Get Mystery Box with random crypto!

በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪

የቴሌግራም ቻናል አርማ bemaledanek — በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
የቴሌግራም ቻናል አርማ bemaledanek — በማለዳ ንቁ ቁጥር ! ፪
የሰርጥ አድራሻ: @bemaledanek
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.09K
የሰርጥ መግለጫ

♥አላማው
☞መንፈሳዊ ወንድምነት እህትነት ማጠናከር
☞መንፈሳዊ ምግብን ተመግበን ንስሀ ገብተን በቅዱስ ቁርባኑ የበቃን መሆን
☞ተሞክሮዎችን በማካፈል መልካም ፍሬዎችን ማግኘት
አስተያየት ከለዎ👉 @Hiyab_Nat ያድርሱን 👉ወደ ግሩፕ ለመቀላቀል @egzabehertalakenew

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-30 18:55:06 የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ


ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
ዘማሪ አርቲስት ይገረም ደጀኔ
ዘማሪ ገ/ዮሐንስን ገ/ፃዲቅ
ቀሲስ ምንዴዬ ብርሀኑ
ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ
ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
ዘማሪ ዲ/ን ሮቤል ማቲያስ
ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን
ዘማሪት አቦነሽ አድነው
ዘማሪት ዶ/ር ሔለን ተስፋዬ

እና የሌሎችንም ...........

ዘማሪዎችን መዝሙሮች እና አዳዲስ
መዝሙሮችን ለማግኘት ከስር OPEN
የሚለውን ይጫኑት።

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
58 views15:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 22:21:11    ማየት የተሣነው ሰው መንገዱን በራሱ እርምጃ ሊጓዘው እንደማይችል፤ እንዲሁ የአምላክን ቃልና ፈቃድ ከማየት እምቢ ያልነው እኛም፤ የኑሮ እጃችን መዳፉን ለዲያቢሎስ አሳልፎ በመስጠቱ፤ ሕይወታችን በጊዜ መንገድ ላይ ሲሄድ የሚገኘው ከእግዚአብሔር እየሸሸ ነው፡፡

   "ሰው" ሆኖ የመኖር ልክን በሥጋዊ ሚዛኖች ብቻ ለክቶ የሚሰፍር አመለካከት እንደ ጣዖት ሁለንተናችንን ስለገዛው፤ በኃጢኢት ቀናቶች ተሞልተው ያለፉት ዓመታቶቻችን እግዚአብሔርን ከማየት የተከለከለ ታሪክ በዕድሜያችን ላይ ስለማስቀመጣቸው ገና በደንብ አልተረዳንም፡፡

   እያንዳንዷ በኃጢአት ቆይታ ውስጥ ያለፈችው ደቂቃ የነፍስ ዓይናችንን በበደል ስለት እየደነቆለች መንፈሳዊ እይታችንን በመጉዳቷ፤ ዓለም ላይ በገሐድ ተጨብጦ ከሚታየው ጉዳይ ውጪ ሌላ አተያየት በፍጹም ሊኖረን አልቻለም፡፡ የዲያቢሎስ ሠራዊት ወደ ሰዎች ሕይወት ሲመጣ "ባላጋራ" ይሆን ዘንድ አለውና፤ እነርሱ ከሰማይ (ከእግዚአብሔር ከሆነው) የተለዩበትን ባሕሪይ ለኛ ሰብአዊ ባሕሪይ ከውስጥ በኩል በማጋራት፤ እነርሱ ብቻ ወደሚታያቸው የጥልቁ አድራሻ በዝግታ ይወስዱናል፡፡

   ይህንን ወደ ዘላለማዊ ጽልመት የሚገፋ የመናፍስት ኮሽታ አልባ አካሄድ በራሱ የግንዛቤ ችሎታ በመደገፍ መርምሮ ሊረዳ የማይችለው ሥጋችንም፤ የሕይወትን (ሰማያዊና ምድራዊ) ሙሉ ትርጉም ሲኖር በገበየው የእውቀት ልክ እየጠቀለለ፤ ረቂቁን መንፈሳዊ ጎን ሳያገኘው፥ የመኖር ዘመኑ እስኪያልቅ በአንድ ጎኑ ተንጋድዶ ይኖራል፡፡

   የሥጋው ዓለም ትውልድ ሃይማኖታዊ ሥነ ሕይወትን ከነአካቴው ትቶ የሚገኝበት በተለይ ይሄ ዘመን፤ ኃጢአት ምድርን በመላ የሸፈነ የሰዎች የጋራ ገጽታ እስኪሆን ድረስ በመናፍስት ጥልፍልፍ አሠራር እንደተቀደመ ለማረጋገጥ የዚህ ዘመን ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው፡፡ ስለዚህ ከኃጢአት ኋላ ረድፉን ጠብቆ ብቅ የሚለው ጨለማ ሁላችንን በሚያስብል የቁጥር ብዛት የውስጥ ዕውሮች አድርጎናል፡፡ ከዚህም በላይ አስቸጋሪና የመፍትሔ ውስብስነቱን በእጅጉ የሚጨምረው ጉዳይ ደግሞ፤ መድኃኒታችን "ዕውር ዕውርን ቢመራው ሁለቱም ከጉድጓድ ይወድቃሉ" ሲል ያስጠንቀቀበትን ቃል በውል ሳናጤነው፤ አንዳችን አንዳችንን እየመራን እጅ ለእጅ በመያያዝ በረጅም ሰልፍ ተቀጣጥለን የመጋመዳችን ጉዳይ ነው፡፡ (ወላጅ ልጆቹን፣ ወዳጅ ወዳጆቹን፣ አስኳላ ተማሪዎቹን፣ ከተማ ኗሪዎቹን፣ መንግሥት ዜጎቹን፣ .. የሚመራበት ሕግ፣ መመሪያ፣ ጽንሰ አሳብና ፍልስፍና መንፈሳዊ አዕማዶችንና የነፍስ መሥፈርቶችን መጠበቅ የማይችለው፥ ሥጋዊው አእምሮ የወለዳቸው ዕውር ሥርአቶች ናቸው)

   ማየት የማይችልን ሰው ሊመራ የሚችለው ግለሰብ ዓይናማ መሆን እንዲገባው ምንም አያወላዳም፡፡ ወደ ርዕሳችን ጨዋታ ዓረፍተ ነገሩን ስንቀላቅለው፤ የነፍስ ዕውርነትን ሊፈውስልን የሚችለው ብቸኛው መድኃኒት የእግዚአብሔር ብርሃን ነው እንላለን፡፡ ነፍስን የሚያሳውራት ጨለማ ደግሞ ኃጢአትን ተከትሎ ይመጣል ተባብለናል፡፡ በዚህ መሠረት ስንቀጥል የእግዚአብሔር ብርሃን ብለን የተጠራነው ኃይል ኃጢአትን ከሥሩ ነቅሎ በመገርስስ ጥቁር መጋረጃውን ሊቀድበት ይገባል ማለት ነው፡፡

   ይሄን የውስጥ ዕውርነትን በመዳሰስ የሚፈውስ መለኮታዊ መዳፍ ክርስትናችን ንስሐ ስትል ትጠራዋለች፡፡

   የእግዚአብሔርን ፍጹም ቸርነት ተስፋ አድርገው ንስሐ የሚገቡ ምዕመናን፤ ጌታ ከመንደሩ ለይቶ አውጥቶ የዳበሰውን ዕውር ሰው ይመስላሉ፡፡ ምክንያቱም "ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሃን" ኢየሱስ ክርስቶስ በምሕረት እጁ ዳስሷቸው፤ አጥርቶ ከማየት የጋረዳቸውን የዓለም፣ የሥጋና የክፉ መንፈስ ጨለማ ይገፍፉታልና፡፡ (የዮሐንስ ወንጌል 1፥9)

   ንስሐ ስንገባ፤ ለዓመፅ ሥራችን ክፍያ ሊሆን ተጠቅራሞ የነበረው የሞት ገንዘብ በመንፈስ ቅዱስ እሳት አመድ እስኪሆን ይቃጠላል፡፡ በዚህ ጊዜ ዙሪያችንን ከብቦ የዘጋው የዲያቢሎስ ጨለማ በእግዚአብሔር የይቅርታ ጸዳል ስለሚሸነፍ፤ ከቅርብም ከሩቅም ሳይቀር ሁሉን መመልከት ይቻለናል፡፡ ዳዊትም የሚመክረን ይሄንኑ ነው፦ "ወደ እርሱ ቅረቡ (ንስሐ ግቡ) [ከዛ] ያበራላችሁማል (ጨለማው ይገለጥላችኋል)፥ ፊታችሁም አያፍርም።" (መዝሙረ ዳዊት 34፥5)

   ስለ ንስሐ የተለያየ ትምህርት የተማሩ አማኞች፤ በቃል ጥሪ የተቀበሉትን የንስሐ ድምፅ ወደ ተግባር ሥጋ መግለጥ ሲቸገሩ ይስተዋላል፡፡ በእርግጠኝነት ክርስቲያኖች በብዛት ካደመጧቸው ስብከቶች መካከል የአንደኝነቱን ደረጃ የሚይይዘው "ንስሐ ግቡ" የሚለው ስብከት ነው፡፡ ሆኖም የትምህርቱ ተደጋጋሚነት ከመለመድ ርቆ የተሻገረ አመርቂ ውጤት አላመጣም፡፡ ስለዚህ ጉዳይ አያሌ አመንክዮቶችን በየዘርፍ በየዘርፉ በመደርደር ጥልቅ ትንታኔ ሊሰጥበት እንዲገባ ቢታወቅም፤ በጽሑፋችን ማዕከላዊ አሳብነት አንድን መሠረታዊና መነሻ ምክንያት ለማስቀመጥ እንሞክር፡፡ ዮሐንስም ይረዳናል፦

"ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና፥ ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም" (የዮሐንስ ወንጌል 3፥20)

   በመግቢያችን እንዳወጋነው የእግዚአብሔር ብርሃን ወደ መላእክት ባሕሪይ በደረሰ ጊዜ፤ ዓመፀኛው መንፈስና ሠራዊቱ ከክሕደትና ከትምክህታቸው ባለመመለሳቸው በመረጡት ጽልመት ውስጥ ተውጠው ቀርተዋል፡፡ በሌላ አባባል የጨለማ ግብር የሚሰኘው ክፋት፣ ምቀኝነት፣ ሁከትና ጥላቻው ጥሟቸዋል፡፡ ታማኙ መልአክ "በያለንበት ጸንተን እንጠብቅ" ሲል ያስተላለፈውን የብርታት መልእክት እነርሱም ሳይሰሙት አልቀረም፡፡ ልቦናቸው ኃጢአትን ከማጠንጠንና ከማፈለቅ በጭራሽ የሚታጎል አይነት አይደለም፡፡ እንደው ተሳስተው ጽድቅና እውነትን አያስቡም፡፡

    ይሄ የመናፍስቱ ወደ ግራ ዘሞ የመጥመም ባሕሪይ በሰዎች ሕልውና ውስጥ ደባል ሆኖ ሲገባ፤ በሰዎቹ እንደ ሰዎቹ ሆኖ ይገለጣል፡፡ መንፈሱን "ባላጋራ" ብለን እንደጠራነው እንዳትረሳ! ዲያቢሎስ በመጀመሪያ ወደ ሰዎች ራሱን አጋርቶ፤ በመቀጠል እርሱን ወደ ሰዎች እንደሚያጋራ ልብ በል፡፡ ጉዳዩ መንፈሳዊ ነው፡፡ ማለት እርሱ ወደ ሰው፥ ሰው ወደ እርሱ የሚያያዝበት ሰንሰለት ረቂቅ በሆኑት በጠባይ፣ በአሳብ፣ በፍላጎት፣ በስሜት፣ በእውቀት፣ በእንዲህ .. እንዲህ መልኩ የሚገለጽ እንደሆነ ማስተዋል ይኖርብሃል፡፡

   ስለዚህ .. ሰዎች ለንስሐ ከሚሰጡት ሰብአዊ አረዳድ ጀርባ ሰፊ ጥናት ያልተደረገበት የመናፍስት ሽሽት እንደሚኖር ከተጨዋወትናቸው አሳቦች አንጻር መጠቅለል እንችላለን፡፡ ወንጌላዊው እንደተናገረው፤ ንስሐ የኃጢአትን ጨለማ የሚገልጥ የእግዚአብሔር ብርሃን በመሆኑ፤ ጨለማን ጎሬያቸው አድርገው ለክፋት ተልዕኮአቸው የሚያደፍጡት ክፉ መናፍስት መኖሪያቸው በቀላሉ ላለማስፈረስ ወጥረው መታገላቸው የሚጠበቅ ነው፡፡ ይህንን የመናፍስቱን ድብቅ ትግል ለመረዳት፤ ከራሳችን ጀምሮ በእምነት ታዛ ሥር እንኖራለን የሚሉ ሰዎችን ሁሉ "በኃጢአት ተይዞ እንደመሞት ያለ ከባድ ዕዳ ከፊታችሁ ሳለ፥ ንስሐ ስለምን አትገቡም?" ተብለው ሲጠየቁ በሚሰጡት ምላሽ ተንተርሰን፤ የክፉዎቹን ስልታዊ ሴራና በባሕሪይ ያለ ግፊት ልናስተውለው እንችል ይሆናል፡፡

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek
446 views19:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 22:20:45 2•  ንስሐ    2.2•  ንስሐ ለምን እንግባ? ክፍል - ፪                 ✞ የኃጢአትን ምሽግ ለማፍረስ ✞    ኃጢአት የሚለውን ቃል በቀጥተኛ ፍቺ ስንተነትን፤ ከእግዚአብሔር ንጹሕ ፈቃድ መለየት፣ የእግዚአብሔርን ፍጹም አሳብና ባሕሪይ መሳት፣ እግዚአብሔር አስቀድሞ መልካም አድርጎ ባየው ነገር ላይ ማመፅ፣ የጽድቅን በጎ ሥርዓትና ትእዛዝ መተላለፍ፣ የቅድስና አነዋወርን መቃወም አሊያ…
287 views19:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 10:29:36 ፬. ዮሴፍና ዮሃንስ

ዮሴፍ ለማርያም በእጮኝነት ስም የተመደበ ባለአደራ ነው። ይህ ሰው በማያውቀው ሁኔታ የማርያምን መፀነስ ሲያውቅ ሊተዋት ሲፈልግ ‘እርሷን ለመውሰድ አትፍራ፣ የፀነሰችው በመንፈስ ቅዱስ ነውና ውሰዳት” ተብሎ ወስዷታል። ዮሓንስ በቀራንዮ “እነሆ እናትህ“ ተብሎ ወስዷታል። ሁለቱ ሰዎች ማርያምን ውሰዱ በመባል አንድ ናቸው፤ አንዱ በጽንስ ሌላው በመስቀል። ዮሴፍ ተወዳጁ በህጻንነቱ እንዳይገደል ከእናቱጋ ይዞት ሸሽቷል። ሄሮድስ አላገኘውም። በመከራው ብዙ ተፈትኗል። ቤተሰብ ይዞ መሰደድን የሚያውቅ ያውቀዋል። ፈተናው “ውሰድ” ከተባለ በኋለ የተከተለው ነው። ዮሓንስ ማርያምን ተወዳጁ በመከራ ሳለ ነው የወሰዳት። እነሆ እናትህ ተባለ። በማርያም እናትነት በኩል የጥምቀትን እናትነት ተመልክቶበታል። በጌታ ሞት እኛ ተወልደንበታል። ስለዚህ በማርያም ውስጥ የዮሓንስ ልጅነት ሲኖር በዮሓንስ ውስጥ የማርያም እናትነት ታውቋል። በዚህ ውስጥ የአብን ወላዲነት የወልድን ልጅነትንም አውቋል። “አባት ሆይ አንተ በእኔ እኔም ባንተ እንዳለሁ እነርሱም በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ” ያለውን ቃል ያስቧል። ዳግም ከተወለድን በኋላ ሰውን በክርስቶስ እንጂ በሥጋው አናውቀውም። ለምሳሌም ማርያምን የምናውቃት ኢየሱስ በእርሷ በሰራው ታላቅ ስራና ጥበብ እንጂ በመልኳ ወይ በዜግነቷ አይደለም። የተነሳው ክርስቶስ በመልክ እንደማንረዳው ሁሉ በትንሳኤው ያሉትንም በመልክ አናውቃቸውም። በቃል፣ በድምጽ ይታወቃሉ። ቃሉም መንፈስና ህይወት ስለሆነ ስንሰማና ስንኖራቸው እናውቃቸዋለን። ዮኃንስ ይህን የመንፈስ ቅዱስ ስርዓት አግኝቶታል። ቃሉን ሰምቶ የሚያደርገው ለጌታ እናቱም ወንድሙም ዘመዱም ነው። ተወዳጇ እመቤትም “እንደቃልህ ይደረግልኝ” በማለቷ ቃል በእርሷ ሥጋ ሆኗል። እናቱ ሆናለች። በዚህ በኩር ናት።

በዮሴፍ ጊዜ ተወዳጁ አልተገደለም። በዮሓንስ ጊዜ ግን ተወዳጁ በፈቃዱ ሞቷል። ዮሴፍ የግርዘቱን ደም ሲያይ ዮኃንስ የመከራውን ደም ተመልክቷል። ማርያም ሁለቱንም ጊዜ ተመልክታለች። ዮሓንስ በራእዩ ሴቲቱ 1260 ቀን እንደተስደደች ጽፏል። ይህ ሶስት ዓመት ከመንፈቅ በዮሴፍ ጊዜ ሆኗል።
ኢትዮጵያ ዮሴፍ ህፃኑና እናቱን ይዞ ከሄሮድስ ተሸሽጎባታል። ግብጽና ኢትዮጵያ መሸሸጊያ ናቸው(መንበረ ማርቆስ)። ይህን ያወቅነው በዮሃንስ የመቅደስ መለኪያነት ነው።መለኪያው ያለው ዮሓንስን ሆኗል (ማርያምን “ፀጋን የሞላብሽ” የሚያስብለን መንፈስ ለእኛም የተሰጠ እንደሆነ ያመለከተን ዮሓንስ ነው።”ቃል ስጋ ሆነ።ጸጋና እውነትን ተሞልቶ በእኛ አደረ” በማለት...በዓለም ያሉ አብያተ ክርስቲያናት ክፍፍል መነሻዎች ይህ የቃል ሥጋ ሆነ ነገር ነው)።

1260 ቀን በሰሜኑ በር 1985 ዓመታት ናቸው። ዓለምም እውነቱን ሲያሳድድና ሲገል እስከዛሬ አለ። ለዚህን ያህል ዘመን ይህ የወንጌል እውነት ተሸሽጎ ነበር። አሁን ከስደት ተመልሷል። እንደ ዮሴፍ በዚህ ተሸሽጓል። እንደዮኃንስ ከዚህ ይነገራል። 1985 ዓመታቱ ተጠናቀዋል። ዮሴፍ ስራውን ፈጽሟል። ዮሓንስ ይቀጥላል። በትንሣኤው “ና ተከተለኝ” ተብሎ በድጋሚ የተጠራ እሱ ነው።ወደ አብ የሚያርገው ተወዳጅ ስለጠራው ሙሉውን መለኪያ አግኝቷል። ‘በመጀመሪያ ቃል ነበር’ ብሎ ከአብ መወለዱን መስክሯል። የማርያምን የአብ ምሳሌነት አውቋል። አግኝቶታልም። ኖሮታልም።

ቅዳሴያችን በቤተልሄም ጀምሮ በቀራንዮ ያልቃል። እንደ ማርያም ስናየው በዮሴፍ ጀምረን በዮሃንስ እንፈጽማለን። ይህ እውነት በህይወታችን ከተፈጸመልን በእውነት ፍልሰታው ለእኛም ሰርቷል። በእምነቱ በዮሴፍነት ላይ ያለም በበአለ ሃምሳ ያለም ይጸልይ። ፍጻሜው ጌታ ነው፤ ይገለጻል። አበው ዮሴፍና ዮሃንስ አብረው ሲቀድሱ የዓለም ፍጻሜ ይሆናል ይላሉ። ሁለቱን በአንድ ሰብእናና ዘመን አግኝተን እየኖርነው አይደል? ኢትዮጵያ የዮኃንስ ራእይ ማእከል ናት። በመቅደሱ ፍጻሜ በቅድስተ ቅዱሳን ነን። በሃያው ክንድ ወይም በአስሯ ቀን ነን። እርሷም መቶሃያው ቤተሰብ የተጉባትና በመንፈስ ቅዱስ የተጠመቁባት ናት። አህዛብን ሁሉ በብረት በትር የሚገዛው ወንዱ ልጅ በዚያ ይኖራል። ለሁሉም እንደየቋንቋው ሊሰማው የሚችል ከነገድ ከቋንቋ የሚዋጅ የፅዮን ድምጽ ይነገርባታል።

፻፳ን በ፲ ስናበዛው ፲፪፻(1200) ቀናትን ይሆናል። ከዋናው የበዓለ ሀምሳ ፶ ቀናት'ጋ ሲደመር ሶስት ዓመት ከስድስት ወር ይሆናል (እራሳቸው መቶሃያው ቤተሰብ ሶስት ዓመት ከመንፈቅ ተሰደዋል። አሁን ይህ እየሆነ ነው። በምስራቁ በር መንፈስ ቅዱስ የወረደው በማርቆስ እናት ቤት ነው። በሰሜኑም እንደዚያው ይሆናል (ኢትዮጵያ በማርቆስ መንበር ናት፤ እዚያ ነን)፡፡ ዛሬ በዓለምና በተለይ በሃገራችን ዘንዶው እያሳደደ ያለው ይህን እውነት ነው። ምእመኗን ካላጠፋሁ ብሎ የከበበው ለዚህ ነው። ለ1260ቀን ውሸቱን እየለቀቀ ያሳድዳል። "ምድር ግን ሴቲቱን ረዳቻት" ይላል ዮኃንስ። ዘንዶው የተፋውን ውኃ ውጣዋለች። እኛ ከተማይቱን ገልጾልን አይተናታል። ከሃያው ክንድ ኅይል ይወጣል። እንደሄደብን ይመጣል። ደግሞም መጥተናል። እስቲ እንደሀዋርያት እንዲገለጽልን የምንፈልገውን ነገር እንንገረው። ፍጻሜው ላይ ነን፤ ሚካኤል ስራ ላይ ነው (ለዛሬ በጸሎት ያላችሁ የዮኀንስ ወንጌልን እያነበብችሁ አስቡን)።

ተጻፈ: በደመወዝ ጎሽሜ (ጋሼ)
ማስታወሻ :- ፲፮ የሚለውን መጽሐፉን ካላነበባችሁ የቁጥር ስሌቱን ጨምሮ ሙሉ መረዳት አይኖራችሁም:: ለአሁን፣ የሆነ ነገር ካገኛችሁበት በቂ ነው:: ዞሮ ዞሮ፣ እስቲ መልካም ቆዩ!

@bemaledanek
1.4K views07:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 10:29:07 ሰሙነ ፲፮
ማርያምና ኢትዮጵያ

ሰሞኑ ለተዋሕዶ ክርስትና አማኞች የፆም ወቅት ነው። የፍልሰታ ፆም! እስቲ አንዳንድ እውነታዎችን እንጨዋወትበት።

፩. የሕያዋን እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም!

ከቶማስ ውጭ ያሉት ሌሎች ሐዋርያት የማርያምን ትንሣኤ ከእርሱ ሰምተው መንፈሳዊ ቅናት ይይዛቸውና ሱባኤ ይገባሉ። ተገለጸችላቸውም። ጾሙ የዚህ መታሰቢያ ነው። እኛ ጾሙን ለሕይወታችን እንጠቀምበታለን። ታሪኩ እንዳለ ሆኖ 'ለሐዋርያት ምስጢር ይከፈልባቸዋል ወይ? ለአንዱ ተገልጾ ለሌላው ሳይነገር የሚቀር ነገር አለ?' ብለን እንጠይቅ። እርገት በመጽሀፍ ቅዱስ ሲመሰጠር የወንድ ስርዓት ነው። የሴት አይደለም። ዝርዝሩ ይቆየን። ሐዋርያትን ሊያስደንቃቸው የሚችለውም ይሄ ነው። በተለምዶ ይሁን ለቃል ካለመጠንቀቅ ባላውቅም የድንግል ማርያም እርገት ከተወዳጁ እርገት'ጋ ተመሳስሎ ይነገራል። የማርያም እርገት ከጌታ እርገት ይለያል። የጌታ ወደአብ፣ ወደክብሩ፣ ወደ አባቱ የገባበት ነው። በሊቀ ካህንነቱ እስካሁን ነፍሳችን ትገለገላለች። ወደ አብ በመግባቱ በምልአት እንደ አባቱ ሆነ። በሰው በኩል ሲታይ “ሰው አምላክ ሆነ “። የእግዚአብሔር ሀሳብ በእኛ ለመታሰብ ቻለ። ይህ የሆነልን በተወዳጁ እርገት ምክንያት ነው። ጳውሎስም ከሰማይ ከወረደው በቀር ወደሰማይ የወጣ የለም የሚለው ለዚህ ነው። የማርያምና የሀዋርያት ግን በትንሳኤው ቢመስሉትም በእርገት ወደ አብ አልሄዱም። በነፍስ ስርዓት ይኖራሉ። ጌታ ተነስቶ ለአርባ ቀናት በኖረው ስርዓት ይቆያሉ። እነሱ የሞትና የሕይወት ቁልፍ ያለው የእግዚአብሔር ልጅ የሰጣቸው ልጅነት አለቻቸው። ስለዚህ ሲሞቱም ፈልገውት እንጂ ሞት ገዝቷቸው አይደለም። ጳውሎስ “ቢሆንልኝ የሞቱን ጥምቀት እጠመቃለሁ” የሚለው በሞት መንገድነት የሚገኝ ታላቅ ምስጢር ስላለ ነው። ልጅነት ካለችህና ሙት ካስነሳህ አንተም ትነሳለህ ማለት ነው (ጠንቋይ ነው ለራሱ የማይሆነው)። ጌታ የኅያዋን እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም። እነማርያም ሕያዋን ናቸው። ጌታ እንዳለው ”አምላክ ሙሴን ሲያናግረው የአብርሃም፣ የይስሃቅ፣ የያእቆብ አምላክ ነኝ” ማለቱን በመጥቀስ የህያዋን አምላክነቱን ተናግሯል። በሞቱ እንደመሰሉት በትንሳኤውም ይመስሉታል። ሞቶ መነሳት ዋንኛ መገለጫው በአንድ ጊዜ ሁሉም ቦታ መገኘትን ነው። አንዱ ስንዴ ሞቶ ሲነሳ ብዙ ሆኖ መውጣቱን ይመለከቷል። ጳውሎስ ስለ ትንሳኤ ሙታን ሲናገር “እኛ ህያዋን ሆነን የምንቀረው ያንቀላፉትን አንቀድምም” በማለት ነው። ታሪክ ጳውሎስ እንደሞተ ይናገራል። እርሱ ግን እስከ ምጽአት ህያው እንደሆነ ይናገራል። ጳውሎስ ትክክል ነው። እነርሱ በዙሪያችን አሉ። እንደ ደመና ከበውናል። የትንሳኤን ትምህርት ምስጢር የሚያሰኘውም እንደዚህ አይነት በመኖር ብቻ የሚታወቁ ነገሮች ስላሉት ነው። በዚህ የተነሳ ማርያምም ተነስታለች። ሁሉም ግን በራሱ ተራ ነው።

፪. ቶማስ

ሀዋርያት በቶማስ ያዩት ግን ያላወቁት አንድ ጉባኤ አለ። ይህም ከእርሱ በስተቀር ትንሣኤውን ያመኑት በቃልና በመገለጽ ነው። እንደ ቶማስ በመንካት አላመኑም። የተወዳጁን ጎን በመንካት የሚያነጋግረው ኢየሱስ እንደሆነ አውቆ አመነ። ያ ጎን በቀራንዮ ደምና ውኃ የፈሰሰበትና አባት በልጁ አምጦ እኛን የወለደበት ነው። ማየ ገቦ እንዲል መጽሀፍ። ከተወለድንበት ማህጸን ነው ማለት ነው። እናት!

የተነሳው ተወዳጅ ስጋና አጥንት ከመስቀል በፊት ከነበረው ስጋው የሚለይበት አንድ ነገር አለ። የተነሳው የሞት አገልግሎት አይከናወንበትም። ቀን በጨመረ ቁጥር ለሞት አይቀርብም እንደማለት ነው(በትንሳኤ የማያስፈልጉ የሰውነት ክፍሎችና ስርዓቶች አሉ። የሆድ እቃ ላያስፈልግ ይችላል እንደማለት ነው) እኛ ወደእርጅና እንገሰግሳለን። ጌታ ከተነሳ በኋላ ይህን አስቀርቶታል። ከክብር ወደ ክብር እየሄደ በመጨረሻም እየረቀቀ ሄዶ ወደ አባት ገብቷል። መርቀቅን ነው ማረግ የምንለው። ቶማስ ይህን አካል ነክቶት አምኗል። ይህ የነካው ስጋ ከማርያም የነሳው ስጋ ነው። ይህ ስጋ በነፍስ ስርዓት ውስጥ ያለ ነው።

፫. መቶ ሃያው ቤተሰብ

ጌታ ካረገ በኋላ ያሉት አስሩ ቀናት በሰሜኑ የመቅደሱ በር ሲለኩ 16.4 ዓመታት እንደሆኑ ከዚህ በፊት አውስተናል። ይህ የቅድስት ቅዱሳን ቁጥር አብን ይወክላል። ከአስሩ ቀን መንፈሱን ልኮ ወልዶናል። ማርያም የአብ ምሳሌ የተባለችውም በዚህ ወላጀነቷ ነው። በ16.4 ዓመቷ ወልዳዋለች። ይህ በስጋ ነው። በእነዚያ አስር ቀኖች ውስጥ 120ው ቤተሰብ እየጸለዩ ነበር። ማርያም እዚህም አለች። በስጋዋ የሆነውን ነገር የተረዳችውና ያወቀችው በመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ነበር። የዚህ እውነት ምሳሌነቷን በሥሉስ ቅዱስ ተረጋገጠላት። ይህ የፅዮን እናትነት ነው፤ ሁሉም የሚወለድበት። 16.4 ለእርሷ ብቻ ታውቆ አልቀረም። ሁሉም ይህን እናትነት አገኙት። ተገለጸላቸው።

አጠቃላይ መቅደሱ በዘመን ሲለካ 1968 ዓመታትን ይሆናል (ፖለቲካችን ከመቅደስ የወጣበት ዘመን ነው)።መቶ ሀያው ቤተሰብ የኖራት ፲ ቀን ወይም 16.4 ዓመታት ቅድስተ ቅዱሳን ናቸው። ሁሉም ይህንን የወላጅነት ስርዓት አግኘተውታል። ተገልጾላቸዋል። በሌላ አባባል እያንዳንዳቸው 16.4 በመሆን ዓለምን ለውጠዋል። ስሌቱ ፦
1968 ÷ 120 = 16.4

በበዓለ ሀምሳ በልዩ ልዩ ቋንቋዎች ድምጹ ተነግሯል። ይህ ሁነት በሰሜኑ በር ለ1968 ዓመታት ክርስትና ለዓለም ሁሉ ተሰብኳል። በልዩ ልዩ ቋንቋዎች ተመስክሯል። እኛም ይህ እንዲገለጽልንና እንድንኖረው ያስፈልጋል። ስሌቱም የሚናገረው ይህንን ነው (በነገሬ ላይ አንድ ሰው ለመብቃት 16 ዓመት ይፈጅበታል ማለት አይደለም። ይህ በጉ በሄደበት ሁሉ ለሚሄዱት የተሰጠ ነው። ከእነሱ የተነሳ ይህን በማመን የምናገኘውን ጸጋ ሰው ሆኖ በተገለጸበት ምልዓት መጠን ለመግለጽና ምን ያህል አምላክ እየሰራ እንደሆነ ለማወቅ እንዲረዳን ነው። ሁሉ በእርሱ ሆኗል። ያለ እርሱ የሚሆን እንደሌለም እንድናይበት ነው።)
852 views07:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 20:31:13 + በጾመ ፍልሰታ እንፍለስ + እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ አስቀድሞ ጤናውና ሰላሙ ይኑራችሁ፡፡ ስለርሱም ዘወትር አመስግኑ፡፡ ሌላው ሁሉ በጊዜው ይደርሳል፡፡ ፍልሰታ በጥሬ ቃል ፍቺው መፍለስ ከሚለው ግስ የተነሣ ሲሆን፤ ከአንድ ቦታ ወደ አንድ ቦታ መዛወር፣ መንቀሳቀስ፣ መጓዝ የሚለውን ትርጉም ይይዛል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤና…
922 views17:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 20:30:43 + በጾመ ፍልሰታ እንፍለስ +

እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡ አስቀድሞ ጤናውና ሰላሙ ይኑራችሁ፡፡ ስለርሱም ዘወትር አመስግኑ፡፡ ሌላው ሁሉ በጊዜው ይደርሳል፡፡

ፍልሰታ በጥሬ ቃል ፍቺው መፍለስ ከሚለው ግስ የተነሣ ሲሆን፤ ከአንድ ቦታ ወደ አንድ ቦታ መዛወር፣ መንቀሳቀስ፣ መጓዝ የሚለውን ትርጉም ይይዛል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤና እርገት ጋር የቃልኪዳን ትስስር ያለው ልዩ ጾም ነው፡፡

ጾመ ፍልሰታ በዐሥራ ስድስት ቀናት ውስጥ ተጀምሮ የሚያልቅ ቆይታ ሲኖረው ይኸውም መግቢያ ቀንና መውጪያ ቀን ያለው ሁለት ሱባዔ ይሆናል፡፡ አንድ ሱባዔ ሰባት ቀን ሲሆን፤ ሁለት ከሆነ ዐሥራ አራት ቀን ይሆናል፡፡ ሁለቱ የመጀመሪያው መነሻና መፈጸሚያ መድረሻ ቀናት የጾሙ መግቢያና መውጪያ ጊዜያት ይሆናሉ፡፡ ጾሙ ደቀመዛሙርቱ እንደያዙት ሱባዔ፤ ሰማያዊ መልስ፣ የመንፈሳዊ ሚስጢር መገለጥና የበረከት ስጦታ የምናገኝበት ጾም ነው፡፡ ሐዋሪያቱ ሰማያዊ መልስ ጠይቀው አግኝተውበታል፡፡ ሚስጢር የሆነባቸውን ጉዳይ በመንፈሳዊ መገለጥ ፈትተዋል፡፡ በመጨረሻው ስለ እመቤታችን ትንሣኤ የበረከት ምልክት የሚሆነውን ሰበን ሐዋሪያው ቶማስ ተቀብሎአል፡፡

እኛም መልስ ያጣንለት ጥያቄ ይኖረናል፡፡ ሚስጢር ሆኖ አልገለጥ ያለን ጉዳይ ይኖረናል፡፡ የበረከት ማነቆ በሰላቢ መናፍስት፣ በቡዳ መናፍስት፣ በመተት መናፍስት ምክንያት ደርሶብን፤ የልፋታችንን ከንቱነት እያሰብን የምንገኝ እንኖራለን፡፡ በጾመ ፍልሰታ ታዲያ፤ ከነፍስ፣ ከልብና ከአሳብ በተሰበሰበ አንድ የፍቅር ምዕራፍ ከፈለስን፤ ብዙ ቦታ ላይ አልገጥም ብሎ ያሰቃየን ጉዳይ ቅርጹን ይይዛል፡፡

ጾመ ፍልሰታን እንዴት እናሳልፍ ?

፩. በፍቅር

የመንፈሳዊ ሕይወት ግንባታ መሠረት "ፍቅር" ነው፡፡ ሃያ ዐራቱን ሰዓት ሁሉ ብንጾም፣ ከደመና በላይ ጮኸን ብንጸልይ፣ አጥንታችን እስኪሰበር ብዙ ብንሰገድ፣ ኃይል ከሰማይ እንደዝናብ ቢወርድ፣ የቱንም ያህል ደረጃ ነገሩ ቢሳካ፤ ሕይወታችን ፍቅር ከሌለበት ሁሉ ከንቱ፥ የከንቱ ከንቱ ነው (ይሄ፥ ጥሬ አባባል የሚመስለው፥ ለብዙ ሰው ነው)፡፡ (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፥2) ፍቅር የሌለው መንፈሳዊነት ወግ ይሆናል፡፡ ዘልማድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ፍቅር ሲኖረው መንፈሳዊነቱ ላይ ጠንካራ እምነት ይገኝለታል፡፡ በጣም ግልጽ ጉዳይ ነው፡፡ ወድደን የምናደርገው እና ተገደን አሊያ ማድረግ አለብን ብለን አስበን የምንከውነው ጉዳይ መካከል የራሱ የሆነ ርቀት አለ፡፡ ዐሥራ ስድስቱ ቀናት እየጣፈጡህ ማለቃቸውን እንኳ ሳታስተውል እንድትፈልስባቸው፤ መጀመሪያ ቀን አንድ ስትል፥ ከፍቅር ጀምር፡፡ እውን የእመቤታችን ፍቅር ነፍስህን ይዞት፤ ትንሣኤዋ ልብህ ላይ ተቀምጦ፤ የሐዋሪያቱ ሱባዔ አሳብህ ውስጥ ሆኖ ክብሩን ባነገሠ ምግባረ ክርስትና መሄድ ስትጀምር፤ ቀኖቹ እንዲያልቁ ሳይሆን እንዳያልቁ በስስት እያየህ እያንዳንዷን ቀነ ደቂቃ እየነጠልክ ትጾማቸዋለህ፡፡

፪. በአምልኮትና በጸጋ ስግደት

ስግደት ጸሎት ማጽደቂያና ማሰሪያ ነው፡፡ መሥዋዕት የማቅረቢያ አንድ መንገድ ነው፡፡ የመገዛትና የማክበር መግለጫ ነው፡፡ እነሆስ፥ "ተወዳጂቱ ቤዛዊት ዓለም ሆይ፥ ቢመጣም ባይመጣም፣ ቢሠራም ባይሠራም፣ ቢከናወንልን ባይከናወንልም፣ ቢደርስም ባይደርስም በእውነትም እንወድሻለን!" የምንለው በጸጋ ስግደት በኩል ነው፡፡ የሚሰግድ ሰው የፍቅሩ ኃይል ላይ ማኅተም አለው፡፡ ማረጋገጫ አለው፡፡ ዋጋ ስለመስጠቱ መታያ ነው፡፡ እንኪያስ፥ የእመቤታችንን ስግደት በጾመ ፍልሰታ ከዘወትሩ ስግደት ጋር አስተባብራችሁ በደንብ ስገዱ፡፡

፫. በጸሎት

ጾመ ፍልሰታ የእመቤታችንን ወደ አፀደ ሕይወት መፍለስ እያሰብን የምንጾመው ከሆነ ዘንዳ፤ እንግዲያው እኛም በመንፈሳዊ ጉዞ በኩል ወደላይ መፍለስ አለብን፡፡ መጨመር አለብን፡፡ የአምልኮት ልምምድ፤ ጊዜ፣ ብዛትና አቅም መጨመር አለብን፡፡ ሁለቴ የምትጸልየው ሦስቴ፥ ሦስቴም ከሆነ አራቴ፥ አራቴም ከሆነ አምስቴ ለማድረግ እንጀግን፡፡ በሥጋ ላይ ያለን ከፍታ ለማምጣት ዓለም ሁሉ ይሮጣል፡፡ የነፍስ ብልጽግና ግን ለተመረጡት ነው፡፡ ድምፁን ለሚሰሙት .. ለበጎቹ! (ውዳሴ ማርያምን ጸሎት በገባችሁ ልክ ብትጸልዩ ጥሩ ይሆናል፡፡ ለምሳሌ ቀን 6:00 መልክአ ሚካኤል ሲነበብ፤ አስቀድማችሁ ውዳሴ ማርያምን በመቀጠል የመልአኩን መልክአ መጸለይ፡፡ በሥራና ሌሎች ጉዳዮች የተወጠራችሁ ሰዎች እስከምትችሉት ያህል ጸልዩ፡፡ ከፍቅር መሠረት ላይ መነሣት የሚገባን ለዚሀ ነው፡፡ ፍቅሩ ካለ እስከ የትኛው አቅም ልክ እየሄድን መበርታት እንዳለብን ማንም ሳይጠቁመን እናውቀዋለን)

፬. ክፉውን በመዋጋት

ጥሩ ንቃተ ሕሊና የታደለ ሰው መናፍስት ብርታት የሚሆኑ የጽድቅ ጠላቶች እንደሆኑ ያውቃል፡፡ በተለያየ መንገድ ፈተና ውስጥ የሚከቱን አጥፊ ኃይሎች ባይኖሩ ኖሮ ማን ያበረታናል? .. አባቶቻችን መከራ ሲርቃቸው ተጨንቀው ያለቅሱ ነበረ፤ እግዚአብሔር የተዋቸው እየመሰላቸው፡፡ በአንክሮ ስንገንዘብ፤ ያለ ፈተናና ትግል ክርስትና ውስጥ መንፈሳዊነት ለካ አይበረታም፡፡ የተዘጋብንን ለማስከፈት በሰገድን፣ በጸለይን፣ በመቁጠሪያ በተዋጋን ቁጥር ወደ አርያም ሰማይ ምን ያህል እየፈለስን እንደሆነ ብዙዎቻችን አይገባንም (ችግር ችግሩን ስለምንቆጥር)፡፡ እስኪ ከትናንት ዛሬ የመጣንበትን በደንብ እናጢነው፡፡ ስግደት አናውቅም ነበረ አሁን እንዴት ሆነናል? ጸሎት በርትተን አንጸለይም ነበር አሁን ከምን ደርሰናል? .. መናፍስቱን በተዋጋንበት ልክ፤ የኛም መንፈሳዊ ለውጥ በዛው ልክ ከፍ ይላል፡፡

በሉ ስለዚህ በጾመ ፍልሰታ መናፍስቱ ላይ መለኮታዊ ማዕበል አውርዱ፤ ዝመቱ፤ በደንብም አድክሟቸው፡፡ በነገራችን የፍልሰታ ጊዜ የሱባዔ መልክ ያለው ጊዜ ነው፡፡ ሱባዔ ደግሞ ብቸኝነት ይፈልጋል፡፡ አርምሞ ይወዳል፡፡ ከሥጋ ወከባና መዝናኛ መለየት ደስ ይለዋል፡፡ ስለዚህ .. የነፍስ ቆይታ ላይ ትኩረት እንስጥ፡፡ ከለመድናቸው የሥጋ ጉዳዮች ሸሸት እንበል፡፡ ዘፈን ከመዝሙር አናምታታ፤ ጸሎትን ከቂም አንቀላቅል፤ ዓለማዊን ከመንፈሳዊ አናወሳስብ፡፡ ምክንያቱም ተወዳጁ.. እንኳን በሰላሙ ሰዓት .. በመሰቀል ጭንቅ ሳለም .. ቀላቅለው የሰጡትን መጠጥ ሊጠጣው በፍጹም አልወደደም!

፭. በመቀደስ

ጾመ ፍልሰታ ጊዜ ውስጥ የሁለት ሳምንታት ቅዳሴዎች አሉ፡፡ በመሆኑ የምንችል ሰዎች ስናስቀደስ፤ በዛውም መቀ'ደስን እንወቅ፡፡ ንስሐ ገብታችሁ ያለ ቅዱስ ቁርባን ቁጭ ያላችሁ ወገኖቼ መቼ ልትቆርቡ ነው? ምን እየጠበቃችሁ ነው? ምንድነው'ስ አላስቆርብ ያላችሁ? ..

በነዚህ የፍልሰታ ሳምንታት መቁረብ እጅግ ታላቅ ጥቅም አለው፡፡ ምክንያት ካልን፤ አንደኛ ጾሙ በራሱ የሱባዔ መልክ እንዳለው ተነጋግረናል፡፡ ሱባዔና ቅዱስ ቁርባን ደግሞ እጅ ለእጅ ተያይዘው የሚሄዱ ባልንጀሮች ናቸው፡፡ ሁለተኛ፤ ፍልሰታ የቃልኪዳን በረከት ያለው ጾም ነው፡፡ ይሄ በረከት ደግሞ ስለመኖሩ ራሱ የሚታወቀን በቅዱስ ቁርባን ስንቀደስ ነው፡፡ ሦስተኛ፤ ጾሙ ውስጥ መንፈሳዊ መገለጥ ታሪካዊ መዝገብ ሆኖ ይገኛል፡፡ የዚህ የመገለጥ ቁልፍ መክፈቻ ደግሞ የመድኃኒቱ ሥጋና ደሞ ነው፡፡ እናሳ? .. እንዴት ነው ምን ወሰናችሁ?
765 views17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 20:30:16
+ በጾመ ፍልሰታ እንፍለስ +
681 viewsedited  17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 21:21:47 አንዴ ብቻ ይንኩት አለማትን የፈጠረውን ጌታ
በሕይወት ያመስግኑ ፣ ስትነኩት የሚወስዳችሁ
ቦታ በጣም ይጠቅማቹሀል!

.            ✦              ‍ ‍ ‍ ‍                  ,    

.             .   ゚     .                    .           .            

 ˚                     ゚     .               .      ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ,                * .                    .           ✦           ˚              *                      .  

.             .   ゚     .             .

      ,       .                                                              *         .           .             .                                                               ✦      ,         *          ,    ‍ ‍ ‍ ‍               .            .                                   ˚          ,                              .                 

         

             *          ✦                                .                  .        .        .                .           .            

 ˚                     ゚     .               .
38 views18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 11:54:57   አንድ በእግዚአብሔር ሕያው አምላክነት በእውኑ አምናለሁ የሚል ግለሰብ፤ ንስሐ በሚባል መንፈሳዊ መንገድ ላይ ለመጓዝ ሲዘጋጅ፤ በኑሮና በዕድሜው ውስጥ ከተፈጸመው የኃጢአት ሥራ ጀርባ መግፍኤ የሆነ ጉልበት ያሳደረ ክፉ መንፈስ እንዳለ ማወቅ ያስፈልገዋል፡፡ ምክንያቱም ንስሐ በመግባት ከሚገኙ መሠረታዊ ሰማያዊ ትሩፋቶች መካከል አንዱና ዋነኛው፤ ኃጢአትን እንደ ምቹ ምሽግ ተጠቅሞ በባሕሪይ የሚደበቀውን ዲያቢሎስ በቀጥታ መቃወምና መጣል ስለሆነ፡፡ ባለ ራእዩ የሚለንን እንመልከት፦

"ቀንና ሌሊትም በአምላካችን ፊት የሚከሳቸው የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሎአል።" (የዮሐንስ ራእይ 12፥10)

   አጥፊው መንፈስ ትልቁና መድረሻ ሥራው፣ ዓላማው፣ ራእዩና ፍላጎቱ፤ በጽድቅና በኩነኔ መካከል ባለ የክስ መዝገብ ላይ ኃጢአታችንን አብዝቶ መደርደር ነው፡፡ በእያንዳንዷ ዕለት ላይ (ቀንና ለሊት) ኃጢአትን በኛ ፈቃድና ውሳኔ እንድንሠራ በተለዋዋጭና በዘርፈ ብዙ መናፍስታዊ ስልቶች በየደቂቃው በመፈተን፤ በእግዚአብሔር ፊት የሚነበብ የበደልን ጽሕፈት በስማችን ይከትባል፡፡

   ይህ በእንዲህ ሳለ፤ እግዚአብሔርን በአፍ አመልካለሁ ብለን በተግባር ስንተወው፤ በአንጻሩ ሰይጣንን በአፍ ከድቻለሁ ብለን በተግባር ኃጢአትን ያለምንም ሥጋትና ቅደመ ሁኔታ በመፈጸም አብረነው ስንኖር፤ "እኔ መንፈስ የለብኝም" እያልን፤ የ'የለብኝም" ድምፃችንን እንደ ጭዳ ቆጥሮ ከማንነታችን ኋላ ይበልጥ ተሰውሮ እንዲገባ እና ራሳችን ቀድመን እንደሰየምንለት "እንደሌለ ሆኖ" የሚያደፍጥበትን ጊዜ እንዲጨምር፤ አቅሙን የምናበልጽግለት ሰዎች ጥቂቶች አይደለንም፡፡

   የመናፍስት ብቸኛ መግለጫና ኃይል የሆነውን ኃጢአት ዘወትር እንደልብ እየሠራን በእግዚአብሔር የጽድቅ ነገራት ላይ ድንዝዝ ብለን ስንቀመጥ፤ "ምንድነው ነገሩ? ለምንድነው በእምነት ሕይወቴ ውስጥ በእውነተኛ ምግባር መመላለስ ያቃተኝ? በእርግጥ የኃጢአት ራስ ከሆነው የዲያብሎስ መንፈስ የጸዳሁ ሰው ብሆን ኖሮ ፥ኑሮዬ ታዲያ ከጥፋት ገጽታዎች ስለምን ጸድቶ አይታይም? በአምላክ ላይ ያለማቋረጥ ዓመፃን እያስነሳሁ የምኖር መሆኔን በሚገባ ሳውቅ፥ የዓመፅ መሠረት የሆነው ክፉው መንፈስ የለብኝም ለማለት እንደምን ይቻለኛል?" ብለን በረጅም ጥሞና ተረጋግተን መመርመር ገና አልጀመርንም፡፡
 
    ዓለማችን በዚህ ዘመን ባለ ዕድሜዋ ኃጢአትን ሥር በሰደደ አኳኋን በብዙ ለምዳና የመኖር አንድ አካል አድርጋ፤ ከትውልዶች ፊተኛ የለውጥ ግስጋሴ ጋር አብሮ ቅርጽና ይዘት እየለወጠ በሚከተል የእርግማን፣ የርኩሰትና የክፋት ገጽታዎች የተሞላች ስትሆን፤ ይኸውና አሁን የጽድቅ እውነት ኃጢአት፥ የኃጢአት ውሸት ደግሞ ጽድቅ ሆኖ ተገላብጦ ቁጭ ብሏል፡፡
 
    አምላካዊ መሥፈርት የሆኑ የቅድስና እውነታዎች ነጻነትን እንደሚገፍፉ የባርነት እስር ቤቶች በአእምሮ ስሌት ተቆጥረው፤ በሥጋ ምቾት ላይ የተለጠፉ ኃጢአቶች የየዕለት ሽርፍራፊ ክስተቶቻችን ሆነው እንዲዛመዱን፤ በእግዚአብሔር የተቀደሱ አምባዎች ላይ መቆም በምድር የሚገባንን የቅንጦት ኑሮ እንዳንኖር የጎታችነት ቀንበር የሚያሳርፍ ተጽዕኖ እንዳለው ክፉ መናፍስቶች በቀላልና ለመቀበል በሚስማማን ጥቁር ጥበብ ካሳመኑን አያሌ ዘመናት አልፎዋል፡፡

    በተለይም በ17ተኛው ክፍለ ዘመን ከተነሳው፥ የኢንዱስትሪ ሥልጣኔን ሽፋን አድርጎ ከተቀጣጠለው የርዕዮት ሽግግር ወዲህ፤ የፉክክር መድረክ እንድትሆን አብዮታዊ ቅርጽ በወጣላት ዓለም ውስጥ አሸናፊ ለመሆን፤ የርኩሰትንና የዓመፃን ግብራት መፈጸም እንደ ተራ የተለምዶ ክብደት እየተዘመነ፤ "ሁሉም ሰው ኃጢአት ይሠራልና እኔም በዚህ ሁሉነት ውስጥ የደርሻዬን ኃጢአት ልውሰድ" በሚል ጋርዮሻዊ አኗኗር ሁላችን እየተመራን፤ የነፍሳችንን ዘላለማዊ ጩኸት አፍነን የሥጋችንን ጊዜያዊ ሹክሹክታ አድምቀን በመስማት ወደ ጨለማው ጠለል በዝግታ አንድ በአንድ ስንወርድ እንገኛለን፡፡

    በእውነት አስቸጋሪው የጥፋት ዘመን ላይ ደርሰናል፡፡ ኃጢአትን በመልመድ የኖርንበት ጊዜ የመልካምነትን ፍቅርና መሥዋትነት ከጠባያችን ውስጥ ደምስሶ፤ "በአንድነትም የማይጠቅሙ ሆነዋል፤ ቸርነት የሚያደርግ የለም፥ አንድ ስንኳ የለም" ለሚለው የሮሜው ቃል መጽደቂያ ፍጻሜ አስገኝቷል፡፡ ኃጢአትን በመልመድ የቆየንበት ኑሮ የእግዚአብሔር ረድኤት በእጅጉ ርቆበት፤ የማይነዋወጽ ሰላም የምንለው የቅድስና አንድ መልክ "በበረሃ ውስጥ እንደሚፈልቅ ምንጭ" በጣም ውድ ሆኖብን ይገኛል፡፡ ኃጢአትን በመልመድ ያሳለፍንበት ቸልተኛ ዕድሜ በሁላችን ታሪክ ላይ ተመሳሳይ ሆኖ ሲገኝ፤ ቅዱስ መሆን ተአምር እስከሆነበት ጥግ ድረስ ርኩሰት ተላምዶን፤ ስለ ነፍስ መጨረሻ መጨነቅ እያቃተን፤ የደመወዝ ቀን መድረሻው እያስጨነቀን፣ የሥጋ ድሎት መጀመሪያው እያስጨነቀን፤ የውስጥ ሕልውናችን ባላወቅነው ደባል ጠላት በአዚምነት ግርዛዜ መካከል ተሸፍኖ እንዳለ ሳይገባን እንኖራለን፡፡

   ንስሐ፥ በኃጢአት ውስጥ የኃጢአት ኃይል ሆኖ የመሸገው ርኩስ መንፈስ በኛ ሕይወት ውስጥ የሚደበቅበትን የማድፈጫ ቦታ እንዲያጣ ያደርገዋል፡፡ በሚገባ ጸድቶ የተወለወለ ጠረጴዛ ላይ ቆሻሻን የምትፈልግ ዝንብ ልታርፍና ልትቆይ አትችልም፡፡ ሆኖም ጠረጴዛው በሚገባ ካልጸዳ፤ ባልጸዳው የቦታ ክፍል ላይ አንዣባ ሄዳ ታርፋለች፥ ትቀመጥማለች፡፡

   ምሳሌውን ወደ መንፈሳዊው እውነት ስናመጣው፤ ዲያቢሎስ ኑሮአችን ውስጥ ተመሳስሎ ገብቶ ራሱን ለመከለል የሚጠቀምባቸው መደበቂያዎች ንስሐ ያልገባንባቸው የኃጢአት ታሪኮቻችን በሙሉ ናቸው፡፡ (ልብ ውስጥ እስኪሰርጽ ተደጋግሞ ይነበብ)

   ከእግዚአብሔር ፈቃድ የተለየንበት፣ የእግዚአብሔርን ንጹሕ አሳብና ባሕሪይ የሳትንበት፣ በእግዚአብሔር መልካም ነገር ላይ ያመፅንበት፣ የቅድስናን ሕግ የጣስንበት ማንኛውም አስተሳሰብ፣ አነጋገርና አኗኗር ሁሉ፤ ከሥጋዊ ኑሮአችን የተደበቀ የጠላት መንፈስ መጋረጃ አድርጎ የሚከለልባቸው የዲያቢሎስ መጠለያዎች ናቸው፡፡ ስለዚህ ንስሐ በገባን ቁጥር እያፈረስን የምንሄደው የኃጢአትን ክምር ተራራ ብቻ ሳይሆን ከተራራው (ፊትና ጀርባ) ሆኖ በተጨባጭ በማይታይ ገመድ እንዳንርቅ ጠፍንጎ ያሰረንን ኃይል ነው፡፡

   አገላለጻችንን በጳውሎስኛ አጻጻፍ መልክ ብናሲዘው፤ ንስሐ ማለት በኛ ውስጥ አድሮ እኛ ሳንፈልግ የምንሠራውን፥ ደግሞ ፈልገን የማንሠራውን ሥራ እንድንፈጽም ምክንያት የሚሆን ኃጢአትን የሚያስወግድ መለኮታዊ መሣሪያ ነው፡፡

   ወይንም ደግሞ የራእዩን ጥቅስ መግቢያ በራችን አድርገን ንስሐን ብናይ፤ ንስሐ ቀንና ሌሊት በአምላካችን ፊት የሚከሰንን የወገኖቻችን ከሳሽ፤ የኃጢአት መዝገቡን የሚያሰፍርበትን ሰነድ የሚቀድ የእግዚአብሔር መሐሪ እጅ ነው ልንል እንችላለን፡፡

   (እናስተውል!) ካለ ንስሐ በምንመራው ሕይወት ውስጥ፤ የዲያቢሎስ እርምጃ ከኛ አንድ እርምጃ የሚቀድምበትን ዕድል ያገኛል፡፡ በሌላ አነጋገር ንስሐ ባልጎበኘው የዕድሜያችን ዘመናት ሁሉ ላይ መናፍስት ወደፊት ቀድመው በመጓዝ ፈቃዳቸውንና እቅዳቸውን በኛ ላይ ለመፈጸም የሚያስችል ጥንካሬና አቅም አላቸው፡፡ ምክንያት? .. የእግዚአብሔር ኃይል ጽድቅ ነው ከተባለ፤ እንኪያሳ የዲያቢሎስ ኃይል ደግሞ ኃጢአት ይሆናላ፡፡ በመሆኑም በንስሐ ያልተገረሰሱ የኃጢአት ጊዜዎቻችን ራሳቸውን የቻሉ ዲያቢሎሳዊ ጉልበቶች ሆነው ለክፉው መንፈስ ያገለግላሉ፡፡

ወደ ሥጋና ደሙ መጓዛችንን እንቀጥላለን. . .
#ጸባኦት_ይከተላችሁ
@bemaledanek
817 views08:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ