2022-08-27 20:13:49
ከጀናዛ ማጠቢያ ክፍል ቁ • 30
በአስራዎቹ እድሜ ውስጥ የሚገኝ ቁርአንን በአግባቡ የሀፈዘ ለጋ ወጣት ነው ወደ መስጂድ መመላለስ ያዘወትራል። በጠና ታመመና ወደ ማይቀርበት ጉዞ ሞት ሄደ። አጎቱ ነበር የሚያስታምመው የሞተውም ማታ ስለነበር ለቤተሰብ እየደወለ መሞቱን አሳወቀ። አጥበው ለመቅበር ንጋትን በመጠባበቅ ላይ ናቸው። አጎቱ እንቅልፍ አሸነፈውና አሸለበ። ታሪኩን በአንደበቱ ይቀጥልልናል :- « እንቅልፍ እንዳሸለበኝ በህልሜ ዱንያ ላይ አይቼው የማላውቀውን ውበት የተላበሰች እንስት ወደኔ አቅጣጫ መጣችና «ይህንን ልጅ አጥበህ ቅበርልኝ ከሞተበት ሰአት ጀምሮ እሱን በመጠበቅ ላይ የምገኝ የጀነቷ እንስት ነኝ በአላህ ይሁንብህ ባሌን በፍጥነት አጥበህ ቅበርልኝ» በማለት በጆሮዬ አስተጋባች።
ከእንቅልፌ በድንጋጤ ነቃሁ የቤቱ ሽታ በመልካም ጠረን ተሞልቶ ያውዳል። ጀናዛውን በማጠቢያው እንጨት ላይ ዘርግቼ ጓደኞቼን ጠርቼ ማጠብ ጀመርኩ። በመሀል መብራት ጠፋ። ከጓደኞቼ መካከል አንዱ ባትሪ ሊያመጣ ወጣ። በዚያ ድቅድቅ ጨለማ ጀናዛው ያበራ ጀመር ቤቱ አብረቀረቀ።
«አላህ ብርሀንን ያላደረገለት ሰው ለርሱ ብርሀን የለውም።»
እባክዎ ለወዳጅ ዘመድዎ ሼርና ፎርዋርድ በማድረግ ያዳርሱ የሰዎች የተውበት ሰበብ በር ይሁኑ
በቻናላችን በሚሰጡ ትምህርቶች ተሳታፊ ለመሆን ይህን ይጫኑና ጆይን ይበሉ
https://t.me/shekalidarashid
https://t.me/shekalidarashid
1.9K views., 17:13