Get Mystery Box with random crypto!

የዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች

የቴሌግራም ቻናል አርማ deaconhenokhaile — የዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች
የቴሌግራም ቻናል አርማ deaconhenokhaile — የዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ትምህርቶች
የሰርጥ አድራሻ: @deaconhenokhaile
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 64.23K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ፈቃድ ትምህርቶች የሚለቀቁበት ነው::
@deaconhenokhaile
"ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን"
2ኛ ቆሮ. 2:14

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 37

2022-07-09 05:46:20 በእርግጥ እግዚአብሔር ጥቂት እሾኾች
እንዲያቆስሉን ያደርጋል፤ ይህም ፍቅሩንና ለእኛ
ማሰቡን የሚያስረዳ ነው፡፡ በእሾኽ እንድንወጋ
የሚፈቅደው በቁስላችን ፣ በስቃያችንና በሕመማችን ስለሚደሰት አይደለም ፤ በዚህ ስቃይእንድናድግና እንድንጎለምስ ሊያስተምረንና ሊያለማምደን ነው እንጂ፡፡ ወልደ እግዚአብሔር
ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ስቃይና መከራ አልቀረለትም ፤ እንዲያው በተገላቢጦሹ እስከ
መጨረሻው መራራ ጽዋን ጠጣ፡፡ እንዲህ ተብሎ ስለ እርሱ እንደተጻፈ ፡- ‹‹ምንም ልጅ
ቢሆን ከተቀበለው መከራ መታዘዝን ተማረ›› (ዕብ. ፭፥፩-፰)
ሌሎችን የመፈወስ ጸጋ የተሰጠው ቅዱስ ጳውሎስ ራሱ ‹‹በሥጋው ላይ ስለነበረበት
እሾኽ›› አቤቱታ አሰምቶ ነበር፡፡ እንዲህ ማለቱን ልብ በሉ ፡ ‹‹ስለዚህም በመገለጥ ታላቅነት
እንዳልታበይ የሥጋዬ መውጊያ እርሱም የሚጎስመኝ የሰይጣን መውጊያ ተሰጠኝ ይኸውም
እንዳልታበይ ነው፡፡ ስለዚህ ነገር ከእኔ እንዲለይ ሦስት ጊዜ ጌታን ለመንሁ፡፡ እርሱም ፡-
ጸጋዬ ይበቃሃል ኃይሌ በድካም ይፈጸማልና አለኝ፡፡ እንግዲህ የክርስቶስ ኃይል ያድርብኝ
ዘንድ በብዙ ደስታ በድካሜ ልመካ እወዳለሁ፡፡ ስለዚህ ስለ ክርስቶስ በድካም
በመንገላታትም በችግርም በስደትም በጭንቀትም ደስ ይለኛል ፤ ስደክም ያን ጊዜ ኃይለኛ
ነኝና፡፡›› (፪ቆሮ. ፲፪፥፯)

‹‹ፍጥረት ለከንቱነት ተገዝቶአልና በተስፋ ስላስገዛው ነው እንጂ በፈቃዱ አይደለም
፤ ተስፋውም ፍጥረት ራሱ ደግሞ ከጥፋት ባርነት ነፃነት
ወጥቶ ለእግዚአብሔር ልጆች ወደሚሆን ክብር ነፃነት
እንዲደርስ ነው፡፡ ፍጥረት ሁሉ እስከ አሁን ድረስ አብሮ
በመቃተትና በምጥ መኖሩን እናውቃለንና›› (ሮሜ.፰፥፳)

ስለዚህ እግዚአብሔር በእነዚህ እሾኾች እኛን
በማሰቃየት ደስታን የሚያገኝ ሆኖ አይደለም ፤ ይህ
ለድኅነታችን አስፈላጊና ወሳኝ የሆነ ልንሸከመው የሚገባን መስቀል ለሆነ ነው፡፡ ንስር
ልጆቹን ከዕባብ ለመጠበቅ ጎጆውን በእሾኽ እንደሚያጥር እግዚአብሔርም ከቀደመው ዕባብከዲያቢሎስ እጅ ይጠብቀን ዘንድ በሕይወታችን ውስጥ ጥቂት እሾኾች እንዲኖሩ ይፈቅዳል፡፡
ሁልጊዜ እግዚአብሔርን ‹‹ለምን?›› ብለን እንጠይቀዋለን፡፡ እርሱም እንዲህ ሲል ይመልሳል ፡
- ‹‹እኔ የማደርገውን እናንተ አሁን አታውቁም በኋላ ግን ታስተውሉታላችሁ፡፡›› (ዮሐ.፲፫፥፯
፣መዝ. ፸፪ ፣ዕብ.፲፪)

ንስር ጎጆውን እንደሚያናውጽ እግዚአብሔርም እንዲሁ ያደርጋል፡፡
ንስር እሾኾች ጫጩቶቹን ለመብረር እንዲገፋፉ ለማድረግ ሲል ጎጆውን
ያነዋውጻል፡፡ ይህ ዓይነተኛ ፈተናና ትምህርት ነው፡፡ በእኛም እንዲሁ ነው ፤ እግዚአብሔር
ጎጆእንን በኃይል ያነዋውጸዋል ፤ ይሁናና በፍጹም አያፈርሰውም፡፡

ይህ ንውጽውጽታ ኃይለኛ ከመሆኑ የተነሣ ሊያስደነግጥ ይችላል ፤ ይሁንና አትጨነቁ
ዓላማውንም አትዘንጉ፡፡ እንድትበርሩ ሊያስገድዳችሁ
ነው ፤ አዎን በሰማያዊው ህዋ ደስ እንድትሰኙ
ሊያደርግ ነው፡፡ በዘመናችን የሚከሰተው የመሬት
መንቀጥቀጥና ዓውሎ ነፋስም የብዙዎችን ጎጆ
የሚያናውጽና ሰዎችን ለንስሓ ለማዘጋጀት የሚደረግ
የማንቂያ ጥሪ አንዳች ማሳያ ነው፡፡ እግዚአብሔር
ከእርሱ ጋር በመንግሥቱ ለዘላለም የምንኖርበትን
ዘላለማዊ ጎጆ አዘጋጅቶልናል፡፡ ስለዚህም ሰነፎችና
ከዚህች ዓለም ጋር የተሳሰርን እንድንሆን
አይፈልግም፡፡ ይህን ታላቅ ተስፋ በልባችሁ አኑሩ ፤ ምድራዊ ስቃይን ሁሉ ትዘነጋላችሁ፡፡
‹‹የክብር ተስፋ ያለው ክርስቶስ›› በእናንተ ዘንድ እንዳለም አስታውሱ፡፡ (ቈላ.፩፥፲፯) ከዚህ
ተግባር ጠቀሜታዎች አንዱ ደግሞ ‹‹እግዚአብሔርን በመተማመን መጠባበቅንና ኃይልንማደስን እንደ ንስር በክንፍ መውጣትን›› የምንማር መሆናችን ነው፡፡ (ኢሳ.፵፥፥፴፩) እርሱ
‹‹መንግሥትህ ትምጣ›› ብለን እንድንጸልይ አስተምሮናል፡፡ እናም አንድ ቀን ወደ ሰማይ
እንነጠቃለን ፤ ወደ ምድራዊው ጎጆአችንም በፍጹም አንመለስም፡፡
ክንፎቹን ዘርግቶ ይሸከማቸዋል!

መዝሙር ፺ ይህንን እውነታ በሰፊው ያስረዳል፡፡ ስለ እግዚአብሔር ፈጣን እርዳታ
፣ ስለ መግቦቱ ፣ ጥበቃውና አድኅኖቱ ይናገራል፡፡ ‹‹በልዑል መጠጊያ የሚኖር ሁሉን
በሚችል አምላክ ጥላ ውስጥ ያድራል፡፡ … እርሱ ከአዳኝ ወጥመድ ከሚያስደነግጥም
ነገር ያድንሃልና፡፡ በላባዎቹም ይጋርድሃል ፤ በክንፎቹም በታች ትተማመናለህ ፤ እውነት
እንደ ጋሻ ይከብብሃል፡፡›› መዝ. ፺፥፬

(በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ)
21.8K viewsካልባረከኝ አለቅህም, 02:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 05:46:20 "በንስርም ክንፍ ተሸከምኋችሁ!"

ንስር ንጉሠ አዕዋፍ ነው ፤ በመብረርም ፈጣንና
ጠንካራ የሆነ ነው፡፡ ረዥም ዘመን የሚኖር ፣ ከሩቅ አጥርቶ
የሚያይ ፣ እስከ ተራሮች ከፍታና ከደመናት በላይ
ለመብረር የሚያስችሉ ኃያላን አክናፍ ያሉት ነው፡፡
እንዲሁም ንስር ለጫጩቶቹ ርኅሩኅ ነው፡፡ በጥበብ
ይንከባከባቸዋል ራሳቸውን ችለው እንዲቆሙም
ያለማምዳቸዋል፡፡

ከእነዚህ ተነጻጻሪ ባሕርያት የተነሣ እግዚአብሔር በትሕትና ራሱን ከንስር ጋር
አመሳስሏል፡፡ እግዚአብሔር ዘላለማዊ ፣ ሁሉን ቻይ ፣ ሁሉን ተመልካች (ሁሉን የሚያይና
የሚያውቅ የጥበብ ምንጭ) ፣ ምሕረትን የተሞላ ፣ ለሕዝቡ የሚራራና ወደ ድኅነት
የሚመራቸው ነው፡፡

ጌታ እግዚአብሔር ሕዝቡን መርቶ ከግብፅ ባወጣቸውና ከፈርኦን ሠራዊት ጠብቆ
በተአምር ቀይ ባሕርን ባሻገራቸው ጊዜ እንዲህ ብሏቸው ነበር ፡- ‹‹በግብፃውያን ያደረግሁትን በንስርም ክንፍ እንደተሸከምኋቸችሁ ወደ እኔም እንዳመጣኋችሁ አይታችኋል፡
፡›› (ዘጸ. ፲፱፥፬)

በንስር ሕይወት ውስጥ ካሉት ምሥጢራት አንዱ ሁልጊዜ ጎጆውን በከፍታ ላይ
መሥራቱና በአለታማ ቋጥኞችና ምሽጎች ውስጥ መኖሩ ነው፡፡ እግዚአብሔር ለኢዮብ
ጥበቡንና ኃይሉን ሲያሳየው ያለውን ልብ በሉ ‹‹በአፍህ ትእዛዝ ንስር ከፍ ከፍ ይላልን?
ቤቱንስ በአርያም ላይ ያደርጋልን? በገደል ላይ ይኖራል በገደሉ ገመገምና በጥጉ ያድራል፡፡
በዚያም ሆኖ የሚነጥቀውን ይጎበኛል ፤ ዓይኑም በሩቅ ትመለከታለች፡፡›› (ኢዮ.፴፱፥፳፯)

ንስር ስለምን ከፍ ብሎ ጎጆውን በተራሮች ጫፍ ላይ ይሠራል ?
እንደ አዳኞችና አራዊት ያሉ ጠላቶቹ ሊደርሱበት ከማይችሉበት ስፍራ ለመገኘት
ብሎ ነው፡፡ ይህም ሆኖ ወደ ጎጆው ደርሶ ጫጩቶቹን ሊበላበት የሚችል ሌላ ጠላት አለ፡፡
ይህም ጠላት እስከዚያ ከፍታ ድረስ እስኪደርስ በልቡ ሊሳብ የሚችለው ዕባብ ነው፡፡
ዕባቡ ዘልቆ እንዳይገባ ጎጆውን በመጠን ብዙ በሆኑ
እሾኆች ከውጪ በኩል ያጥረዋል፡፡ የጎጆው ውስጠኛ ክፍል
ደግሞ በላባዎች የተደራጀ ሞቃታማና ምቹ ነው፡፡ ውጪው
ግን በእሾኽ የታጠረ ነው፡፡ ታላቁ ንስር ለጫጩቶቹ ጥሩ
እንክብካቤ ያደርጋል፡፡ የሚበሉትን ያቀርብላቸዋል ፣ በክንፎቹ
እያንዣበበ ይጋርዳቸዋል ፣ በአፉ (በመንቆሩ) ይመግባቸዋል፡፡
ትንንሾቹ አንስርት (ንስሮች) እንዳሻቸው እንዲኖሩ የተተዉ
ቢሆኑ ኖሮ ለዘላለም ከጎጆአቸው ባልወጡ ነበር፡፡

ስለዚህ ጊዜው ደርሶ ጫጩቶቹ ሲያድጉ ታላቁ ንስር የመብረር ችሎታቸውን
ይፈትናል ፤ ጎጆውንም መትቶ ያነቃንቀዋል፡፡ አንዳንድ ጊዜ መገፋቱ ጠንከር ሲል ጎጆው
ከተራራው ጫፍ ወደ ዝቅተኛው ጫፍ ሊወድቅ ይችላል፡፡

ጎጆው በተነዋወጸ ጊዜ ከውጪ ያሉት እሾኾች ወደ ውስጥ ይገባሉ ፤ በጫጩቶቹም
ላይ መወጋትንና ሕመምን ያስከትላሉ፡፡ ክንፎቻቸውን ያንቀሳቅሳሉ ለመብረርም ይሞክራሉ፡
፡ ከተሳካላቸው ለመጀመሪያ ጊዜ ለመብረርና ንጹሑን የሰማይ አየር እየተነፈሱ ለመደሰት
ይችላሉ ፤ ዳግመኛም ወደ ጎጆአቸው በፍጹም አይመለሱም፡፡ በዚህም ተልእኮውን በሚገባ
ያለችግር በማከናወኑ ታላቁ ንስር ደስታ ይሰማዋል፡፡

የጫጩቶቹ የክንፋቸው ላባ በበቂ ሁኔታ ካላደገና መብረር ሳይቻላቸው ከወደቁ ታላቁ
ንስር ፈጥኖ ክንፎቹን ዘርግቶ ይይዛቸዋል ፤ በክንፎቹም ይሸከማቸዋል፡፡ ለተጨማሪ
ቆይታም ወደ ጎጆአቸው ይመልሳቸዋል፡፡ ይህንን ዑደት መብረር እስከሚችሉ ድረስ
ይደጋግመዋል፡፡ አይደንቅም ትላላችሁ?

‹‹ንስር ጫጩቶቹን እንደሚያወጣ በእነርሱም ላይ እንደሚሰፍፍ ክንፎቹን ዘርግቶ
ወሰዳቸው ፤ በክንፎቹ አዘላቸው፡፡ እግዚአብሔር ሕዝቡን ብቻውን መራው›› ዘዳ.፴፪፥፲፩

ከላይ እንደተገለጠው እግዚአብሔር ራሱን ከንስር ጋር አመሳስሏል፡፡ እኛም ከድንቅ
ፍጥረቱ ከንስር ሕይወት አንዳንድ ቁም ነገሮችን እንቀስማለን፡፡

ምእመናን የንስር ጫጩቶችን ይመስላሉ!
የንስር ጫጩቶች ደካሞችና በራሳቸው ለመቆምና በራሳቸው ለመኖር የማይችሉ
ናቸው፡፡ የሰው ልጅም ሲወለድ በራሱ መብላት መጠጣት ፣ መሄድ ፣ መናገር ፣ማሰብ ፣ ፍላጎቶቹን መፈጸም የማይችል ሆኖ ነው የሚወለደው፡፡ በተመሳሳይ
በመንፈሳዊ ሕይወቱም ጠላቶቹን ኃጢአትን ፣ ሰይጣንን ፣ የሥጋ ምኞትንና
የዚህችን ዓለም መስህብነት ለመቃወም ደካማ ነው፡፡
ነቢዩ ንጉሥ ዳዊት ይህንን እውነታ ከአስከፊው ውድቀቱ በኋላ በስድስተኛው
መዝሙሩ ሲገልጥ ‹‹አቤቱ በቊጣህ አትቅሠፈኝ በመዓትህም አትገሥጸኝ፡፡ ድዉይ ነኝና
አቤቱ ማረኝ›› ብሏል፡፡ (መዝ.፮፥፩-፪) የእግዚአብሔር ንቁ ዓይኖች ፣ ኃያላን ክንዶቹና
ሁልጊዜ በላያችን የሚጋርዱን ክንፎቹ ያስፈልጉናል፡፡ ይህንን ደካማነታችንንና
ኃጢአተኛነታችንን እስካላመንን ድረስ ግን የእግዚአብሔር ኃይል ወደ እኛ ፈጽሞ
አትመጣም፡፡
በሌላ ያማሩ ቃላት መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል ፡- ‹‹በሰማያት ላይ ለረድኤትህ
በደመናትም ላይ በታላቅነት እንደሚሄድ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማንም የለም፡፡ መኖሪያህ
የዘላለም አምላክ ነው ፤ የዘላለም ክንዶች ከአንተ በታች ናቸው፡፡›› (ዘዳ.፴፫፥፳፯)

የንስር ጫጩቶች እንደ እኛ አላዋቂዎች ናቸው፡፡
እኛ ከትምህርታችንና ከዲግሪዎቻችን ያገኘነው ምንም
ይሁን ምን አላዋቂነታችንንና የእግዚአብሔር መሪነት
እንደሚያስፈልገን ማመን ይገባናል፡፡ በመንፈሳዊው ዕይታ
የሰው ልጅ አላዋቂ ነው፡፡ ወደፊት ስለሚመጣው ነገር ፣
ከሞት በኋላም ስላለው ነገር ፣ ሌላው ቀርቶ ስለ ራሱና
በፍጥረታት ውስጥ ስላሉ በሚልዮኖች ስለሚቆጠሩ ነገሮች እንኳን አያውቅም ፡፡
ማየት የማይችል ከመሆኑም የተነሣ የቃለ እግዚአብሔርና የመንፈስ ቅዱስ
ብርሃንነት እንዲሁም ምክረ ካህን ያስፈልገዋል፡፡እግዚአብሔር እኛን የሚንከባከበት መንገድ ከንስር ጋር ይመሳሰላል!

ንስር ከፍ ከፍ እንደሚልና ጎጆውን በከፍታ ላይ እንደሚሠራ እግዚአብሔርም
ልጆቹ ከሌላው ሰው በተለየ መዓርግ እንድንኖር ይፈልጋል፡፡ በቅድስና ሕይወት
እንድንኖርና ከእርሱ ጋር ለዘላለም በመንግሥቱ ለመኖር ራሳችንን እንድናዘጋጅ
ይፈልጋል፡፡ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ በጥምቀት ከተወለድን ጀምሮ የመንግሥተ
ሰማያት ዜጎች ሆነናል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በፊልጵስዩስ ፫፥፲ ፡ ‹‹እኛ ሀገራችን በሰማይ
ነውና›› ብሏል፡፡ ከሰማያዊው አምላክ ተወልደናል ፤ ምግባችን ቃለ
እግዚአብሔርም ፣ ሥጋ ወደሙም ፣ ጸሎትና አንድነታችንም ሁሉም ከላይ ነው፡፡
‹‹በጎ ስጦታ ሁሉ ፍጹምም በረከት ሁሉ ከላይ ናቸው ፤ መለወጥም በእርሱ ዘንድ
ከሌለ በመዞርም የተደረገ ጥላ በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ፡፡››
(ያዕ.፩፥፲፰)

ስለዚህም ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ ክርስቶስ
በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ ያለውን እሹ ፤ በላይ ያለውን አስቡ እንጂ
በምድር ያለውን አይደለም፡፡ ሞታችኋልና ሕይወታችሁም በእግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር
ተሰውሮአልና ሕይወታችሁ የሆነ ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ በዚያን ጊዜ እናንተ ደግሞ
ከእርሱ ጋር በክብር ትገለጣላችሁ፡፡›› (ቈላ.፫፥፩-፬)

እግዚአብሔር ጎጆአችንን በእሾኾች ያጥረዋል!
18.3K viewsካልባረከኝ አለቅህም, 02:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 08:13:09 እመቤታችን ተወለደች ማለት ጌታ ሊወለድ 15 ዓመት ቀረው ማለት ነው:: እግዚአብሔር ከሴት የተወለደ ልጁን ሊልክ የዘመኑ ፍጻሜ ቀረበ ማለት ነበር። እግዚአብሔር ሃና እና ኢያቄምን ሳይወልዱ ያዘገያቸውም ለዚህ ታላቅ ክብር እንዲበቁ ነበር።
ቀድመው ልጅ ቢወልዱ ኖሮ ይህችን የፍጥረት ደስታ የሆነች ልጅ አይወልዱም ነበር:: የእርስዋ የልደት ቀን የፍጥረት ደስታ ቀን ነው::

ክርስቶስ ፀሐይ ከሆነ የዛሬው ዕለት ሰማይዋ የተዘረጋችበት ዕለት ነው።

ክርስቶስ የሕይወት ውኃ ከሆነ ዛሬ ምንጭዋ የፈለቀችበት ዕለት ነው።

ክርስቶስ መድኃኒት ከሆነ ዛሬ የመድኃኒቱ ሙዳይ የተገኘችበት ዕለት ነው::

ወንጌል በመጥምቁ ዮሐንስ መወለድ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል ይላል። በእመቤታችን መወለድ ምን ያህል ሰዎች ደስ ይላቸው ይሆን? የእመቤታችን ልደት በብዙ ሀገራት ብሔራዊ በዓል ሆኖ ይከበራል።

እኛም በሊባኖስ ተራሮች (አድባረ ሊባኖስ) መወለድዋን በማሰብ ከደጅ ወጥተን ቅድም አያቶችዋ በጨረቃ ተመስላ በህልማቸው ያዩአትን የጨረቃችንን (በግሪኩ ሶልያና) ልደት ጨረቃን እያየን እናከብራለን። የልደትዋ ቀን ልደታችን ነው!

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
21.9K viewsካልባረከኝ አለቅህም, 05:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 08:53:16 እርስዋም አንተ አይሁዳዊ ስትሆን ሳምራዊት ከምሆን ከእኔ ውኃ ትለምናለህ? አለችው፡፡ እንዲህ ነው ነገሩ፡፡ የቆሰለች ነፍስ ስለ ዘር ታወራለች፡፡ ተስፋ የቆረጠች ነፍስ የዘር ጉዳይ ሲሆን ልሳንዋ ይከፈታል፡፡ ውኃ ለማጠጣት ዘር መጠየቅን ምን አመጣው፡፡ ውኃው አይሁዳዊ ነው? ወይንስ ሳምራዊ? ውኃ ጠማኝ የሚል ሁሉ ውኃ ይገባዋል እንጂ ዘሩ አይጠየቅም፡፡ እርስዋ ግን ጠየቀችው፡፡ በእርግጥ ይህች ሳምራዊት ሴት ይህን ጥያቄ የጠየቀችው ክርስቶስ መሆኑን ከማወቅዋ በፊት ነበር፡፡ ክርስቶስ መሆኑን ካወቀች በኋላ ግን ስለ አይሁዳዊነትና ስለ ሳምራዊነት ስትናገር አልተሰማችም፡፡ ‘’አንተ አማራ ስትሆን ጉራጌ ከምሆን ከእኔ ውኃ ለምን ትለምናለህ?’’ ‘’አንቺ ኦሮሞ ስትሆኚ ትግሬ ከምሆን ከእኔ እንዴት ውኃ ትለምኛለሽ?’’ በሚል ጥያቄ ሀገሩን ያጨናነቁተ ክርስቶስን ያወቁ ክርስቲያኖች መሆናቸው ግን ልብን የሚሰብር እውነታ ነው፡፡ በዚህ ጠባያችን እንደ ክርስቲያን ሳንኖር እንደ ክርስቲያን ልንሞት መሆኑ ምንኛ ያሳዝናል?

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ)
24.2K viewsካልባረከኝ አለቅህም, 05:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 04:03:08 https://www.facebook.com/490069727707457/posts/pfbid02brLwjwuT2pxmQrv6HEeqausTFvvcZEys24GtZEZwFovDENq45YK5KJ1Up2r18xwWl/?sfnsn=mo
21.4K viewsካልባረከኝ አለቅህም, 01:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 10:41:32 + ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንዲህ አለ +

“ከልቦቻችን በማይነቀሉ የፍቅሩ ችንካሮች ተቸነከርን:: ያዝነው አንለቀውም እርሱም አቀፈን አልተወንም:: ወደ እርሱ በሃይማኖት አቀረበን:: ከእርሱም ወደ ቀኝ ወደ ግራ አንሸሽም:: እንደ ቀለበት በልባችን እንደ ማኅተም በክንዳችን አኖርነው:: እንደ ዕንቁ በልባችን ሳጥን አስቀመጥነው:: እንደ ወርቅ በሕሊናችን መዝገብ አኖርነው::
እንደ ግምጃ ለበስነው:: እንደ ሐር ግምጃ ተጎናጸፍነው:: እንደ ወታደር ሰይፍ ታጠቅነው:: ለጦር ዕቃ እንደተዘጋጀ የድል ጋሻ ተደገፍነው:: ተከዜና ግዮን በኢሎል ወር እንደሚሞሉ ፍቅሩ በልባችን መልቶአል:: እንደ መከር ጊዜ የዮርዳኖስ ወንዝ እንደ ክረምት ጊዜም የጤግሮስ ወንዝ ስንዴ ሲያሹት እንደሚሆን እንደ ኤፍራጥስ ወንዝ ልባችንን በወንጌል ፈሳሽነት አረሰረሰው:: መርከባችንንም በሃይማኖት ወንዝ አስዋኘው"
መጽሐፈ ምሥጢር 24:20

"ከእኛ ወገን ክርስቲያን እየተባሉ በገዛ መንገዳቸው የሚኖሩ ብዙዎች ናቸው ... የእንስሳ ሥጋ ከመብላት የሚከለከሉ የሰውን ሥጋ ለመብላት ግን የሚተጉ እነዚህ ናቸው"

"ስምዖን ጴጥሮስ ከሐዋርያት ሁሉ አብልጦ ክርስቶስን ወደደው:: ክርስቶስ ግን ከሐዋርያት ሁሉ አልቆ ወንጌላዊው ዮሐንስን ይወድደው ነበር::
ስለወደደው ግን አለቃ መሆንን ለዮሐንስ አልሠጠም:: እርሱ ከወደደው በላይ እርሱን የሚወደውን አለቃ አደረገው እንጂ"

"ክርስቶስን መውደድ ከወንድሞቹ ይልቅ በጴጥሮስ ላይ በዛ:: ከወንድሞቹ ይልቅ ወደ ጌታ ኢየሱስ ለመድረስ ቸኩሏልና ከመርከቢቱ ዘልሎ ወደ ባሕር ተወረወረ እንጂ በመርከብ ለመጎተት አልቆየም::
ወደ ወደደው ለመድረስ ቀደማቸው:: ከመርከቢቱ ላይ ያዘለለችው ወደ ጥልቁም ባሕር የወረወረችው ፍቅር እርስዋ የክህደቱን መጽሐፍ ደመሰሰችለት::
ራሱን ወደ ጥልቁ የጥብርያዶስ ባሕር በወረወረ ጊዜ የዕዳው መጽሐፍ ሰጠመ:: እርሱ ግን በብዙ ጭንቅ በብዙም ፍለጋ በዋናተኞችም በብልጠታቸው ጥበብ እንደሚገኝ እንደሚያበራ ዕንቁ ሆኖ ከባሕር ውስጥ ወጣ"

ከመጽሐፈ ምሥጢር ውብ ገጾች

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሰኔ 27 2014 ዓ.ም.
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን አጥብቃችሁ ስለ እኔ ጸልዩልኝ!
በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)

ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-

የፌስቡክ ገጽ :- https://www.facebook.com/officialHenokhaile/
የቴሌግራም ቻናል : https://t.me/deaconhenokhaile
የዩቲዩብ ገጽ: https://www.youtube.com/channel/UCOaVsWC05aUjeqIEW3fWj7g
28.1K viewsካልባረከኝ አለቅህም, 07:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 01:26:54 Watch "ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ| ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ | ተግባራዊ ክርስትና ክፍል 6- Reading Holy Books |Henok Haile-Part 6" on YouTube


23.7K viewsካልባረከኝ አለቅህም, 22:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 01:44:57 Watch "ቀጥታ ሰርጭ ከ skylight part 2" on YouTube


25.9K viewsካልባረከኝ አለቅህም, 22:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 10:12:51 ++ በሰንበት መፍረስ ++

የኢያሪኮ ሰዎች የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ኃይል በመናቃቸው ምንኛ ተጎዱ?! እርሱ ዓለምን የፈጠረ መሆኑን ስላላመኑ እንዳልተፈጠሩ የሆኑት የኢያሪኮ ሰዎች መጨረሻ እጅግ አሳዛኝ ነበር፡፡

ቅጥራቸው ከመፍረሱ በፊት እስራኤል የእግዚአብሔርን ታቦት ይዘው ለስድስት ቀናት ያህል በዝምታ ኢያሪኮን ዞሯት፡፡ ዓለምን በስድስት ቀናት የፈጠረውን ጌታ እንዲያስተውሉ ስድስት የዝምታ ቀናት ተሠጧቸው፡፡ በሰባተኛው ቀን ግን ጮኹ የኢያሪኮም ቅጥር ፈረሰ፡፡

ሰባተኛ ቀን የዕረፍት ቀን ነው፡፡ ለኢያሪኮ ግን የመፍረስ ቀን ሆነባት፡፡ ሰባተኛ ቀን ፈጣሪን ለሚያምኑ የተቀደሰ ቀን ነበር ፤ ለኢያሪኮ ግን የመረገም ቀን ሆነባት፡፡
እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም እንደሆነ ባየበት ሰባተኛ ቀን ኢያሪኮ ግን ከፉ እንደሆነች ታየባት፡፡

እግዚአብሔር የሌለበት ሕይወት እንዲህ ነው፡፡ ወዳጄ እግዚአብሔር በሕይወትህ ውስጥ ከሌለ የሰንበት ቀን የነፍስህ ዕረፍት ቀን መሆኑ ይቀርና እንደ ኢያሪኮ የመፍረስ ቀን ይሆናል፡፡ በዚያ ቅዱስ ቀን ቅጥርህን በመጠጥ ፣ ብስካር ብዝሙት ስታፈርስ ትውልና ታድራለህ፡፡ ራስህን አንድደህ ትሞቃለህ ፤ እያራገብህ ትቃጠላለህ፡፡ ታቦት ይዘው ቢዞሩህም የኃጢአት ግንብን አጥረሃልና አትሰማም፡፡ በላይህ ላይ ቢቀደስብህም እንደ ኢያሪኮ ሰዎች ካህናቱን እያየህ ‘ዝም ብሎ መዞር ምንድር ነው?’ እያልክ ትስቃለህ፡፡ የካህናቱ የቅዳሴ ዜማ ለአንተ የሚያፈርስ ጩኸት ይሆንብሃል፡፡ የኢያሪኮ ሰው ከመሆን ፣ በሰንበት ፈራሽ ከመሆን ያድንህ!

ቅዳሴያችን መካከል ካህኑ ዕጣን እያጠኑ ዞረው ሲመለሱ የዚህች አጭር ጽሑፍ መነሻ ሃሳብ የሆነውን ይህንን ጸሎት ይጸልያሉ፦ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ አስቀድመህ በባሪያህ በነዌ ልጅ በኢያሱ እጅ የኢያሪኮን ግንብ እንዳፈረስከው የእኔንና የሕዝብህን የኃጢአታችንን ግንብ አፍርሰው፡፡

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ ጸልዩ! ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like እና Share ያድርጉ
FB: https://www.facebook.com/officialHenokhaile/
Telegram: https://t.me/deaconhenokhaile
Instagram: https://www.instagram.com/p/CBnMF0nnhcQ/?igshid=549jvl607bv4
Youtube: https://www.youtube.com/channel/UCOaVsWC05aUjeqIEW3fWj7
27.3K viewsካልባረከኝ አለቅህም, 07:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 19:42:26
22.8K viewsחנוך כּוֹחַ, 16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ