Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Electric Utility

የሰርጥ አድራሻ: @eeuethiopia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.33K
የሰርጥ መግለጫ

EEU Official Telegram Channel
Web: www.eeu.gov.et

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2023-02-18 14:20:38
ከ7 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የትራንስፎርመር መልሶ ግንባታ ስራ እየተከናወነ ነው

የአማራ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል መቆራረጥንና መዋዥቅን ለመቀነስ የሚያስችል የትራንስፎርመሮች መልሶ ግንባታ ስራ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡

የትራንስፎርመር መልሶ ግንባታ ስራው እየተከናወነ የሚገኘው በደሴ፣ በሃይቅና በባቲ ከተሞች ሲሆን፣ የግንባታ ስራው ነባሩን ትራንስፎርመር በአዲስ መልክ የመቀየር ስራን የሚያካትት ነው፡፡

ስራውን ለማከናወን 7 ሚሊየን 319 ሺህ 665 ብር ተመድቦ እየተሰራ ነው፡፡ አፈጻጸሙም በአሁኑ ወቅት 41 በመቶ ደርሷል፡፡

የትራንስፎርመር መልሶ ግንባታ ስራ ማከናወን ያስፍለገው ከዚህ በፊት አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩት ትራንስፎርመሮች ረዥም አመት ያገለገሉና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ማርካት ባለመቻላቸው ነው፡፡

የግንባታ ስራው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በከተሞች አካባቢ የሚስተዋለውን የኃይል መቆራረጥና መዋዥቅ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ያስችላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
2.1K viewsedited  11:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 10:23:36
ውድ የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኛችን የተጠቀሙበትን ወርሃዊ የፍጆታ ሂሳብ #ሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያን በመጠቀም ለመክፈል ሲፈልጉ የሚከተሉትን የአጠቃቀም መመሪያዎች ይከተሉ!!

• በመጀመሪያ የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት ባንኮች ላይ ያስጀምሩ፣
• በመቀጠል ባስከፈቱት መስመር ወደ (*889#) በመደወል አገልግሎቱን መጠቀም ይጀምሩ፣
• ቀጥሎ ከመጣልዎት ዝርዝር ውስጥ ቁጥር 1 ላይ የተጠቀሰውን (Login) የሚለውን በመምረጥ send የሚለውን ይጫኑ፣
• በመቀጠል የሞባየል ባንኪንግ የሚስጥር ቁጥርዎትን (Password) በማስገባት send የሚለውን ይጫኑ፣
• ቀጥሎ ከመጣው ዝርዝር ውስጥ በተራ ቁጥር 5 ላይ የተጠቀሰውን (More Options) የሚለውን በመምረጥ send የሚለውን ይጫኑ፣
• ቀጥሎ በመጣልዎት ዝርዝር መሰረት 1 ቁጥር ላይ የተጠቀሰውን (utility payment) የሚለውን በመምረጥ send የሚለውን ይጫኑ፣
• ቀጥሎ በመጣልዎት ዝርዝር መሰረት በተራ ቁጥር 2 ላይ ያለውን (Ethiopian Electric Utility) የሚለውን በመምረጥ send የሚለውን ይጫኑ፣
• በመጨረሻም የራስዎትን Customer Account No በማስገባት የብሩን መጠን እና ስምዎትን በማረጋገጥ ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ ክፍያዎትን መክፈል ይችላሉ፡፡

# የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
2.1K views07:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 09:10:39
የኤሌክትሪክ #አደጋን እንዴት መከላከል ይቻላል?

• ያልተሸፈነ የኤሌክትሪክ ገመድ ወይንም ሽቦ ከመንካት መቆጠብ፣
• የኤሌክትሪክ ሽቦዎች ከቆሮቆሮ አጥር፤ ከልብስ ማስጫ ሽቦዎች ጋር እንዳይገናኙ ማድረግ፣
• ተበጥሶ መሬት ላይ የወደቀን ወይንም የተንጠለጠለን ኤሌክትሪክ ሽቦ ከመንካት መቆጠብና ሪፖርት ማድረግ፣
• በኤሌክትሪክ የተያዘን ሰው ህይወት ከአደጋ ለማዳን የኤሌክትሪክ መስመሩን ከመቆጣጠሪያው ማጥፋት፣
• ውሃ ውስጥ፤ እርጥብ መሬትና ኤሌክትሪክ አስተላላፊ ነገር ላይ ቆሞ የኤሌክትሪክ መሳሪያዎቹን ከመንካት መቆጠብ፣
• ማንኛውም በኤሌክትሪክ የሚሰራ መሳሪያን ለማጽዳትና ለመጠገን ሲያስፈልግ ከኤሌክትሪክ መስመር ማላቀቅ፣
• በኤሌክትሪክ የሚሰሩ መሳሪያዎች ላይ ቃጠሎ ከተነሳ በውሃ ለማጥፋት አለመሞከር፣
• ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ከአንድ ቤት ወደ ሌላ ቤት የሚዘረጋ የኤሌክትሪክ መስመር አደጋ ስለሚያስከትል ከዚህ ድርጊት መቆጠብ፣
• በማንኛውም ቦታና ጊዜ የኤሌክትሪክ አደጋ የሚያስከትል ምልክት ከታየ ወዲያውኑ በአቅራቢያው ለሚገኝ የአገልግሎት መስጫ ማሳወቅ፣
• የኤሌክትሪክ ስራ ሙያን የሚጠይቅ በመሆኑ በቸልተኝነት የሚሠራ ስራ ለህይወትም ሆነ ለንብረት መጥፋት መንስኤ ስለሚሆን መጠንቀቅ አስፈላጊ ነው፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
2.4K viewsedited  06:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-15 14:28:02
ጭፍራ፣ አውራና እዋ ወረዳዎች ዳግም የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆኑ

በአፋር ክልል በከልዋን ዞን የሚገኙት ጭፍራ፣ እዋና አውራ ወረዳዎችና አካባቢዎቻቸው ዳግም የ24 ሰዓት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆኑ፡፡

የወልድያ ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በመዘረፉ ምክንያት ለረዥም ጊዜ አገልግሎቱ ተቋርጦባቸው የቆዩት እነዚህ ወረዳዎችና አካባቢዎቻቸው ከትላንት ጀምሮ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል፡፡

አካባቢዎቹ በአሁኑ ወቅት ዳግም የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የሆኑት የወልዲያ ዶሮ ግብር ባለ 230/33/15 የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት በመጀመሩ ነው፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ በዳሎል፣ በመጋሌ እና በኢሬብቲ ሳተላይት ጣቢያዎች የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡

በቅረቡም ወልዲያ ከተማና አካባቢው፣ ሃራ፣ ድሬሮቃ፣ ሀሮ እና አካባቢዎቻቸው አዳግም የ24 ስዓት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ማግኘት መጀመራቸው መገለፁ የሚታወስ ነው፡፡


#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
1.4K views11:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-15 11:12:25
የስካዳ ቴክኖሎጂ የኃይል ስርጭቱን አስተማማኝና ጥራት ያለው ለማድርግ ፋይዳው የጎላ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተግባራዊ የተደረገው የስካዳ ቴክኖሎጂው የኃይል ማሰራጫ መስመሮችን የኦፕሬሽን ሁኔታን ከአንድ ማዕከል ሆኖ በመከታተል ሊከሰት የሚችለውን ሃይል መቆራረጥና መዋዥቅ ችግር በቀላሉ ለመለየትና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት አስችሏል፡፡

የዲስትረቡሽን መስመር የስካዳ ቴክኖሎጂው በስምንቱ ዋና ዋና ከተሞች ማለትም በአዲስ አበባ፣ በባህር ዳር፣ በደሴ፣ በመቀሌ፣ በአዳማ፣ በድሬደዋ፣ በሀዋሳ እና በጅማ ከተሞች በስራ ላይ የዋለ ሲሆን ሁለተኛው ዙር የስካዳ ቴክኖሎጂ ትግበራ በአዲስ አበባና 50 ኪ.ሜ ራዲየስ የሚገኙ ከተሞች ላይ ተግባረዊ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
2.0K views08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-14 12:01:48
የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት በተዘረጉባቸው አካባቢዎች ግንባታዎችን ማከናወን በህግ የሚያስቀጣ ከመሆኑ በተጨማሪ ለሰዎች ህይወት መጥፋት፣ ለአካል መጉደል እና ለንብረት መውደም ምክንያት እየሆነና በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ላይም አሉታዊ ተፅኖ እያሳደረ ይገኛል፡፡

የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት በተዘረጋባቸው አካባቢ ግንባታዎችን ማከናወን፣ የኤሌክትሪክ ምሰሶዎችን የአጥር አካል አድርጎ ማጠር፣ ንግድ ስራዎችን ማከናወን፣ ሙያዊ እውቀት በሌላቸው ግለሰቦች ማስጠገን፣ ጥራት የሌላቸው የኤሌክትሪክ መገልገያ መሳሪያዎችን መጠቀም፣ ማስታወቂያዎችን መለጠፍ እና ልብስ መስቀል ለከፍ የኤሌክትሪክ አደጋ ይዳርጋል፡፡

ስለሆነም መሰል ድርጊቶችን የምትፈፅሙ አካላት ከድርጊታችሁ እንድትቆጠቡ እያሳሰብን ለኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት በተፈቀደ ወሰን ላይ ግንባታ በምታከናውኑ አካል ላይ አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ የምንገደድ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
3.4K views09:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-13 17:01:41
የሃራ፣ ድሬ ሮቃ፣ ሃሮ ወረዳዎችና አካባቢዎቻቸው ዳግም የኤሌክትሪክ አገልግሎት አገኙ

በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል ተፈጥሮ በነበረው የፀጥታ ችግር የወልድያ ተንቀሳቃሽ የሃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በመዘረፉ ምክንያት ለረዥም ጊዜ አገልግሎቱ ተቋርጦባቸው የቆዩ የሃራ፣ ድሬ ሮቃ፣ ሃሮ ወረዳዎችና አካባቢዎቻቸው ከዛሬ ጀምሮ ዳግም የኤሌክትሪክ አገልግሎት ማግኘት ችለዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት የወልዲያ ዶሮ ግብር ባለ 230/33/15 የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት በመጀመሩ አካባቢዎቹ ዳግም የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል፡፡

በ33 ኪ.ቮ ወጪ መስመሮች የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ የተደረጉት ሀራ፣ ድሬ ሮቃ፣ ሃሮ ከተሞችና አካባቢዎቻቸው ከአንደ አመት ከስድስት ወር በላይ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋርጦባቸው ቆይቷል፡፡

ከወልዲያ ማከፋፈያ ጣቢያ አገልግሎት ያገኙ የነበሩ በአፋር ክልል በከልዋን ዞን የሚገኙ ወረዳዎች ጭፍራ፣ አውራ እዋና አለሌ ዳግም በጥቂት ቀናት ውስጥ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ያገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የወልዲያ ዶሮ ግብር የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ጥር 17 ቀን 2015 ዓ.ም በከፊል አገልግሎት መስጠት በመጀመሩ የወልዲያ ከተማና አካባቢው ዳግም የ24 ስዓት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ማግኘት መጀመራቸው መገለፁ የሚታወስ ነው፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ወቅታዊና ትኩስ የተቋማችን መረጃዎች ወዲያውኑ እንዲደርሳችሁ ድረ-ፃችንን ይጎብኙ: http://www.eeu.gov.et
2.0K viewsedited  14:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-13 12:31:20
ውድ የድህረ-ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞቻችን፤የተጠቀማችሁበትን ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ ቀላልና ምቹ በሆነው #የቴሌ_ብር ሞባይል መተግበሪያ ይክፈሉ፡፡ ደንበኛችን *127# አጭር ቁጥር በመጠቀም ሳይጉላሉና ሳይንከራተቱ ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብዎን ካሉበት ሆነው በቀላሉ በቴሌብር ይክፈሉ፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
2.6K viewsedited  09:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 15:23:25
ውድ ደንበኞቻችን #ነገ_ቅዳሜ የካቲት 4 ቀን 2015 ዓ.ም ዋናው መስሪያ ቤትን ጨምሮ የክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጽ/ቤቶች፣ ዲሰትሪክቶች እና በየደረጃው የሚገኙ የአገልግሎት መስጫ ማዕከሎቻችን ከጠዋቱ 2፡00 እስከ ቀኑ 11፡00 ድረስ አገልግሎት የሚሰጡ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
2.2K viewsedited  12:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 14:45:57
የኤሌክትሪክ ሃይል ሳያስሞሉ #ለረዥም ጊዜ መጠቀም ለተጠራቀመ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ የሚዳርግ መሆኑን ያውቃሉ? እንግዲያውስ እናሳውቅዎ !! አንዳንድ #የቅድመ ክፍያ ቆጣሪዎች ቴክኒካልና ቴክኒካል ባለሆኑ ምክንያቶች ከተሞላላቸው የኤሌክትሪክ ሃይል መጠን በላይ ለረዥም ጊዜ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሊያስጠቅሙ ይችላሉ፡፡

ይሁን እንጂ ተቋሙ የሲስተም ተጠቃሚ በመሆኑ ቆጣሪው ሃይል እየተሞላለት መሆንና ሳይሞላ የቆየበት የጊዜ ቆይታ ሲስተም ላይ ስለሚታይ ችግሩ በተገኘ ጊዜ ደንበኞች ሲጠቀሙ የቆዩበት #የተጠራቀመ የፍጆታ ሂሳብ ክፍያ ከእነ አገልግሎት ክፍያው እንዲከፍሉ ይገደዳሉ፡፡

ክቡራን የቅድመ ክፍያ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቻችን ሃይል ሳያስሞሉ ለረዥም ጊዜ መጠቀም ለተጠራቀመ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ የሚዳርግ መሆኑን አውቃችሁ የቆጣሪ ካርድ በየወሩ እንድትሞሉና የቆጣሪ ቴክኒካል ችግር ካጋጠማችሁ በአቅራቢያችሁ በሚገኝ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል በአካል በመሄድ ሪፖርት እንድታደረትጉ እናሳስባለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
2.1K viewsedited  11:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ