Get Mystery Box with random crypto!

የዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ deaconhenokhaile — የዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች
የቴሌግራም ቻናል አርማ deaconhenokhaile — የዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች
የሰርጥ አድራሻ: @deaconhenokhaile
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 64.23K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ፈቃድ ትምህርቶች የሚለቀቁበት ነው::
@deaconhenokhaile
"ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን"
2ኛ ቆሮ. 2:14

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-08-05 01:42:17 + ጻድቅ ሆኖ ተመለሰ +

አባ ፕሮፎርዮስ እንዲህ ሲሉ ገጠመኛቸውን ያስታውሳሉ ፦

‘በጥምቀት በዓል ሰሞን ውኃው ተጸልዮበት ከተባረከ በኋላ ለካህናት ወደ ሰዉ ቤት መሔድና ጠበል መርጨት የተለመደ ሥርዓት ነው፡፡ የሆነ ዓመት ላይ ይህንን ጠበል እየረጨሁ ምእመናንን ለመባረክ ከቤተ ክርስቲያን ወደ መንደር ወጥቼ ነበር፡፡ በየቤቱ በር አንኳኳና ‘አመ ተጠምቀ እግዚእነ በዮርዳኖስ...!’ /ጌታ በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ.../ እያልሁ እያዜምሁ እገባለሁ፡፡

ብዙ መኖሪያ ቤቶች ወዳሉበት መንደር እንደዘለቅሁ አንድ በብረት በር የተዘጋ ትልቅ ጊቢ ጋር ደረስሁ፡፡ ከፍቼ ዘልቄ ገባሁ ፤ ጊቢውን የሞላውን መንደሪን ፣ ሎሚና ብርቱካን የተተከለበት የአትክልት ሥፍራ አልፌ ቀጥ ብዬ ገባሁ፡፡ ሕንጻው ወደ ምድር ቤትና ወደ ላይኛው ፎቅ የሚያስወጡ ሁለት ደረጃዎች አሉት፡፡ ወደ ላይ ወጥቼ አንዱን በር ሳንኳኳ አንዲት ሴት ብቅ ብላ በሩን ከፈተች፡፡ ‘አመ ተጠምቀ እግዚእነ በዮርዳኖስ...!’ ብዬ ማዜም ስጀምር በፍጥነት አስቆመችኝ፡፡ ይሁንና ድምፄ በደንብ ተሰምቶ ስለነበር ከግራ ከቀኝ ካሉት ክፍሎች ውስጥ ወጣት ሴቶች ወደ ኮሪደሩ ብቅ ብቅ ማለት ጀመሩ፡፡ ነገሩ ገባኝ ፤ ‘አሃ ዘልዬ የገባሁት ለካ መሸታ ቤት ከሚሠሩ ሴቶች ቤት ኖሯል?’ አልኩኝ በሆዴ፡፡

‘እባክዎን ይሒዱ አባ’’ አለች ቀድማ የወጣችው ሴት ‘እነዚህ ሴቶች መስቀል መሳለም የሚገባቸው አይደሉም ፤ እኔን ያሳልሙኝና ቶሎ ይሒዱ’ አለች በችኮላ፡፡

ኮስተር አልኩና ‘ካህን ነኝ ቤቱን ሳልባርክ አልሔድም’ አልኳት
‘እሱን ይችላሉ እነዚህ ሴቶች ግን መስቀሉን አይሳለሙም’ ብላ ፍርጥም አለች፡፡

‘መስቀሉን መሳም የሚገባው አንቺ ሁኚ እነርሱ በምን እናውቃለን? እግዚአብሔር መስቀሉን መሳለም የሚገባው ማን ነው ብሎ እኔን ቢጠይቀኝ ኖሮ መስቀል መሳለም የሚገባው ለአንቺ ሳይሆን ለሴቶቹ እንደሆነ በነገርሁት ነበር፡፡ ምክንያቱ ከምትመጻደቂው ከአንቺ ይልቅ የእነርሱ ነፍስ ትሻላለች’ ብዬ ገሠጽኋት፡፡ ደንግጣ ዝም አለች ፤ እኔም ሴቶቹን ወደ እኔ እንዲመጡ ጠራኋቸው፡፡

ከዚያም ‘‘አመ ተጠምቀ እግዚእነ በዮርዳኖስ...!’ እያልኩ ከመጀመሪያው በበለጠ ኃይል መዘመር ቀጠልሁ፡፡ እግዚአብሔር ወደ እነዚህ ምስኪን ነፍሳት እንድመጣ እንዳመቻቸልኝ ስላወቅሁ ውስጤ በደስታ ተሞልቶ ነበር፡፡

ሁሉም መስቀሉን ተሳለሙ፡፡ ሁሉም ያጌጠ ልብስ ለብሰው ሊወጡ ተዘጋጅተው ነበር፡፡ እንዲህ አልኳቸው ፦ ልጆቼ እግዚአብሔር ይባርካችሁ ፤ እግዚአብሔር የሚወደው ሁላችንንም ነው፡፡ እርሱ መልካም ነውና ለኃጢአተኞችም ለጻድቃንም ዝናምን ያዘንባል፡፡ እርሱ የሁላችን አባት ነውና ለሁላችን ይጨነቃል፡፡ ከእኛ የሚጠበቀው ወደ እርሱ መምጣት እርሱን መውደድና መልካም መሆን ብቻ ነው፡፡ እርሱን ውደዱ ምንኛ ደስተኛ እንደምትሆኑ ታያላችሁ’’

በመደነቅ ይመለከቱኝ ነበር ፤ በተጨነቀች ትንሽ ነፍሳቸው ውስጥ የሆነ ነገር እንደቀረ ያስታውቅ ነበር፡፡

‘እናንተን ለመባረክ እግዚአብሔር ዛሬ ወደዚህ ቤት የመምጣትን ክብር ስለሠጠኝ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ’ አልኳቸው፡፡ ለመሔድ ስነሣ ‘እግዚአብሔር ለዘላለም ይባርካችሁ’ አልኳቸው ፤ ‘አሜን አባ’ ብለው በአንድነት መለሱ ፤ ጉዞዬን ቀጠልሁ፡፡


ይህንን አጭር ታሪክ በኦርቶዶክሱ ዓለም እጅግ ተወዳጅ ከሆኑ እጅግ ውብ መጻሕፍት አንዱ ከሆነው ‘Wounded by Love ፤ The Life and the Wisdom of Saint Porophyrios’ ከተሰኘው የአንድ መነኩሴን ሕይወት የሚተርክ ድንቅ መጽሐፍ ነው፡፡




ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ‘እግዚአብሔር በጽድቁ ከሚመካ ጻድቅ ይልቅ ስለ ኃጢአቱ የሚያለቅስ ዘማዊን ይወድዳል’ ይላል፡፡ በእርግጥም ራስን አጽድቆ የሌላውን ሰው ኃጢአት የማሰብን ያህል ኪሳራ በክርስትና ሕይወት የለም፡፡ ሰው ወደ እግዚአብሔር የሚቀርበው የሌሎች ሰዎችን ኃጢአት ሲቆጥር ሳይሆን የራሱን በደል ሲቆጥር ነው፡፡ ነቢዩ ዳዊት ‘እኔ መተላለፌን አውቃለሁና ኃጢአቴም ሁልጊዜ በፊቴ ነውና’ እንዳለው እግዚአብሔር ኃጢአትህ ተሰረየችልህ የሚለው ሰው የራሱን ኃጢአት ዘወትር የሚያስብ ሰው ነው፡፡

የነነዌው ቅዱስ ማር ይስሐቅ ‘መላእክትን ከሚያይ ሰው ይልቅ የራሱን ኃጢአት የሚያይ ሰው ይሻላል’’ ይላል፡፡ ባለ በገናው ‘እባክህ ጌታዬ ሥጠኝ መስታወት ፤ የሰው ሥራ ትቼ የእኔን አይበት’ እንዳሉ የራሱን በደል ማየት ከሚችል በቀር ይቅርታን የሚያገኝ የለም፡፡ ለብዙዎቻችን ከራሳችን ይልቅ የሰው ጉድፍ ማውጣት ይቀልለናል፡፡ ሰው ሆኖ ሌላ ሰውን ኃጢአተኛ ነህ የማለትን ኃጢአትና ትዕቢት ግን የለም፡፡ የሰዎችን ድክመት ባየን ጊዜ ከመሳደባችን በፊት እኛ ከዚያ ሰው በኃጢአት ብዛት በምንም እንደማንሻል ማሰብ አንደበታችንን ይሰበስብልናል፡፡

አባ ሲድራስ የተባለ አባት አንድ ወጣት መነኩሴ የወይን ፍሬ ሰርቀሃል ተብሎ ከገዳም ሲባረር አይቶት ተከትሎት ወጣ፡፡ አባታችን ወዴት ትሔዳለህ ሲሉት ‘እሱ ወይን ሰረቆ ከተባረረ እኔ የሠራሁት በደል ብዙ ነውና አብሬው ብወጣ ይሻላል ብዬ ነው’ አለ፡፡ በዚህም ምክንያት መነኩሴውን ከመባረር አዳኖታል፡፡ ወዳጄ እኔና አንተ በወንድማችን የምንፈርደው ከእርሱ የባሰ የተሸሸገ በደል ተሸክመን መሆኑን አንርሳ፡፡ ‘እኔ እንኳን ብዙ ኃጢአት የለብኝም’ የምንል ከሆነ ግን በድሏል ካልነው ሰው የከፋ ለንስሓ መንገድ የሌለው በደል ውስጥ ነን፡፡ እግዚአብሔር ሊያድነን የሚችለው ከምናምነው ኃጢአታችን እንጂ ከመመጻደቃችን አይደለም፡፡

በወንጌል ጌታችን ከተናገራቸው ታሪኮች እጅግ የተዋቡት ምንባባት ኃጢአታቸውን ያልደበቁና ያልተመጻደቁ ኃጢአተኞች ታሪክ ነው፡፡ የዘኬዎስ ፣ የባለ ሽቱዋ ማርያም ፣ ልትወገር የነበረችው ሴት ወዘተ ታሪኮች ኃጢአታቸውን አምነው ይቅርታ ያገኙ ሰዎች ታሪኮች ናቸው፡፡ ከእነዚህ አንዱ ታሪክ ስለ አንድ ቀራጭ ይናገራል፡፡ በቤተ መቅደስ ፈሪሳዊውና ቀራጩ ጎን ለጎን ቆመው ይጸልያሉ፡፡

ፈሪሳዊው በእግዚአብሔር ፊት ቆሞ እንኳን ራሱን ዝቅ አያደርግም፡፡ አፉን ሞልቶ ጽድቁን ያወራል፡፡ ጽድቅን ተናግሮ የሚገኝ ነገር ያለ ይመስል ‘እጾማለሁ ፣ ዐሥራት አወጣለሁ’ እያለ ይመጻደቃል፡፡ አልፎ ተርፎ ‘እንደ ሌላ ሰው ሁሉ፥ ቀማኞችና ዓመፀኞች አመንዝሮችም፥ ወይም እንደዚህ ቀራጭ ስላልሆንሁ አመሰግንሃለሁ’ ብሎ የቀራጩን ኃጢአተኝነት ለእግዚአብሔር አሳሰበ፡፡ ወዳጄ ሺህ ጊዜ በጎ ብትሠራ እንዲህ አደረግሁ ያልህ ቀን ዋጋ ታጣለህ ፣ ስለ ሌሎች ሰዎች ኃጢአት ማውራትና ማሰብ እስካልተውህ ለእኔ ፈሪሳዊ ነህ እያለን ነው መሐሪው ጌታ፡፡

ቀራጩ ግን ‘‘በሩቅ ቆሞ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ሊያነሣ እንኳ አልወደደም፥ ነገር ግን። አምላክ ሆይ፥ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ እያለ ደረቱን ይደቃ ነበር እላችኋለሁ፥ ከዚያ ይልቅ ይህ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመለሰ’’ ይላል ጌታችን፡፡ በእውነት እንዴት ያለ ቃል ነው፡፡
27.0K views , 22:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-03 01:58:28 ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሠሯት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስትያን እናምናለን


23.4K views , 22:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-02 19:42:50 ከፀሐይ አጠገብ የነበረው ኮከብ

የአምላክ ሰው መሆንና ተወልዶ የማደጉ ዜና ሲነገር ሁልጊዜም የሚዘነጋ ክብሩ ግን ከብዙ ቅዱሳን ክብር የሚበልጥ አንድ ታላቅ ሰው ዛሬ በልቡናዬ ውል አለ፡፡ መቼም ከፀሐይ አጠገብ ያለ ኮከብ በፀሐይ ብርሃን ምክንያት መሸፈኑ አይቀርምና በተወለደው የጽድቅ ፀሐይ ፣ የሰላም ንጉሥ በልደቱ ደስታ ተውጠን ፣ በገብርኤል ብሥራት ፣ በድንግል ምስጋና ፣ በመላእክት ዝማሬ ተስበን የዘነጋነውን ፣ ድምቀት ሳያንሰው የተሸፈነውን ኮከብ የቅዱስ ዮሴፍን ነገር ባሰብኩኝ ጊዜ ክብሩን ለመናገር ልቡናዬ ተጨነቀ፡፡

በቅድስናው እያመንን ፣ ውለታውንም እያወቅን የምንዘነጋውን ምናልባትም አንዳንድ ሰዎች የድንግል ማርያምን ዘለዓለማዊ ድንግልና ለማቃለል ስሙን በክፉ ማስረጃነት ሲያነሱብን ከእነርሱ ሸሸን ብለን ሳናውቅ ከበረከቱ የሸሸነውን ጻድቅ ዛሬ ልዘክረው ብል ልቤ በጥፋተኝነት ስሜት ተጨነቀብኝ፡፡

ስለ እርሱ ብዙ ያልዘመርንበትን ፣ ብዙ ያልተቀኘንበትን ዘመን ሳስብ ‘ላዕከ ማርያም ቅዱስ ዮሴፍ ሆይ ስለረሳንህ ቀኛችን ትርሳን ፣ ስላላሰብንህም ምላሳችን ከትናጋችን ይጣበቅ’ ብዬ ይቅርታውን ለመለመን ተመኘሁ፡፡

ቅዱስ ዮሴፍን ማን ብለን እንጥራው? እርሱ እንደሆን እንደ አብርሃም ዘመዶቹን የተወ አማኝ ፣ እንደ ይስሐቅ የታዘዘውን ብቻ ያደረገ ትሑት ፣ እንደ ያዕቆብ በእምነት ግብጽ የወረደ ስደተኛ ነውና እርሱን ለመግለፅ እንደምን ያለ ቋንቋ እንጠቀም ይሆን?

እስቲ ንገሩኝ? ‘መልካሙን እረኛ’ ክርስቶስን የጠበቀውን እረኛ ቅዱስ ዮሴፍን ከቶ በምን ቃል እንገልጸዋለን? የአብን ልጅ ያሳደገውን (ሐፃኔ ወልደ አብ) ቅዱስ ዮሴፍን በምን ቅኔ እናወድሰው?

ሕዝቅኤል ያያትን የእስራኤል አምላክ ገብቶባት ለዘላለም የተዘጋችውን ደጅ የጠበቀውን ታማኝ ዘብ ፤ ‘ከበሩ ደጀ ሰላም መንገድ በዚያ ይገባል በዚያም ይወጣል’ ተብሎ የተነገረለትን የተዘጋችው በር ደጀ ጠኚ ፣ ከታላቅዋ ተራራ ከድንግል ማርያም ያለ ሰው እጅ ድንጋይ ተፈንቅሎ ሲወርድ ቆሞ የተመለከተውን የሐዲስ ኪዳኑን ዳንኤል ከቶ እንዴት ባለ ቃል እንገልጸዋለን?

በቤተ ልሔም ግርግም ውስጥ በላምና አህያ መካከል የተኛውን ሕፃን የተመለከተውንና እንደ ነቢዩ ዕንባቆም
‘በማዕከለ ክልዔ እንስሳ ርኢኩከ’ /በሁለት እንስሳ መካከል አየሁህ/ ሊል የሚቻለውን የቅዱስ ዮሴፍን ክብር በምን አቅማችን እንግለጸው?

ወደ ግብጽ ወርዶ ለወገኖቹና ለዓለም ሁሉ ምግብን እንዳቆየው የብሉይ ኪዳኑ ዮሴፍ ወደ ግብጽ በመከራ ተሰድዶ የሕይወት እንጀራ ክርስቶስን ለሁላችን ላቆየልን ጻድቅ እንዴት ያለ የምስጋና ቃል እናዋጣ?

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

ለቅዱስ ዮሴፍ ዝክር ሐምሌ 26
ከብርሃን እናት ገፆች የተቆረሰ
(ወተዘከረኒ ለኃጥእ ገብርከ ተክለ ማርያም )
25.5K views , 16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-01 22:41:47 ++ አባቶቻችን እንዲህ አሉ ++

"መካሪ አያስፈልገኝም የማለትን ያህል ታላቅ ትዕቢት የለም"
ቅዱስ ባስልዮስ

"በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ ተስፋ ቆርጠህ ጸሎትህን እንዳታቆም። ንስሓ እስከምገባ ድረስ ብለህ ጸሎት ካቆምክ መቼም ንስሓ አትገባም። ምክንያቱም ጸሎት ራሱ የእውነተኛ ንስሓ መግቢያ በር ነው" ቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊ

"ሰዎች አንድ ሰው ተነሥቶ ሌላውን ሲገድል ወንጀለኛ ነህ ይሉታል። አንድ ላይ ተሰባስበው ብዙ ሰዎችን ሲገድሉ ግን ውጊያ ይሉትና መግደላቸውን ጀግንነት ይሉታል" ቅዱስ ቆጵሮሳዊ

"የክርስቲያኖች መሣሪያ በእጃቸው ሰይፍን መታጠቅ ሳይሆን እጃቸውን ወደላይ ለጸሎት መዘርጋት ነው"
ቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ

"እግዚአብሔር ለአብርሃም "ከሀገርህ ውጣ ከወገኖችህ"ተለይ ብሎት ነበር። በዚህ ጥሪ እግዚአብሔር ሁላችንንም የተወለድንበት ዘር እንድንተው ይጠራናል። ሰማዕቱ ዮስጦስ (100 AD-165 AD)

"ክርስቶስ ጴጥሮስን "ሰይፍህን ወደ ሰገባው አስገባ" ሲለው ትጥቅ ያስፈታው ጴጥሮስን ብቻ ሳይሆን እንደ ጴጥሮስ በእርሱ የሚያምኑትን ሁሉ ነበር" ሊቁ ጠርጡለስ (160 AD - 220 AD)

‹‹ይጸልያል ነገር ግን የሌሎችን ጸሎትም ይሰማል፡፡ ያለቅሳል የሌሎችን ዕንባ ግን ያብሳል፡፡ ሰው ነውና አልዓዛር ወዴት እንደተቀበረ ጠየቀ፡፡ አምላክ ነውና አልዓዛርን ከሞት አስነሣ፡፡ እርሱ በርካሽ ዋጋ ያውም በሠላሳ ብር ብቻ ተሸጠ፡፡ ነገር ግን ዓለምን በውድ ዋጋ በከበረ ደሙ ገዛ፡፡ እንደ በግ ለመታረድ ተነዳ እርሱ ግን የእስራኤል እረኛ የዓለምም ሁሉ ጠባቂ ነበረ፡፡ እንደ በግ ዝም አለ ነገር ግን እርሱ በምድረ በዳ በሚጮኽ ሰው ድምፅ የተሰበከ ቃል ነበር፡፡ እርሱ የተሰቃየና የቆሰለ ነበር ፤ ሁሉንም በሽታና ቁስል ግን ይፈውስ ነበር›› ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ

"ለቤተ መቅደስህ ተክል ያደረግኸኝ፡፡ አቤቱ ሆይ የውጭ ተክል አታድርገኝ፡፡ የጽድቅ ተክል አድርገኝ፡፡ የኃጢአት አይደለም፡፡ የዕውነት ተክል አድርገኝ የሐሰት አይደለም የፍቅር ተክል አድርገኝ የጽል አይደለም፡፡
የመጻሕፍት መጀመሪያ የምትሆን ኦሪት ደመና የምትጋርደኝ፡፡ ከቅዱስ ወንጌል ፈሳሽ የምጠጣ ከጎንህ ከፈሰሰው ደም የምረካ ልሁን፡፡ በናትህ በድንግል ጸሎት የሃይማኖት አበባ ላብብ፡፡ የጽድቅ ፍሬን ላፍራ ከቅዱሳንህ ሐዋርያትም ከቃላቸው ፍሬ የተነሣ እስከ ዘለዓለሙ ድረስ የተባረከ የወይን ቦታ ልባል የጽድቅን ፍሬ የሚያስቀረውንም የኃጢአት እሾህ ጠምዝዘው ከደጁም አሜከላውን አረሙንም ሙጃውንም ንቀለው፡፡ አቤቱ ከኔም አርቀው ሥርዓትህን የሚሠሩትን ያበባቸውን ፍጻሜ እንዳፈራ አድርገኝ" ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
28.5K views , 19:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-26 19:29:25 የሉቃስ ወን ጌል ተከታታይ ትምህርት ክፍል አምስት| ፭|
[የጌታ መላአክ]
በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ



https://t.me/deaconhenokhaile
https://t.me/deaconhenokhaile
https://t.me/deaconhenokhaile
33.6K views , 16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-26 19:25:47 የሉቃስ ወንጌል ተከታታይ ትምህርት ክፍል {፲}
+ሕዝቡም ይጠብቁት ነበር +
በመምህር ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
27.8K views , 16:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-21 12:27:11 ለአራት ቀናት ብቻ ለሞተው አልዓዛር ያለቀሰ ጌታ ለዘመናት በኃጢአት ለሞትን ለእኛ ምንኛ ያለቅስ ይሆን? ሰውነታች በበደል ለረከሰ ፣ በምኞት መቃብር ለተቀበርን ፣ በዝሙት ለተበላሸን ፣ በጥላቻ ለሸተትን ለእኛ ክርስቶስ ምንኛ ያለቅስ ይሆን? የኃጢአት ድንጋይ ተጭኖን ፣ የፍትወት መግነዝ ተጠምጥሞብን ላለን ለእኛ የጌታ ዕንባ ምን ያህል ይፈስስልን ይሆን? አልዓዛርስ ውጣ ቢባል ይወጣል ፣ ካለንበት ኃጢአት መቃብር መውጣት ለማንፈልግ ለእኛ ጌታ እንደምን ያለቅስ ይሆን? የእኛ ሞት ከአልዓዛር ሞት በላይ ዘልቆ የማይሰማው ይመስላችኋል? እንዴት አይሰማውም? ለአልዓዛር ዕንባውን ያፈሰሰው ጌታ ለእኛ እኮ ያፈሰሰው ደሙን ነው ።
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
16.8K views , 09:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-19 09:26:32 ስድብ ኃጢአት ባይሆን ኖሮ መሰደብ የሚገባው ዲያቢሎስ ነው:: ፍጥረት ሁሉ ስድብ ቢያዋጣ ለዲያቢሎስ የሚመጥን አይሆንም:: የክፋት ምንጭ ለሆነ ለእርሱ ሁሉም ክፉ ቃል መገለጫው ነው::
ይሁንና ቅዱስ ሚካኤል ይህንን ክፉ ጠላት ደፍሮ አልሰደበውም:: "እግዚአሔር ይገሥጽህ!" አለው:: (ይሁ 1:9)

እንደ ሚካኤል ንጹሕ በእኛ ዘን ማን አለ? እንደ ዲያቢሎስስ ክፉ በእኛ ዘንድ ማን አለ?

መልእክቱ ግልጽ ነው:: አንሆንም እንጂ እንደ ሚካኤል ንጹሕ ብንሆን እንኳን እንደ ሰይጣን የከፋን ሰው እንኳን መሳደብ አንችልም::

የመላእክት አለቃ ሚካኤል ከሥልጣኑ የወረደውን የቀድሞውን የመላእክት አለቃ ዲያቢሎስን አንድም ክፉ ቃል አልተናገረውም:: አንዱ ከሥልጣኑ ወድቆ ሌላው ሲሾም አዲሱ ተሿሚ ስለወደቀው ምን እንደሚል እናውቃለን:: አንደበቱ ስድብ በመናገር ያልረከሰው ቅዱስ ሚካኤል ግን ወድቆ በማያርፈው ዲያቢሎስ ላይ የስድብን ቃል አልተናገረም::

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
Deacon Henok Haile
የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ ጸልዩ! ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like እና Share ያድርጉ
FB: https://www.facebook.com/officialHenokhaile/
Telegram: https://t.me/deaconhenokhaile
Instagram: https://www.instagram.com/p/CBnMF0nnhcQ/?igshid=549jvl607bv4
Youtube: https://www.youtube.com/channel/UCOaVsWC05aUjeqIEW3fWj7g
22.4K views , 06:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-16 12:55:12 "ሰይጣን የማይነካው ዕቃ "

በአንድ ሐገር ድንገት የአንድ" ጠንቋይ ዝና ከዳር ዳር ተሰማ ። ሰውዬው የማያሳየው ምትሐት የለም። አንበሳ ላለ አንበሳ፣ ነብር ላለ ነብር፣ የሞተ ዘመዴን ላለ የሞተ ዘመዱን፣ የጠፋብኝን ዕቃ ከቤት ፈልገህ አምጣልኝ ላለ ዕቃውን ያመጣለታል። እንደሚታወቀው አጋንንት ከክብራቸው የተዋረዱ መላእክት ናቸው። መላእክት ደግሞ በፈለጉት ሁኔታ መገለጥ ይችላሉ። ይህ ጠንቋይ የሚሰጣቸውን ገጸ ባሕርይ ተቀብለው አንዴ አንበሳ፣ አንዴ ነብር፣ አንዴ ሰው እየሆኑ የሚተውኑት እንግዲህ አጋንንቱ ነበሩ።
የበዚህ ጠንቋይ ዝና ወደ ንጉሱ ደረሰ። ንጉሱ ደግሞ ክርስቲያን ቢሆንም ከመጸሐፍ ቅዱስ ይልቅ እንዲህ ያለ ተአምር እዚህ ቦታ ተፈጸመ ሲባል ለማየተት የሚሮጥ ሰው ነበር። ተአምር የሚወድ ሰው ደግሞ ክርስቲያንም ቢሆን ሰይጣን በሚሰራው ምትሐት መታለሉ የማይቀር ነው። ስለዚህ ይህ ንጉስ የተማረውን መጽሐፍ ቅዱስ ዘንግቶ በጠንቋዩ ምትሐት አመነ።
ይህንን የሰሙ የንጉሱ ንስሐ አባት ነገሩን ሰምተው ወደ ቤተ መንግሥት ሲሮጡ ደረሱ። ሲደርሱ ንጉሡ ከቁም ነገር አልቆጠራቸውም። እሱ የጠንቋይ ትርዒት ማየት ቀጠለ።
"እስቲ አሁን ደግሞ እእእ ነጭ ፈረስ አምጣልኝ" ማለቱን ቀጠለ
በነገሩ ያዘኑት "ኧረ ንጉሥ ሆይ ይተዉ፡ ይህ እኮ የሰይጣን ምትሐት ነው "
ብለው ሊያስረዱት ሲሉ በቁጣ አስቆማቸው።
ተአምር የሚከተል ሰው መቼስ ቢነግሩት አይሰማም። ጭራሽ እንዲያው ለንስሐ አባቱ እንዲህ አላቸው።
" የሰይጣን ስራ ነው አትበሉ፤ ቅናት ነው ይኼማ,,,, ይልቅ እርስዎም የሚፈልጉትን ነገር ይጠይቁት ያምጣልዎት!"አላቸው።
ጠንቋዩ «የፈለጉትን ላምጣልውት,,,,,ምን ይፈልጋሉ,,,, " የሞተ ዘመድ አለዎት,,,,, ወይስ ከቤትዎ,,,, » አላቸው በኩራት።
ካህኑ ውስጣቸው በመንፈሳዊ ቅናት ተቃጠለ። « እንግዲያውስ የፈለኩትን ማምጣት ከቻልህ ወደ ቤተ መቅደስ ሔደህ ልብሰ ተክህኖዬ ውስጥ መስቀል አለ እርሱን ይዘህልኝ ና » አሉት።
ይህን ግዜ ጠንቋዩ ገና ድግምቱን ሲጀምር አጋንንቱ እላዩ ላይ ሰፍረው ጣሉት።
በካህኑ ፊት ወደቀ። ሰይጣን ምንም ነገር ማምጣት ይችል ይሆናል። መስቀሉን ግን ማምጣት አይችልም። አባቶቻችን ሰይጣን እንኳን መስቀል ቀርቶ መስቀለኛ መንገድም አይወድም ይላሉ።
የጌታችን ቅዱስ መስቀል ሆይ ቅዱስ ዳዊት እንዳለ «ብከ ንወግዖሙ ለኩሎሙ ጸርነ»
«በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን!

ከዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
30.4K views , 09:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-15 03:09:00 Channel photo updated
00:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ