Get Mystery Box with random crypto!

Bule Hora University

የቴሌግራም ቻናል አርማ bulehorauniversity — Bule Hora University B
የቴሌግራም ቻናል አርማ bulehorauniversity — Bule Hora University
የሰርጥ አድራሻ: @bulehorauniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 15.23K
የሰርጥ መግለጫ

Bule Hora University Official telegram

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-05-10 17:02:56 ሚያዚያ 12/2015 ዓ.ም
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በድርቅ ለተጎዱ ለአካባቢው ማህበረሰብ 355 ኩንታል የስንዴ ምርጥ ዘር ማከፋፈሉን ገለፀ፡፡

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በኦሮሚያ ህብረት ሥራ ኢንተርፕራይዝ የተዘጋጀውን በመግዛት የስንዴ ምርጥ ዘር ማከፋፈሉን ገልፀዋል፡፡የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፍቃዱ ወ/ማርያም የተገዛውን የስንዴ ምርጥ ዘር ለምዕራብ ጉጂ ዞን ም/አስተዳዳሪ ርክክብ ባደረጉት ወቅት እንደገለፁት ዩኒቨርሲቲዉ የልህቀት ማዕከል አደርጎ ከሚሰራባቸዉ ሥራዎች አንዱ የግብርና ልማትን ማስፋፋት መሆኑን በመጥቀስ ይህ እየተከፋፈለ ያለዉ የስንዴ ምርጥ ዘር በአምስቱ ወረዳ ዉስጥ ላሉና በይበልጥ በድርቅ ጉዳት ለደረሰባቸዉ የህበረተሰብ ክፍል መሆኑን ገልፀዉ በቀጣይም ዩኒቨርሲቲዉ ተመሳሳይ ሥራዎችን በማህብረሰብ አገልግሎት በኩል አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግሯል፡፡
በሌላ በኩል በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ማህብረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ታደሰ ጅሎ እንደገለፁት ቀደም ሲል ለአምስቱ ወረዳዎች ዩኒቨርሲቲዉ ነፃ የህግና የጤና አገልግሎት እየሰጠ የቆየ መሆኑን አስረድትዋል:: ከስንዴው ምርጥ ዘር ጋርም በተያያዘ ዩኒቨርሲቲዉ በአጠቃላይ 389 ኩንታል የስንዴ ምርጥ ዘር በሁለት ሚሊዮን ብር መገዛቱን አሳውቆ ከዚህም ላይ 355 ኩንታል ለአምስት ወረዳ አርሶ አደሮች የተሰጠ ሲሆን ቀሪው 34 ኩንታል ለዩኒቨርሲቲው ግብርና ማዕከል ገቢ መደረጉን ገልፀዋል፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
1.5K viewsZedo FM 99.0, 14:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 16:31:22
Ebla 12/2015
Yuunivarsiitii Bulee Horaatti Gamaaggamni Raawwii Hojii Karoora Kurmaana 3ffaa Ji’a 9ffaa Bara 2015 Gaggeeffame .

Daayrektoreetiin qophii karooraa fi baajata Yunivarsiitii Bulee Horaa bakka pireezdaantiin Yuunivarsiitii Bulee Horaa Dr. Fiqaaduu W/Maariyaam fi hoggantoonni olaanoo yuunivarsiitichaa argamanitti gabaasa kurmaana sadaffaa, ji' a 9ffaa bara 2015 dhihaateera .

Yuunivarsiitii Bulee Horaa
2.3K viewsZedo FM 99.0, 13:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 16:24:52
ሚያዚያ 12/2015 ዓ.ም
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የ2015 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የሥራ ዕቅድ ክንዉን ግምገማ ተካሄደ፡፡
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የዕቅድ እና በጀት ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት አቅራቢነት የ2015 ዓ.ም የሦስተኛ ሩብ ወይም የዘጠኝ ወራት የሥራ የዕቅድ አፈፀፃም የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፍቃዱ ወ/ማርያም እና የዩኒቨርሲቲዉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ሪፖርት ቀርቦ ግምገማ ተደርጓል፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
2.2K viewsZedo FM 99.0, 13:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 15:36:15
EBLA 12/2015
Yuuniivarsiitii Bulee Horatti Giddugalli Misooma Qonnaa Sanyii Qamadii Filatamaa Facaasuu Eegaluu Beeksise.

Giddugalli misooma qonnaa Yuunivarsiitii Bulee Horaa Sanyiin qamadii bara 2015 facaafamaa jiru kun Adeemsa baruu barsiisuu,qo’annoo fi qorannoo akkasummas tajaajjila hawaasaa giddugaleeffachuun kan facaafamaa jiruu fi Haala qabatama naannoo irraatti hundaa’uun waqtii isaa eegee facaafamaa jiraachuun ibsameera.

Akka daayrekteerri giddugala misooma qonnaa Barsiisaa Haroo Adulaa ibsaniti, gosti sanyii qamadii filatamaa lamaan kunis Qaqqabaa fi ''kingibardii ''yemmuu ta’uu heektaara soddoma (30) irraatti kan facaafamuu fi Sanyiin qamadii filaatamaan kun heektaara tokko irraa kuntaala soddomii sadii hanga kuntaala soddomii shan (33-35) akka argamsiisu erga dubbatanii booda sanyiin qamadii filatamaani kun Biiroo intarpiraayizii Waldaa Misooma oromiyaa irraa kan bitame ta’uu ibsaniiru.
Yuunivarsiitii Bulee Horaa
2.1K viewsZedo FM 99.0, 12:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 15:22:05
ሚያዚያ 12/2015 ዓ.ም
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ልማት ማዕከል ወቅቱን ጠብቆ ስንዴ መዝራት መጀመሩን ገለፀ፡፡
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ልማት ማዕከል በ2015 ዓ.ም ምርት ዘመን በሰላሳ ሄክታር የእርሻ መሬት ላይ ምርጥ ዘርና ግብዓት በመጠቀም ስንዴ መዝራት መጀመሩን አሳዉቋል፡፡የግብርና ማዕከል ዳይሬክተር የሆኑት መ/ር ሀሮ አዱላ እንደገለፁት የተዘሩት የስንዴ ዓይነቶች "ቀቀባና ኪንግ በርድ" የሚባሉ መሆናቸዉን በመጠቀስ ይህም በሄክታር ከ33-35 ኩንታል ምርት ሊገኝ እንደምችል ተናግሯል፡፡
መ/ር ሀሮ አያይዘዉም የእርሻ ሥራዉ ለዩኒቨርሲቲዉ በገቢ ምንጭነት ከማገልገሉም በላይ ለመማር ማስተማር ፤ለምርምርና ለማህብረሰብ አገልግሎት ከፍተኛ ጥቅም ያለዉ መሆኑን በመግለጽ በቀጣይም በግብርና ልማት ማዕከል ሥር የተለያዩ የእርሻ ሥራዎችን በስፋት ለማከናወን እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
2.0K viewsZedo FM 99.0, 12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 14:48:31
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ስርፀት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ከ25-26/09/2015 ዓ.ም “Pastoralism and climate change Resilience “በሚል ርዕስ አለም አቀፍ ጥናታዊ ኮንፈረንስ ስለሚያካሂድ በኮንፈረንሱ እንድትሳተፉ ተጋብዛችሁዋል፡፡
1.8K viewsZedo FM 99.0, 11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 10:12:51
2.3K viewsTesso Dido, 07:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 10:12:49 መጋቢት 09/2015 ዓ.ም
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በግብርና ሣይንስ ኮሌጅ የ2015 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች የሞዴል ፈተና በኦንላይን ተሰጠ፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ጥራቱ ላይ ትርጉም ያለዉን ለዉጥ ለማምጣት የጀመረዉን አቅጣጫ በመከተል የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ሣይንስ ኮሌጅ ከቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ አይሲቲ ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር እና የኢ-ሌርንግ ሲስቴም በመጠቀም ለአራተኛ አመት ተማሪዎች የ1ኛ ዙር የሞዴል ፈተና በኦንላይን መስጠቱን አሳዉቋል፡፡

የግብርና ሣይንስ ኮሌጅ ዲን የሆኑት መ/ር ንጉሴ ጎዳና እንደገለጹት የሞዴል ፈተና በኦንላይን ለተማሪዎቹ መሰጠቱ ጥቅሙ ከኩረጃ ነፃ በሆነ መንገድ ማለፍ እንዲችሉ ከማድረጉም በላይ በቀጣይ ለሚፈተኑት የመዉጫ ፈተና በራስ የመተማመን ሁኔታን እንደሚፈጥር አስረድቷል፡፡

በተያያዘ መልኩ መ/ር ንጉሴ እንደገለጹት ቀደም ሲል ተማሪዎች ፈተናዉን ተፈትነዉ ዉጤት ለማየት የሚቆዩበትን ጊዜ በማስቀረት ዉጤታቸዉን ወዲያዉኑ እንድያዉቁት ከመርዳቱም በላይ አንዳንድ ጊዜ የሚፈጠረዉን የእርማት እና የዉጤት አጠነቃቀር ስህተትን እንደሚያስቀር የተናገሩት የኮሌጁ ዲን ከወጪ አንፃርም ለፈተናዉ ዝግጅት ልወጣ የነበረዉን የጽፌት መሣሪያ እና ተያያዥ ጉዳዮችን ወጪ ማዳን የተቻለ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡

ተማሪዎች ለፈተና እንድዘጋጁ ከማድረግ አንፃርም በፈተናዉ ዙሪያ አስፈላጊዉ ገለፃ፤ቲቶሪያል ትምህርት እና የተለያዩ ሞጁሎች ተዘጋጅቶ መሰጠታቸዉንም ጠቁመዋል፡፡

በመጨረሻም እንደ ኮሌጁ ዲን ገለፃ ይህንኑ በትምህርት ጥራት ላይ የተጀመረዉን መልካም ሥራ በተጠናከረ ሁኔታ ለማስቀጠል እንዲቻል የተወሰኑ ተግዳሮቶች ማለትም የኮምፒዩተር እጥረት ፤የኢንተርኔት መስመር ዝርጋታ በቂ አለመሆን እና የመብራት መቆራረጥ ችግሮች እያጋጠሙ ስለሆነ የሚመለከታቸዉ አካላት አስፈላጊዉን ትኩረት በመስጠት ችግሩ የሚፈታበትን መንገድ እንድያመቻቹ ጠይቀዉ የሁለተኛ ዙር የኦንላይን ፈተና በቀጣይ ሚያዚያ ወር ዉስጥ እንደሚሰጥ መግለፃቸዉን ለመዘገብ ተችሏል፡፡

ለላቀ ለዉጥ እንተጋለን!
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
2.4K viewsTesso Dido, 07:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 18:21:32
መጋቢት 2/2015 ዓ.ም
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓ.ም ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደዉ የአቅም ማሻሻያ ትመህርት ለመማር ወደ ዩኒቨርሲቲዉ የተመደቡትን ተማሪዎች ለመቀበል ዝግጅት ማጠናቀቁን ገለፀ፡፡
በ2014 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ወስደዉ የማለፍያ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተዉ የአቅም ማሻሻያ ትምህርት እንዲማሩ ትምህርት ሚኒስተር ማሳወቁ ይታወሳል፡፡

በመሆኑም መንግስት ያስቀመጠዉን አቅጣጫ መሠረት በማድረግ በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡትን ተማሪዎች ለሁለት ተከታታይ ቀናት መጋቢት 4 እና 5 ለመቀበል ዝግጅት ማጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲዉ ተማሪዎች አገልግሎት ጉዳይ ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ቦሩ በደያ ገልፀዋል፡፡

እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ከሆነ የአቅም ማሻሻያ ትምህርቱን እንዲማሩ የተመደቡት ተማሪዎች ጠቅላላ ብዛታቸዉ 2700 ሲሆኑ ከነዚህም 1346 ሴት ተማሪዎች መሆናቸዉን አሳዉቀዋል፡፡

በመጨረሻም የተመደቡት ተማሪዎች ምንም ዓይነት ስጋት ሳይኖርባቸና ትምህርታቸዉን የሚከታተሉበት ሁኔታ እንደሚመቻች ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡

ለላቀ ለዉጥ እንተጋለን!
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
2.6K viewsTesso Dido, 15:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 18:17:13
2.4K viewsTesso Dido, 15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ