Get Mystery Box with random crypto!

Deinstein_21

የቴሌግራም ቻናል አርማ deinstein_21 — Deinstein_21 D
የቴሌግራም ቻናል አርማ deinstein_21 — Deinstein_21
የሰርጥ አድራሻ: @deinstein_21
ምድቦች: ጥቅሶች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.98K
የሰርጥ መግለጫ

@Deinstein_21
.
.

Contact👉0913617275 and 0964742005 or @Albetredeinstein

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2022-12-27 19:31:33 #ውይ_እኛ_ማለት_እኮ


በህይወታችን ግድ ሊሰጠን የማይገባን ከሁሉም በላይ ግድ የሚሰጠን ግራ የገባን ፍጥረቶች ነን እኮ
የሚተላለፍ ድራማ ዘገየ ወይም አልተላለፍም ብለን የምናዝን : የዝነኞቻችን ፍችና ጋብቻ የሚጨንቀን የሚጠበን : እከሌ እኮ ሰላም ያላለኝ ስለሚንቀኝ ነው የምንል : የሜሲ የአለም ዋንጫ ማሸነፍ የሚያስቧርቀን ብቻ ምን አለፋቹ የራሳችን እያረረብን የሰው የምናማስል እኛ እኮ ነን::
እና ይገርማችኃል ... ገረማቹህ አልገረማቹህ የራሱ ጉዳይ ... ይሄው አሁን እንዴት እንደዚህ ትላለህ ብለህ ይተናደድህ ነው ... የራሱ ጉዳይ ነገሩ እራሱ .... ትንሽ ሞቅ ላድርግህ ብየ ነው :: ለማንኛውም እናም ይህ የሰው ይሁን የሀበሻ ብቻ የሆነ ባህሪ ተጋላጭ ነበርኩ ነገር ግን ግድ እንዳይሰጠኝ ስል ብቸኛ ሰው በመሆን ማንም ካጠገቤ ድርሽ ሳላደርግ ለአስራ አመታት ኖርኩ እናም የሚያስፈልገኝን እንጂ የምፈልገውን ለማድረግም ሆነ ለመፈለግ አልሞክርም ነበር ::: እናም ከብቸኝነቴ ጋር ውል የሌለው ትዳር ያዝኩና መኖር ስጀምር ይሄው እንደ ሌሎች ግድ የማይሰጣኝ ሰው ሁኜው አረፍኩ እላችኃለው ...... ከዚያም ምን የተፈትጠረ ይመስላችኃል ..... ምንም ስለዚህ ግድ ሰጣችሁም አልሰጣችሁም ትኖራላች ስትሞቱም ትሞታላቹ እዚህ አለም ላይ የናተ ሃላፊነት እራሳችሁን በራሳቹህ አለማሰናበታቹህ ብቻ ነው ሌላው እንደ ሌሎቹ ናቹህ ....... ስለዚህ እኛ እኮ ገራሚ ፍጥሮች ነን



አዲስ አበባ - cmc ሚካኤል
12/04/2015
ማታ 1:30

የጨነቀው ሃሳብ ብየዋለሁ


◉ Join us share◉●••
═════❥━━━❥═════
ነገን ላየው እጓጓለሁ!!! https://t.me/Deinstein_21
120 viewsedited  16:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-26 19:48:22

"ዋናው ጥያቄ ሀቅ ምንድነው ናት እውነትስ ምንድነው ተፈጥሮስ ከየት መጣ አደለም። ዋናውና አንገብጋቢው ልኑረው / ልሙተው ነው።

~ሌላዎቹ ጥያቄዎች ለመኖር ከወሰንኩ የምደርስባቸው ናቸው።

እኔ አሁን አየኖርኩ ነው ያለሁት

ካለመኖር ወደ መኖር ስነቃ ከልጅነት ወደ አዎቂነት ስነቃ እየኖርኩ ነው ያለሁት።

~ስለዚህ መኖሩን ልቀጥልበት ነፃ ምርጫ ወስጃለሁ።

~ስኖር ደግሞ በነፃነት ነው በባርነት ከመኖር ለነፃነት ብዋጋላት መርጣለሁ።
79 views16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-26 14:41:41 #ለወረት_የዘንድሮ_ፍቅር_ባፍንጫዬ_ይውጣ
የመሬት ስበትና ኤሌክትሮማግኔቲዝም የመሳሰሉ የተፈጥሮ ታላላቅ ሃይሎች ከስሜታችን የተሰወሩ ቢሆንም ጉልበታቸው ግን የማያከራክር ነው። በተመሳሳይ የፍቅር ሃይል ከእይታችን የተሰወረ ቢሆንም ከሌሎች ተፈጥሯዊ ሃይሎች ሁሉ በእጅጉ ይልቃል። የሃያልነቱ አሻራም በመላው ዓለም ተሰራጭቶ ይገኛል።ያለፍቅር ህይወት አይኖርም።

እንደመላዕክት ክንፍ ቢኖረኝ እንኳን ፍቅር ከሌለኝ ከንቱ ነኝ የሚለውን የሐዋሪያውን ቃል ሰምቼ ካልገባሁበት ያልኩት ፍቅር ለካስ እራሱን የቻለው መስፈረት አለው።
ፍርሃትን ለማሸነፍ ፍቅር ሃያል ነው ለዚህም ጌታችን እና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው። ሞትን ድል የነሳው በፍቅሩ ነው። እያንዳንዱን የፍራት ካብ ለመናድ ፍቅር ትልቅ ሃይል ነው። ሴት የላከው ጅብ አይፈራም ይባል አይደል። ብቻ ምን ልበላቹ ፍቅር እራሱን የቻለ የማይታይ ሃይል ነው። ይሄን ያህል ስለ ፍቅር ካልን ፍቅር መስፈርት እንዳለው ስንቶቻቹ ታውቃላችሁ?
ፍቅር ትልቅ የሆነ መስፈርት አለው እሱም “መብሰል” ይባላል። በፍቅር ውስጥ መብሰል ከሌለ መርዛማ ይሆን እና ወደ ፍጹም ጥላቻ ይቀየራል። ይሄን ሃሳብ ትንሽ ልበትናት መስሰል። ለምሳሌ ፦ ሰይጣን በመጀመሪያ የአምላክን ዙፋን ከመመኘቱ በፊት ፍቅር ነበረው ያምፍቅር ጌታው ያስቀመጠለት ሲሆን ሳጥናኤል ሁኖ እንዲገኝ አደረገው ነገር ግን ያልበሰል ፍቅር ስለነበረው እኔ ነኝ አምላክ ብሎ ሳታ ለምን አምላክ የመሆን ፍቅሩ ሃይሎ ስለነበረ ባልበሰረ አምዕሮው እንዲዋሽ እና እንዲኪድ አደረገው። ከዚያም ያፍቅር ወደ መርዝነት በውሸት ምክንያት ተቀይሮ በስተመጨረሻም በእሱና በአምላኩ መካከል ጠላችነትን ፈጥሮ በፍቅር የተጀመረው ጥንስስ በጥላቻ ተጠናቀቀ እላችኋለሁ ይህም ጥላቻ እስካሁን እንደ ቀጠለ ነው። ሌላ ያልበሰለ ፍቅር ታሪክ እምንዘዝ እስኪ ከሐዋሪያው ዮሃንስ በስተቀር ሌሎች በጌታቸው ስቅለት (መያዝ) በሰሙ ጊዜ ሸሹ ነገር ግን ከሰዓታት በፊት እነ ቅዱስ ጴጥሮስ በአምላካቸው ፍቅር ተነድፈው እኔ እሆን እንዴ እያሉ አምላካቸውን እየጠየቁ ነበር። ቢሆንም ግን ያልበሰለ ፍቅር ስለነበረ አምላኩን አላውቅውም ብሎ በመካድ ፍቅሩን ወደመርዛማነት አሳደገው ነገር ግን የአምላኩ ፍቅር የበሰለ ስለነበረ። እራርቶለት ጴጥሮስን እና ሌሎች ሃዋሪያት ጥላቻ ውስጥ አምላካቸው ጋር ሳይገቡ እናም ተለያዩ ።
እስኪ የበሰለውን ፍቅር እንይ …..ይበሰለው ፍቅር ለእኔ የኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን መብሰሉን ስለፍቅር ሲል ዝምታን መረጠ ፍቅር የህግ መጨረሻ መሆኑን ለማሳይወቅ እስከ መጨረሻው ደቂቃ ድረስ ምንም ሳይናገር የሚረጉትን እየመረቀ ሲመቱት ምንም ሳይመልስ አለፈ። የመብሰልን አስፈላጊነት ሲነግረን በዝምታው ውስጥ የሌሎችን ጥላቻ እሱ ግን በፍጹም ፍቅር መለሰ የነሱንም የፍቅር ምላሽ አልፈለገም ከመትረፍረፍ የወጣ ፍቅር ስለነበረ ሁሉን እንደ ታረ ቆጠረው።
እና ወደተነሳሁበት የዘንድሮ ፍቅር ስመጣ ፍቅር እንደ ሳጥናኤል የሆነ ነገርን በመፈልግ ላይ የተመሰረት እና ከስሜት ብቻ የሚነዳ በመሆኑ እንዲሁም እንደ ሐዋሪያት በችግር ጊዜ የሚሸሽ፣ ልታይ ላታይ የሚወድ እና አንዱ አንዱን መማማለን በሱ ቁጥጥር ስር በማድረግ ለመጫወት የሚሞክርበት ነው። ……እና እኔም ለምን ይቀርብኝ ብየ የገባሁበት የዘንድሮ ፍቅር ተመርዞ ወደ ዘላለማዊ ጥላቻ ሳይቀየር ባቆመዉስ አይሻልም ትላልቹ።

ነገር ግን ወደዱ አፍቅሩ የጥንቱን ፍቅር ካገኛችሁት እንደዛ ስትባሉ ደግሞ ተጃጃሉ አሏቹ።
ያለፍቅር ህይወት አይኖርም። አፍቅሩ አፍቅሩ ነገር ግን ከእናተ እና ካላማቹ በኋላ አምላካችሁን እያስቀደማችሁህ።

8:40 ቀን
አዲስ አበባ - ቦሌ
17/04/2015

◉ Join us share◉●••
═════❥━━━❥═════
ነገን ላየው እጓጓለሁ!!! https://t.me/Deinstein_21
63 viewsedited  11:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-25 21:00:14 አሁን ያሉ እውቀቶች የሰውን ውስንነት የሚናገሩ
መሰለኝ፡፡

የሚሰብኩ ልበለው?. . .
አንድ ተማሪ
አንድ ኤክስ ገባበት፡፡

ለምን? ብዬ ሳየው ኤክስ
የገባበት ማር ጣፋጭ አይደለም ብሎ ስለመለሰ
ነበር፡፡

እንዴት እንዲህ ብለህ መለስክ አልኩት .
. . እኔ ስለማልወድ ጣፋጭ አይመስለኝም፤
ማርን ስበላው ጣፍጦኝ አያውቅም አለኝ፡፡

ጣፋጭና መራራ ከዚህ ልጅ ስሜት ጋር አብረው
ሄደዋል፡፡

አሁን ለዚህ ልጅ እኔ አስተማሪው
ብሆን ኤክስ ከማድረግ ይልቅ እራሴን
እጠይቃለሁ. . . ለመሆኑ መራራና ጣፋጭ
እንድንል ያደረገን ስሜታችን? ቋንቋችን? ወይስ
ስምምነታችን? ፡፡

ቋንቋ ባይኖር ኖሮ ሰው
መራራና ጣፋጭ ብሎ ስያሜ ይሰጠው ነበር?
ስሜት ከተለያየስ ስምምነት ይኖራል? ሰው
መማር ያለበት ስሜቱን ተፈጥሮውን ወይስ
ስምምነቱን?. . .
ያ ህፃን ግን አያሳዝንም?
የቱንስ እንመን?

የተፈጠርንበትን ያንን? ወይስ
ያስተማሩንን እነርሱን? እነርሱን ከሆነ እንደ ፓሮት
ወይም በቀቀን ሲሉን ስንደግም ልንኖር እኮ ነው.

◉ Join us share◉●••
═════❥━━━❥═════
ነገን ላየው እጓጓለሁ!!! https://t.me/Deinstein_21
52 viewsedited  18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-25 14:52:28 #ዛሬን_በደምብ_መኖር እፈልጋለሁ_ቢሆንም_ነገን_ላየው እguaguaለሁ *

የ ዛሬን አለመኖር ቅንጣት ስህተቶች ነገየን እንደሚያበላሹት አውቃለሁ.
ግን ማድረግ ያለብኝን እያወኩ ማድረግ መቻል ይከብደኛል
ሆኖም ንጉሡን ከመለመን እናቱን ከ ማገልገል ተቆጥቤ አላውቅም.
ነገየ surprise እንደሆነ ይሰማኛል
ነገሬን, ሃሳቤን ለመናገር ቃላት አይኖሩኝም. ጫፉን ለመናገር ስሞክር ማንም አይገባውም . ቀውስ ነሽ ይሉኛል. እኔም በራሴ ዓለም ብቻዬን እኖራለው.
ኪዳነምህረት ካለች ምን ሆናለሁ..
ለ ሁሉም ስብሐት ለእግዚአብሔር ወ ለወላዲቱ ድንግል...

3:30 Am
ኪዳነምህረት church
16/04/15Ec.

Cc- ከቤተሰቦቻችን

◉ Join us share◉●••
═════❥━━━❥═════
ነገን ላየው እጓጓለሁ!!! https://t.me/Deinstein_21
139 views11:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-24 23:29:54 #ይህን_ስቃይ_በጣም_እወደዋለሁ
አንዳንዴ ተናገሬ በወጣልኝ ብየ አስባለሁ ነገር ግን ለመነገር ስሞክር ቃላቶቼ ሃይል አጠው በአንደበቴ ውስጥ በጉሮሮየ ላይ ይጣበቃሉ። አንዳንዴ ዝምታዬ ከቃላቴ በላይ ሃይል እንዳለው ይሰማኛል። ስላ ለሁበት ደረጃ እንዳለቅስ ዝምታዬ ጉልበቴ ይሆነኛል በዝምታዬ ውስጥ ለአምላኬ ምን እነግረው ዘንድ ሃይል ይኖረኝና እንባዬ የልቤን መቃተት ይናገርልኛል። እሱም ሳልነገረራቸው የሰማቸውል። የእባዬ ጉልበት ከአንደበቴ በላይ ጉልበት ኑሮት አምላኬ ጆሮውን ወደ እኔ እንዲያዘነብ ያደረዋል። የአንደበቴን የቃላን ጉልበት ዝምታዬ ከእንባዬ ጋር ይበልጥ ይናገርልኛል። አንዳንዴ ዝምተኝ ነኝ ነገር ግን የአንድበቴ ቃላት ከዝምታዬ ይቀድማል በዚህ ሁሉ ድካሜ ሁሉ ግን የአማላኬ እናት ከእኔ ጋር ናት ሞቴን ወደ ህይወት ትቀይረዋለች ። እናም እላችኋለሁ እንዲህ ግራ የገባኝ ነኝ አንዳንዴ ብቻ። ከሁሉ በላይ ዛሬም ነገም ከተሰጠኝ ነገር ሁሉ እንደ አምላኬ እናት ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም በላይ ስጦታ የለኝም ስለዚም እሷ ሁሉ ነገሬ ናት። ከሷ ውጭ እስካሁን ድርስ በህይወት አልገኝም ነበር ። ምንም ግራ የገባኝ ቢሆንም ይህን ስቃዬን እወደዋለሁ። ለማንኛውም ሁሌም በሃዘኜም ሆነ በደስታዬ ውስጥ እግዚአብሔር ሁልግዜም ይመስገን ።


ተመስገን ሁልጊዜም

ታህሳስ 15-2015
ከምሽቱ 11:13
AASTU ቤተ-መጽሃፍ
◉ Join us share◉●••
═════❥━━━❥═════
ነገን ላየው እጓጓለሁ!!! https://t.me/Deinstein_21
49 viewsedited  20:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-23 11:06:34

50 views08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-22 22:55:00 ህይወትህ ይህ ነው እስከምትረዳው ድረስ ይጠባበቅህ የነበረው።እስከአሁን አስቸጋሪና ትግል እንደሆነ አድርገህ አስበህ ይሆናል።በስበት ህግ መሠረትም ያሰብከውን አይነት ህይወት ልትኖር ትችላለህ።አሁኑኑ ለዓለም"ህይወት እጅግ ቀላል ነው።ህይወት እጅግ ጥሩ ነው።ጥሩ ነገሮች ሁሉ ያጋጥሙኛል"ብለህ ጮክ ብለህ ለእራስህ ተናገር።በውስጥህ እንድታገኘው እየጠበቀ ያለ አንድ እውነት አለ።ይህም እውነት"ህይወት መስጠት ያለባትን ጥሩ ነገር ሁሉ ታገኛለህ"የሚል ነው።ይህን ጉዳይ ሲጀመርም ታውቀዋለህ።ምክኒያቱም መልካም ነገር ሳያጋጥምህ ሲቀር የሚሰማህን አለመመቸት ታውቀዋለህና ነው።ጥሩ ነገሮች የተፈጥሮ መብቶችህ ናቸው።አንተ የራስህ ፈጣሪ ነህ።የስበት ህግ በህይወትህ የምትፈልገውን ለማግኘት የሚረዳህ መሳሪያ ነው።ወደ ህይወትህ የምትፈልገውን ለማግኘት የሚረዳህ መሳሪያ ነው።ወደህይወት ሚስጥርና ወደ ራስህ ሉአላዊነት እንኳን ደህና መጣህ።
"ሚስጥሩ"
በጎነት የህሊና ምግብ ነው!!!
https://t.me/zezereyaakob
39 views19:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-22 22:29:48 "ቂም "

ታህሳስ 12 በዛሬው ዕለት የተደረገ ተአምር!

አቡነ ዘርአ ቡሩክ

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ!

ተወዳጆች ሆይ ኢትዮጵያዊው ፃድቅ ባለ 12 ክንፉ አባታችን አቡነ ዘርአ ቡሩክ ከእለታት አንድ ቀን በቅዱስ ሚካኤል በአል ታህሳስ 12 ቀን እግዚአብሔር ነፍሳትን ከሲኦል እንዲያወጡ አዘዛቸው። አባታችንም የፈጣሪያቸውን ትእዛዝ ተቀብለው ወደ ሲኦል ወረዱ። ወደ አስፈሪው ሲኦል ገብተው በእሳት ሰንሰለት ለዘመናት በሰይጣን የታሰሩትን ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ነፍሳት አገኙ።

ፃድቁም የእሳቱን ሰንሰለት በፈጣሪያቸው ስልጣን ፈተው እነዛን ምስኪን ነፍሳት ከስቃይ አወጧቸው። ግን አንድ አሳዛኝ ነገር ተመለከቱ። በሲኦል የተናቀች እና የወደቀች የአንድ የደግ መምህር የኤዎስጣቴኦስ ደቀ መዝሙር ስሙም አብሳዲ የሚባል ነፍስ ሰም ከፈትል እንደሚጣበቅ ተጣብቃ በሲኦል ባህር ውስጥ ስትሰቃይ አገኟት።

አቡነ ዘርአ ቡሩክም ያቺን ነፍስ "እግዚአብሔር በዚህ የስቃይ ቦታ የጣለሽ በምን በደልሽ ነው" አሏት። ያቺም ምስኪን ነፍስ "በጥቂት ነገር እግዚአብሔር በዚህ የመከራ ቦታ ጣለኝ ኃጥአቴም ""ቂም ""
ናት" አለቻቸው። አባታችን አቡነ ዘርአ ቡሩክም "በዚህ በመከራ ቦታ ምን ያህል ዘመን ኖርሽ" አሏት።

ምስኪኗ ነፍስም "በዚህ በመከራ ቦታ ከተቀመጥኩ 500 ዘመን ሆኖኛል" አለቻቸው። አባታችንም ይህን ነገር ከዚያች ነፍስ ሰምተው አዝነው "ከቅዱሳን ጋር በገነት ትኖሪ ዘንድ ነይ ውጪ" አሏት"

ያን ጊዜ ከሞት ጉድጓድ አውጥተው በዚያች ቀን ከሲኦል ከወጡት ነፍሳት ጋር በእግዚአብሔር ፊት አቆሟ። እግዚአብሔርም ያችን ነፍስ በፃድቁ ቃል ኪዳን በገነት ውኃ ተጠምቃ ከገብበት መውጣት፣ ካገኙ ማጣት ከሌለባት ገነት እንደገባች ድንቅ ገድላቸው ይነግረናል።

ቸል የምንለው ቂም ምንኛ የነፍስ እዳና ፍዳ እንደሚያመጣብን፣ ለዓመታት በሲዖል እንደሚያኖረን ልብ እንበል ። ፃጻድቁ የአቡነ ዘርአ ቡሩክ ጸሎት እና በረከት አይለየን።

ታህሳስ 112-4-15 ዓ.ም
አዲስ አበባ
67 views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-20 11:06:16 ፍቅር የእግዚአብሔር ሕግ ነው፤



ሚርዳድ - ፍቅር የእግዚአብሔር ሕግ ነው። የምትኖሩት ፍቅርን ትማሩ ዘንድ ነው። የምታፈቅሩትም መኖርን ትችሉ ዘንድ! ለሰው ልጅም ከዚህ ውጪ ሌላ ትምህርት አያሻውም።

ማፍቀር ማለትስ ምንድነው፣ አፍቃሪ ተፈቃሪውን ለዘለዓለሙ ወደ ራሱ ስቦ ሁለቱ አንድ እንዲሆኑ እንጂ?

ደግሞስ ... ማንን ወይም ምንን ይሆን ማፍቀር የሚገባ? እውን ከሕይወት ዛፍ ቅጠሎች አንዷን መርጦ ልብ ያጋተውን መላውን ፍቅር ማዝነብ ይገባ ይሆን?

ግና፣ቅጠሉን ያፈራው ቅርንጫፍ፣ ቅርንጫፉን የያዘው ግንድ፣ ግንዱን ያቀፈው ቅርፊትስ ? ቅርፊት፣ ግንዱን፣ ቅጠላ ቅጠል፣ ቅርንጫፎቹን የመገቡት ስሮችስ? ስሮቹንስ ያቀፈው አፈር? አፈሩንስ ያለማው ፀሐይ? ውቅያኖስ ... አየሩስ?

ዛፍ ላይ ያለች ትንሸ ቅጠል፣ ለፍቅራችሁ ከተገባች፤ መላ ዛፉን ምን ያህል እጥፍ ትወዱት!? ከእጠቃላዩ ነጥሎ አንዱን ክፋይ የሚወድ ፍቅር፣ ራሱን ለሐዘን አጭቷል ቀድሞ ነገር!

እናንተ ግን፣ “ከአንድ ዛፍ ቅርንጫፍ እንኳ፣ እልፍ አእላፍ ቅጠሎች አሉ...

አንዳንዱ ጤነኛ፣ አንዳንዱ ታማሚ፤ ገሚሱ ቆንጆ ሌላው አስቀያሚ።

ከፊሉ ግዙፍ ከፊሉ ድውይ፣ አማርጦ መውደድ አይገባም ወይ?”

ስትሉ ሰማሁ...

እኔ ግን እንዲህ እላችኋለሁ፣

ከታማሚው መጠውለግ ነው የጤነኛው ትኩስነት የሚመነጭ። እናም እንዲህ እላችኋለሁ፣ አስቀያሚነት የውበት መኳያዋ፣ ቀለም እና ብሩሿ ነው። ኧረ ለመሆኑ፣ ድውዩ ቁመቱን ለለግላጋው ባይሰጥ ለግላጋው መለሎ የሚሆን ይመስላችኋል? ነገን ላየው እጓጓለውሁ
@deinstein_21
cc- ምንጭ ፦ መፅሀፈ ሚርዳድ
ፀሀፊ ፦ ሚካኤል ኔይሚ
ትርጉም ፦ ግሩም ተበጀ
164 viewsedited  08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ