናሉ፣ የኔ ቀላልና ርካሽ ናቸው፤ ሁለታችንም ራቁትነታችንን ሸፍነናል።
አንተ ብዙ የምግብ ዐይነቶችን ከጥሩ መስተንግዶ ጋር አማርጠህ በልተህ ይሆናል፣ እኔ ቤት ያፈራውን ወስጄ በልቻለሁ፤ ሁለታችንም ግን የምግብ ፍላጎታችንን ለማርካት ስንል ተመግበናል።
አንተ Land Cruser TurboV8፣ Range Rover፣ Lexus Jeep፣ Hummer Jeep ወይንም G Wagon...መኪና ትነዳ ይሆናል፣ እኔ የህዝብ ትራንስፓርት እጠቀማለሁ፤ ሁለታችንም ግን ወደፈለግንበት መዳረሻ ደርሰናል።
ምናልባት ይሄንን ልጥፍ (post) እያነበብክ ያለኸው፤ በSamsung Galaxy 8Edge፣ በiPhone7s+፣ በSony Xperia፣ በGoldvish Le Million ወይንም በVertu Signature Cobra...ስልክህ ታግዘህ ይሆናል፣ እኔ ይህንን የምፅፈው ስክሪኑ በተሰበረ ስልኬ ቢሆን እንኳ ሁለታችንም መልእክቱ እኩል ይታየናል።
ይሀውልህ፤ በአእርግጥ ህይወት የፉክክር መድረክ ነች።ነገር ግን ነገሮችን ለማሳካት ብዙ መንገዶች ቢኖሩ እንኳ ሁሉም የህይወት መስመሮች የሚመሩን ወደ አንድ አቅጣጫ ነው። ይኸውም- ሞት። ደግሞ ደስታ ሁሉንም ነገር በማግኘት ውስጥ አይመጣም፣ ካለህ ነገር ውስጥ መልካሙን በማውጣት እንጂ። ትልቁ ቁምነገር ያለው ራስህን የምታይበት መነጽር ነው። ደስታ ማለት የምትወደውን ማግኘትም አይደለም፣ ደስታ ማለት ያገኘኸውን በቂ ነገር መውደድ ነው። ልብ በል፤ ያንተ በዚህ አለም መኖር የሚያስደስተው ሌላውን ሲሆን አንተን የሚያስደስትህም የሌላው መኖር ነው።
የትላንት ትላንት ምንም አልነበረህም፤ ምንም ሳትይዝ፣ ራቁትህን ነው ይችን ዓለም የተቀላቀልከው፤ ይሁንና ትላንት ያጣኸውን ዛሬ አግኝተሃል፣ ዛሬ ያጣኸውን ነገ ታገኘዋለህ፣ ሁሉንም ደግሞ የነገ ነገ ታጣዋለህ። ባጭሩ አንድ ቀን ሁሉንም ትተህ ትሞታለህ።
ከሞትክ በኋላስ?
ከ3 ቀን በኋላ የጣቶችህ ጥፍሮች መወዳደቅ ይጀምራሉ። ከ4 ቀን በኋላ የራስ ቅልህና ሰውነትህ ላይ ያሉ ጸጉሮች በሙሉ ይረግፋሉ። ከ5 ቀን በኋላ አንጎልህ መርገብ ይጀምራል፣ የሰውነትህ ሥጋ ይጠወልጋል፤ መቀመጫህ፣ ጡትና ኃፍረተ-ስጋህ ይበሰብሳል። ከ6 ቀን በኋላ ቆዳህ መሳሳትና ቀስ በቀስም ከአጥንትህ ላይ መለያየት ይጀምራል። ከ7 ቀን በኋላ ሆድህ ይቀልጣል፣ መጥፎ ጠረንም ማውጣት (radiate ማድረግ) ይጀምራል። ከሞትክ ከ60 ቀን በኋላ መላው የሰውነትህ አካል ወዳልነበር ይለወጥና "አንተ" ማለት "አጥንት" ብቻ ትሆናለህ።
ታዲያ፤
• ለምን ይሆን ይሄ ሁሉ ትእቢት?
• ለምን ይሆን ይሄ ሁሉ ራስ ወዳድነት?
• ለምን ይሆን ይሄ ሁሉ ክርክር፣ ጭቅጭቅና ንትርክ?
• ለምን ይሆን ይሄ ሁሉ ቅናት?
• ለምንስ ይሆን ይሄ ሁሉ ጥላቻ?
• እኮ ለምን ይሆን ይሄ ሁሉ የክፋት ሥራ?
ጥለህ ለምትሄደው አለም?!። እስኪ ለሞት ሩብ ጉዳይ እንደቀረው ሰው እንኑር። ደሃ ሃብታም እያልክ ሳታደላ፣ የተማረ ያልተማረ ብለህ ሳትለይ፣ መልከ መልካም መልከ ጥፉ ሳትል፣ ባለስልጣን ተራ ሰው ብለህ ሳትመርጥ...ሁሉንም በሰው'ነቱ እኩል- ተመልከት፣ ስማ፣ እርዳ፣ አድን የዚህን ሁሉ ህይወት ደመዎዝ ከእግዚአብሄር እጅ ትቀበላለህ

ፍቃዱን ያኑርህ
https://t.me/Emmausmengdgnch
https://t.me/Emmausmengdgnch
136 views🇩aኒ Revival , 08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 19:16:19 ልቤ አንተን ይላል
መንፈሴም ወዳንተ ይገሰግሳል
ጉጉቴ አንተን ማክበር ነው
ፍላጎቴ ክብርህን ማየት ነው

የእኔ ደስታ አንተን ማስደሰት ነው
ዓላማዬ የአንተ ዓላማ ነው
የእኔ ደስታ ደስ ሲልህ ማየት ነው
ዓላማዬ የአንተ ዓላማ ነው

ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ (2x)

ከምትወደው ጋራ እስማማለሁ
የምትጠላው ለኔ ጠላቴ ነው
በመታዘዝ ፍቅሬን እገልጻለሁ
ዝቅ ማለቴ አንተን ከፍ ላደርግ ነው

መኖር ትርጉም ሚስጥሩ አንተ ነህ
እወዳለሁ ዛሬም ልገዛልህ (2x)

ዋላ ወደውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ
ነፍሴ አንተን ተጠማች
ነፍሴ አንተን ተጠማች (2x)

ኢየሱስ…

እንደልብህ ሆኜ ልኑርልህ
ልቤን ትቼ ያየኸውን ልይልህ
መንፈስን ከኔ አትውሰደው
አጥፍ ልስገድ ሁሌም ላገልግለው

ከውሃ ውስጥ እንደወጣ ዓሣ
መኖር አልችልም ተለይቼ ጌታ (2x)

ዋላ ወደውኃ ምንጭ…

ኢየሱስ…
https://t.me/Emmausmengdgnch
https://t.me/Emmausmengdgnch
104 views🇩aኒ Revival , edited  16:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 07:23:12 #ክብሩን #ብቻ
ሁሌም አንድ ነገር መንፈስ ቅዱስን እለምናለሁ የእግዚአብሔር #ክብር ብቻና ብቻ ነው!!!!!
መዝሙረኛው ዳዊት እንዲህ አለ፦
መዝሙር 63
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ አምላኬ፥ አምላኬ፥ ወደ አንተ እገሠግሣለሁ፤ ነፍሴ አንተን ተጠማች፥ ሥጋዬ አንተን እንዴት ናፈቀች እንጨትና ውኃ በሌለበት በምድረ በዳ።
² ኃይልህንና #ክብርህን አይ ዘንድ እንዲሁ በመቅደስ ውስጥ ተመለከትሁህ። አለ በኤዶምያስ ምድረ በዳ ላይ ሆኖ መለመን የነበረበት ከሀረሩ ለማምለጥ ጥላ ከጥሙ ለመረካት ውሃን ከድካሙ ለመበርታት የምበላ ምግብ ነበር ዳዊት ግን እውነተኛ የነፍሱን ራሃብ ምን እንደሆነ ያውቃል እሱም የእግዚአብሔር #ክብርህን !! ጥጋቡ የእርሱ መገኘት ብቻ ነው!!!!
“እኔ ግን በጽድቅ ፊትህን አያለሁ፤ ክብርህን ሳይ እጠግባለሁ።”
— መዝሙር 17፥15
ያንተስ/ያንቺስ ?!!!!!
መንፈስ ቅዱስ በዚህ ዘመን ሰዎች ብዙ ከምመኙት ከምድር ረሃብ ይልቅ የሰማዩን የክብር ራብተኞች እንድትሆኑ ያድርጋችሁ
https://t.me/Emmausmengdgnch
https://t.me/Emmausmengdgnch
116 views🇩aኒ Revival , edited  04:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 12:05:11 Channel photo updated
09:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 09:27:43 #ሰማይ #ባንተ #የሚያየውን
#እንጂ #ሁኔታ #የሚለውን #አትይ
በነፍስ ገዳዩ #ሙሴ
ታላቅ መሪነትን ዘጽ 3 : 7 :10)
ከጣኦት አምላኪው #አብርሃም ውሰጥ
የኪዳን ሕዝብ አባትነትን (ዘፍ 17 : 3 )
በተራና ብላቴና እረኛው #ዳዊት
ውሰጥ ንጉስነትን(1ሳሙ16:1 :13) (
ከማህጸን ሳይወጣ #ኤርምያስ
ውስጥ ነቢነትን ኤር 1 : 4: 10)
በሞተ ሬሳ ውስጥ ጉብዝናን
(ሉቃ 7 : 11 : 15)
በወላዋይና ተሰባሪ #ስምኦን
ውስጥ ጴጥሮስ (አለት)
(ማቴ 16 : 17 : 19)
አገር ባወቃት ሴተኛ አዳሪ ሴት
ውስጥ ሌሎችን በወንጌል
የመድረስ አቅምን (ዮሐ 4 : 1 :43)
በአሳዳጁና አንገላቹ #ሳኦል
ውስጥ ዓለምን በወንጌል
የሚያካልል የሐዋርያት ጸጋና ጥሪ
አገር በረገመው ቀራጩ #ሌዊ
ውሰጥ የማቴዎስ ወንጌል
መጽሐፍን አይቶ የጠራ ጌታ .... በእርሱ እጅ ዋጋ የሌለውና የማይጠቅም አንድም ሰው የለም።... ዛሬ ምናልባት በማንም የማትታወቅ በብዙ አሉታዊ ነገሮች የተከበብክ የእኔ ነገር በቃ ብለህ ለሽንፈትና ለውድቀት እጅ ሰጥተህ ይሆናል ።....... ጌታ ግን ባንተ ውሰጥ አልፎ የሚሰራውን ልዩና ታላቅ ነገር ያያል .... እንደገና መሠራት የማይችል የተበላሸ ማንነት በእግዚአብሔር እጅ ሊኖር አይችልም እርሱ አምላክ የእንደገና አምላክ ነው !!
እጅ አትስጥ አምላክህ ሁሌም ፊተኛ ነው ለጥያቄዎች መልስ ለጨለማው ብርሃን በራሃቡ ዘመን እንጀራ ልያደርግህ ሆስኖአል አረባም አልጠቅምም አትበል አታልቅስ አትዘን አምላክህ አይጥልህም አይተውይም ......
በድል ጌታ ሁሌ የድል ሰው እንደሆንክ ለራስህ ደጋግመህ ተናገር!!!!!
https://t.me/Emmausmengdgnch
https://t.me/Emmausmengdgnch
99 views🇩aኒ Revival , 06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-26 06:17:54 እቺን ለቅምሻ!!!

በህይወታችን ከፍ ያለ ቦታ ለመገኘት ትናንሽ ደረጃዎችን መውጣትና መሰናክሎችን ማለፍ ያስፈልጋል!
እሾህ የሌለው መሬት እንቅፋት የሌለው ሂወት የለም እና ሁሉንም በትዕግስት እንለፍ...

የሰውን ልጅ ቀና የሚያደርገው ትራስ ሳይሆን ጊዜ ነው!!! ሁሌም ቢሆን ፈገግ በል ምክንያቱም ለአንተ እንባ ማንም ሰው ግድ የለውምና !

ከፈጣሪህ በቀር በማንም ላይ ተስፋ አታድርግ አብዛኞቹ ሰዎች በምታስፈልጋቸው ስዓት እንጂ በሚያስፈልጉህ ስዓት አይገኙም

መቼም ቢሆን ተስፋ እንዳትቆርጥ በዝግታም ቢሆን ተራመድ እንጂ በፍፁም ወደ ኋላ እንዳትመለስ።

ወድቆ የሚነሳ ወድቆ ከማያውቅ እጅግ ጠንካራ ነው። ትልቁ የጦርነት ሥፍራ አእምሮ ነው ትልቁ ድል ደሞ ራስን ማሸነፍነው::

እግዚአብሔር ለእናንተ የከፈተውን በር ማንም ሰው መዝጋት አይችልም! ካሳለፍነው የሚመጣው የተሻለ ይሆናል !

መልካም የድል ቀን !!!!!
ባላቹበት ቦታ ሁሉ ሰላማቹ ብዝት ይበልልኝ
ተጨማር ትህምርቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንኩን በመጫን ይከታተሉ

https://t.me/Emmausmengdgnch
https://t.me/Emmausmengdgnch
86 views🇩aኒ Revival , edited  03:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ