Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Electric Utility

የሰርጥ አድራሻ: @eeuethiopia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.33K
የሰርጥ መግለጫ

EEU Official Telegram Channel
Web: www.eeu.gov.et

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-02-28 11:21:21
ውድ የድህረ-ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞቻችን፤ የተጠቀማችሁበትን የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ ተቋሙ በዘረጋቸው ዘመናዊ የክፍያ አማራጮች በመጠቀም ይፈፅሙ፡፡ #ዘመናዊ የክፍያ አማራጮችን መጠቀም አስፈላጊ ካልሆነ ወጪና እንግልት ያድናል! ኑሮንም ያቃልላል! በጥሬ ገንዘብ ለመክፈል ወደ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በመምጣት ጊዜዎትን፣ ጉልበትዎትንና ገንዘብዎትን አያባክኑ፡፡ ካሉበት ሆነው በተዘረጉ ቀላልና ዘመናዊ የክፍያ አማራጭ ብቻ ይጠቀሙ!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


ዝርዝር መረጃዎቻችን ለማግኘት ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
4.1K viewsedited  08:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-27 13:00:00
የጋና ኤሌክትሪክ ኩባንያ የስራ የኃላፊዎች የልምድ ልውውጥና ምርጥ ተሞክሮ እያከሄዱ ነው

የጋና ኤሌክትሪክ ካምፓኒ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒግ ፕሮግራም የአሰራር ስርዓት ትግበራ ዙሪያ የልምድ ልውውጥና ምርጥ ተሞክሮ ቅመራ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ፡፡

በመረሃ-ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አውቶሜሽንና ኢነርጂ ማኔጅመንት ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ ደመቀ ሮቢ ተቋሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶችን በመገንባት በመላ ሃገሪቱ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን እውን በማድረግ ላይ መሆኑንና የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል አዳዲስ ቴክኖሎጀዎችን በስራ ላይ እያዋለ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ም/ስራ አስፈጻሚው አክለውም ተቋሙ የኢ.አር.ፒ የአሰራር ስርዓት ተግባራዊ ማድረጉንና በዚህም በርካታ አሰራሮችን ማዘመን መቻሉን ገልፀው፤ ይህ ፕሮግራም ሁለቱም ተቋማት ለሃገራቸው ህብረተሰብ የኤሌክትሪክ ተደራሽ በማድረግ ረገድ ያካበቷቸውን ተሞክሮዎች ለመቀያየር ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡

በጋና ኤሌክትሪክ ኩባንያ የልዩ ፕሮጀክቶችና ፕሮግራሞች ጀነራል ማናጀር የሆኑት ኢንጂነር ፓትሪስ አፌንዮ በበኩላቸው ኩባንያቸው በጋና ከፍተኛውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅራቢ ተቋም መሆኑን ጠቅሰው የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን የኢ.አር.ፒ ቴክኖሎጂን ከቅርብ አመታት ወዲህ ስራ ላይ ማዋሉን ተናግረዋል፡፡

የተሞክሮና ልምድ ልውውጥ ፕሮግራሙ ከዛሬ ጀምሮ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ይሆናል፡፡


#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
568 views10:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-25 16:57:31
በአዲስ አበባና በዙሪያዋ ለምትገኙ ደበኞቻችን በሙሉ

የተቋማችን 905 ነጻ የጥሪ ማዕከል በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከሚስተዋሉ ችግሮች ጋር የተያያዙ ጥቆማዎችን ለመቀበል የተቋቋመ የጥሪ ማዕከል ነው፤ ይሁን እንጂ ነገ እሁድ የካቲት 19 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 በዋናው መ/ቤት የዲዝል ጀነሬተር ጥገና ስለሚከናወን አገልግሎት መስጠት የማይችል መሆኑንን እየገለፅን፤ የዲዝል ጀነሬተር ጥገና ስራው እስኪጠናቀቅ ድረስ በትግዕስት እንድትጠባበቁና ከሃይል መቆራረጥ፣ ከፍጆታ ሂሳብ ክፍያ እንዲሁም ሌሎች ከአገልግሎት አሰጣጡ ጋር የተያያዙ ችግሮች ካጋጠማችሁ በአቅርቢያችሁ ወደ ሚገኙ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል በአካል በመሄድ ቅሬታችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
167 viewsedited  13:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-25 13:24:11
ከመደበኛ የስራ ስዓት ውጪ አገልግሎት መሰጠት መጀመሩ የሚበረታታ መሆኑ ተገለፀ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአዲሱ በጀት ዓመት ከመደበኛ የስራ ስዓት ውጪ ቅዳሜ ግማሽ ቀን ነጻ የስራ ዘመቻ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ የሚበረታታ መሆኑን ደንበኞች ገልፀዋል፡፡

ዛሬ ቅዳሜ የካቲት 18 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሰሜን ዲስትሪክት ስር በሚገኙ ቁጥር 1፣ 3 አና 4 አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ሲገለገሉ ያገኘናቸው ደንበኞች እንደገለፁት ተቋሙ ቅዳሜን እንደ መደበኛ የስራ ቀን የአገልግሎት መስጠት መቻሉ ለተገልጋዮች ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል፡፡

በተለምዶው ሰሜን ቀለበት መንገድ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኘው ቁጥር 3 የአገልግሎት መስጫ ማዕከል በመገኘት ካርድ ሲሞሉ ያገኘናቸው ወ/ሮ ሙሉ በለጠ እና ወ/ሮ እናትነሽ ተፈራ እንደገለፁት በእረፍ ቀናቸው በማዕከሉ አገልግሎት ማግኘት መቻላቸው ከዚህ በፊት አገልግሎት ለማግኘት ይባክን የነበረውን መደበኛ የስራ ሰዓት ለስራቸው እንዲያውሉ እንደረዳቸው ጠቁመዋል፡፡


ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
1.3K viewsedited  10:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 09:43:57
በሃይል አጠቃቀም ችግርና ምክንያት ሊከሰት የሚችለውን የሃይል ብክነት ለመከላከል ኃይል ቆጣቢ የሆኑ የኤሌክትሪክ መገልገያ ዕቃዎችን ይጠቀሙ፣ የኤሌክትሪክ መጠቀሚያ ዕቃዎችን ኃይል ቆጣቢ መሆናቸውን ያረጋግጡ፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ለረዥም ጊዜ ያገለገሉ የኤሌክትሪክ ምጣድ፣ ምድጃ፣ ማሽን እና ሌሎች የኤሌክትሪክ መገልገያ ዕቃዎችን በአዳዲስ በመቀየር እና የኃይል ጭነት በማይበዛበት ጊዜ ማለትም ከምሽቱ 3 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12 ሰዓት በመጠቀም ሊኖር የሚችለውን የሃይል ብክነት በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ ይችላሉ፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
2.6K views06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 11:12:34
ከ116 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመካከለኛ መስመር መልሶ ግንባታና ማስፋፊያ ስራ እየተከናወነ ነው

የአማራ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ116 ሚሊየን ሦስት ሺህ 709 ብር በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ ከተሞች ላይ የመካከለኛ መስመር መልሶ ግንባታና ማስፋፊያ ስራ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡

የመካከለኛ መስመር መልሶ ግንባታ የሚከናወነው ከሚሴ እስከ ቦሩ ሃራዋ፣ ከመሃልሜዳ እስከ ዘመሮ፣ ከባህር ዳር እስከ አዴት፣ ከሊብሶ ጎራርባ ወረቃሉ እስከ ዉርጌሳ፣ ከሐሮ እስከ ድሬሎቃ እና ከብቸና ሰብስቴሽን እስከ የዕድ ውሃ ባሉ አካባቢዎች በተዘረጉ መስመሮች ላይ ነው፡፡

እንዲሁም የመካከለኛ መስመር ማስፋፊያ ከኮምቦልቻ ሰብስቴሽን እስከ ካርቪኮ፣ ከሞጆ ሰብስቴሽን-እጀሬ፣ ከእጀሬ እስከ አረርቲ፣ ከጣና በለስ ሰብስቴሽን እስከ ቁንዝላ ባሉ ቦታዎች ላይ ነው፡፡

ፕሮጀክቱ በሶስተኛ ወገን አማካኝነት እየተከናወነ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ 149 ነጥብ 95 በኪ.ሜ መዘርጋት ተችሏል፡፡

የመካከለኛ መስመር መልሶ ግንባታና ማስፋፊያ ስራ መከናወኑ በከተሞቹ ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አስተማማኝና ቀልጣፋ አገልግሎት ከማድረጉም ባሻገር የማህበረሰቡን የእለት ተእለት ኑሮና የከተሞቹን የእድገት ለማሻሻል የሚያግዝ ፕሮጀክት ነው፡፡

በተጨማሪም ለኢንዱስትሪ፣ ለውሃ ልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ለሚሰጡ ተቋማት መስፋፋት አይነተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል፡፡

ከስድስት ወር በፊት የተጀመረው ይህ የመካከለኛ መስመር መልሶ ግንባታ ፕሮጀክት 72 ነጥብ 45 ፐርሰንት እንዲሁም የማስፋፊያ ስራው ደግሞ 86 ነጥብ 28 ፐርሰንት ተጠናቋል፡፡ በተያዘው በጀት አመትም ስራው ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ ይጎብኙ፡- http://www.eeu.gov.et
2.2K viewsedited  08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-22 11:47:48
ውድ #የድህረ_ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኛችን የተጠቀሙበትን ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ ክፍያ ከዚህ በፊት በሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ተቋሙ በዘረጋቸው ዘመናዊ የክፍያ አማራጮች ይፈፅሙ! ከዚህ በተጨማሪም ወርሃዊ የቆጣሪ ንባብ እየተወሰደ መሆኑን ያረጋግጡ! የቆጣሪ ንባብ ካልተወሰደ ለተጨማሪ ውዝፍ እዳ የሚዳርግ በመሆኑ ወቅቱን የጠበቀ ንባብ መወሰዱን ያረጋግጡ፤አለመነበቡን እርግጠኛ ከሆኑ በአቅራቢዎ ለሚገኙ የደንበኞች አገልግሎት መስጫ ማዕከል በመሄድ ያሳውቁ፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ ይጎብኙ፡- http://www.eeu.gov.et
1.6K views08:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 11:01:20
ውድ የድህረና ቅድመ ክፍያ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቻችን ለማሻሻያ ስራ ስለሚቋረጥ የሃይል አቅርቦት፣ የፍጆታ ሂሳብን እና ሌሎች ተቋሙን የሚመለከቱ መረጃዎችን ተደራሽ ለማድረግ ያመች ዘንድ የደንበኞቻችን ስልክ ቁጥር እና የኢሜል አድራሻ መሰብሰብ አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል፡፡

ስለሆነም ከዚህ በፊት ስልክ ቁጥር ያስመዘገባችሁ የኢሜል አድራሻችሁን እንዲሁም ያላስመዘገባችሁ ደግሞ ስልክ ቁጥራችሁን እና የኢሜል አድራሻችሁን መልዕክቱ ከተላለፈበት ቀን ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በአካባቢያችሁ በሚገኝ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል በአካል በመሄድ እንድታስመዘግቡ በአክብሮት እንጠይቃለን ፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
2.2K viewsedited  08:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 10:48:03
የቡሪ ቀበሌ ነዋሪዎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ የሚያድረግ የግንባታ ስራ በመከናወን ላይ ነው

በአፋር ክልል በዞን አንድ ስር በምትተዳደረው ቡሪ ቀበሌ ለሚገኑ አንድ ሺ ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ግንባታ ስራ በመከናወን ላይ ነው፡፡

በከተማው በመካሄደ ላይ የሚገኘው ግንባታ የተጀመረው በተያዘው በጀት ዓመት ጥር ወር መጀመሪያ ላይ ሲሆን በአሁኑ ወቅት አፈፃፀሙ 16 በመቶ ደርሷል፡፡

የቀበሌውን ነዋሪ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተከናወነ በሚገኘው በዚህ ግንባታ ሶስት ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር እና 27 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር ግንባታ የሚከናወን ሲሆን አምስት ትራንስፎርመሮች የሚተከሉ ይሆናል፡፡

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአፋር ክልል አገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ፕሮግራም እየተከናወነ የሚገኘው ይህ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ግንባታ በአሁኑ ወቅት 155 የዝቅተኛ መስመር ምሰሶዎች ተከላ ተከናውኗል፡፡

የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ግንባታው በመንደሩ ያለ የጤና ጣቢያ እና መሰል በግንባታ ላይ የሚገኙ የአገልግሎት መስጫ ተቋማትን ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላል፡፡፡፡

በ7.4 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚከናወነው ይህ ግንባታ በበጀት ዓመቱ ሰኔ መጨረሻ ላይ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡


#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
2.2K viewsedited  07:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 10:37:46
ውድ #የድህረ_ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኛችን ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታዎን በቴሌ ብር ለመክፈል የሚከተሉትን ቅደም ተከተሎች ይጠቀሙ

በመጀመሪያ ወደ *127# በመደውል የቴሌ ብር ደንበኛ ይሁኑ፤ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆኑ ካረጋገጡ በኋላ ከታች ያለውን መመሪያዎች ይጠቀሙ፡፡
1. መልሰው ወደ *127# ይደውሉ፣
2. ከሚያመጣሎት መዘርዝር # በማስገባት ምላሽ ይስጡ፣
3. በመቀጠል ቁጥር 7 በማስገባት በቴሌ ብር ለመክፈል ብለው ምላሽ ይስጡ፣
4. በቴሌ ብር ለመክፈል በሚል ዝርዝር ከሚቀርብሎት መዘርዘር የአገልግሎት ክፍያ ለመፈፀም የሚለውን አማራጭ ቁጥር 2 ይምረጡ፣
5. በድርጅት ስም የሚለውን ለመምረጥ 1ን ያስገባሉ፣
6. 1ን በማስገባት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚለውን ይምረጡ፣
7. ከዛም የውል ቁጥሮን ማለትም ደረሰኝዎ ላይ ያለውን /Contract Account Number/ (10000*******) የሚለውን ያስገቡ፣
8. ለማረጋገጥ 1ን የሚለውን ያስገቡ፣
9. ምክንያትዎን ያስገቡ፣
10. በመጨረሻም የሚስጥር ቁጥርዎን ያስገባሉ፣

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et
1.1K views07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ