Get Mystery Box with random crypto!

በኩር ጋዜጣ Bekur Newspaper

የቴሌግራም ቻናል አርማ bekurnewspaper — በኩር ጋዜጣ Bekur Newspaper
የቴሌግራም ቻናል አርማ bekurnewspaper — በኩር ጋዜጣ Bekur Newspaper
የሰርጥ አድራሻ: @bekurnewspaper
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.53K
የሰርጥ መግለጫ

የሰኞ ጋዜጣዎ

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-30 06:06:00
1.1K views03:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 06:05:38 በተባበረ ክንድ ጠላትን ድል መንሳት ይቻላል!

ነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም
በተናጠል የተኩስ አቁም ስምምነት ለወራት ከግጭት ርቆ የቆየው የሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ጦርነቱን በሰላም ውይይት የመፍታት አዝማሚያ ታይቶበት እንደነበር ይታወሳል:: በተለይም በፌዴራል መንግሥት በኩል የሀገርን ጥቅም ባስከበረና ኢትዩጵያን ባስቀደመ የሠላም ውይይት ችግሩን ለመፍታት በየትኛውም ቦታ እና ያለ ቅድመ ሁኔታ ዝግጁ መሆኑ በተደጋጋሚ ገልፆል::
ይሁን እንጅ ከአመሠራረቱ ጀምሮ በውይይት ችግሮችን የመፍታት ልምድ የሌለው እና ጦርነትን መነሻ አድርጎ የመጣዉ አሸባሪዉ የትግራይ ወራሪ ቡድን ውጤት የማያመጡ ቅድመ ሁኔታዎችን በመደርደር ለሠላም የሚደረገውን ጉዞ እንደ ልማዱ አጨናግፎታል:: ሁሌም ተጎጂ መስሎ በመቅረብ አለማቀፉን ማህበረሰብ የማወናበድ ልማድ ያለው ቡድኑ ይፋዊ የሆነ ጦርነትም ከፍቷል:: አሸባሪ ቡድኑ ካለው የቆየ ባህሪይ አንፃር ቀድሞውንም ቢሆን ለሠላም ውይይት ዴንታ የማይሠጥ መሆኑን አስመስክሯል::

መንግሥት እስከአሁን ለሠላም ሲባል የሄደበት ርቀት በመልካም ሊነሣ ይገባዋል:: ይሁን እንጂ ለሀገር ጥቅም ቆሞ የማያውቀው አሸባሪ ቡድኑ ከሀገሪቱ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመወገን ዳግም ጦርነት ከፍቷል:: ወራሪ ቡድኑ ከዓመት በፊት በአማራና አፋር ክልሎች በከፈተው ወረራ በርካታ ሰብአዊና ቁሣዊ ውድመት ማድረሱ የሚታወስ ነው:: ወራሪ ቡድኑ ትግራይ ተነስቶ ሰሜን ሸዋን እስኪረግጥ ድረስም ይሠራው በነበረው የሀሠት ፕሮፕጋንዳ አብላጫውን ወስዶ እንደነበረ ሊታወስ ይገባዋል:: ያልተቆጣጠረውን ከተማ ተቆጣጥሪያለሁ፣ ይህን ያህል ሰራዊት ማርኪያለሁ፣ ደምስሻለሁ በሚሉ የሀሰት ወሬዎቹ ከሆነው በላይ ሆኖ ነበር:: በሚፈበርከው ወሬ ወራሪ ቡድኑ የጥቃት አድማሱን ያሰፋበት አጋጣሚ ተፈጠሮ እንደነበር ማስታወስ ይገባል::
አሁን ዳግም በጀመረው ጦርነት እንደ ከዚህ ቀደሙ በሀሰት ፕሮፖጋንዳ መረበሽም መዘናጋትም አይገባም ብለን እናምናለን:: በመገናኛ ብዙሃን የሚተላለፉ መረጃዎችንም በጥንቃቄ መመልከት የሚያስፈልግበት ወሳኝ ወቅት ላይ እንደምንገኝ መገንዘብ ግድ ይላል:: ወራሪ ቡድኑ ራሱ የጀመረውን ጥቃት በተጠቃሁ መግለጫ አጅቦታል:: በዚህ መግለጫና በጀመረው ጦርነት መላው ኢትዩጵያዊያን ግራ ሣንጋባ ዳግም በአንድነት ቆመን ለማሸነፋችን ጥርጥር ሳይገባን ልንታገል ይገባል::

ኢትዩጵያዊያን ከዚህ የጥፋት ቡድን የሚሰነዘርን ማንኛውንም ተግባር በፅናት ታግለን የማሸነፍ አቅሙ እንዳለን መገንዘብ ይጠይቃል:: ይህም የሚሆነው እንደቀድሞው ታሪካችን በጋራ ቆመን ጠላቶቻችን በመፋለም ነው::

ዜጐችን ከጥቃት የመጠበቅ ሀላፊነት ያለበት መንግሥት ሀገርን የማዳን ሕጋዊ፣ ታሪካዊና ሞራላዊ ግዴታውን በተገቢው መንገድ መወጣት ከመቸውም ጊዜ በላይ ይጠበቅበታል:: ይህንንም ጀግናዉ የሀገር መከላከያ ሰራዊትና ሌሎች የፀጥታ ሀይሎች በተግባር እያሣዩን ነው:: ለዚህ ሀገርን የመታደግ ታላቅ ተጋድሎም መላው ኢትዩጵያዊ ድጋፉን ሊሰጥ ይገባል::
መንግሥት የመጀመሪያዉን ሕግ የማስከበር ዘመቻ በድል ካጠናቀቀ በኋላ ለስምንት ወራት ያህል የትግራይ ክልልን በጊዜያዊ የመንግሥት አስተዳደር መርቷል:: በወቅቱ በክልሉ የፖለቲካ ሥራ በመሥራት ህዝቡን ከአሸባሪ ቡድኑ መነጠል አልተቻለም ነበር:: አሁንም ጦርነቱ በአጭር ጊዜ ይጠናቀቅ ዘንድ የአሸባሪ ቡድኑን እኩይ አላማ በማጋለጥ ከህዝብ የመነጠል ሥራው ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባዋል::

በመንግሥት በኩል አሁን ያለውን ሕዝባዊ አንድነት ይበልጥ በማጐልበት የፀጥታ ሀይሉን ዝግጅት በማጠናከር ወራሪ ቡድኑን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ማክሰም ግድ ይላል:: የአሸባሪ ቡድኑን እንቅስቃሴ በዘላቂነት እልባት ለመስጠትም መንግሥት በተቀናጀ ዕቅድ በመመራት የፀጥታ ሀይልን ከማጠናከር እኩል የጎለበተ የፖለቲካ አካሄድን ሊከተል ይገባል:: አሸባሪ ቡድኑ በጦርነቱ ከገፋበትም ህልውናውን አጥፍቶ የህዝብን ሠላም በዘላቂነት ማረጋገጥ ይገባል::
የሀገር መከላከያ ሰራዊትና መላ የፀጥታ ሀይሉ የሀገርን ሉዓላዊነት ለመጠበቅ የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት መወጣት እንዲችል ህዝባዊ ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን መረዳት ይጠይቃል:: ይህ ሲሆንም የሀገር አንድነትና ሉዓላዊነትን አስከብሮ መቀጠል ይቻላል::

የሕወሓት አፈቀላጢዎች የሀገር መከላከያ ሰራዊትን ሥም በማጉደፍ ተግባራቸው ተሰማርተዋል:: ይህ ተግባር እኩይ አላማ ያለው መሆኑን በመገንዘብ በተቃራኒ ቆሞ መታገል ይገባል:: አንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ግን እኩይ ተግባሩን ከማውገዝ ይልቅ የተዛባን መረጃ ሲቀባበሉት ይስተዋላል:: እናም ከዚህ ተግባር መታቀብ ይገባል::
ሠራዊቱ ማንኛውንም ጥቃት ለመመከት በፅናትና በጥንቃቄ ተዘጋጅቶ በቆመበት በአሁኑ ወቅት በጠላት የተለመደ የሀሰት የፕሮፓጋንዳ ወጥመድ መጠለፍ አይገባም:: የሰራዊቱን እንቅስቃሴ በመገናኛ ብዙሃን ባልተገባ መልኩ ማሰራጨትም የሚኖረውን አሉታዊ ተፅዕኖ በመገንዘብ ዜጐች ከዚህ ድርጊት ሊቆጠቡ ይገባል:: ይህን ተላልፈው በሚገኙት ላይም ተጠያቂነትን በማስፈን ተገቢውን እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል:: የጠላትን አጀንዳ ከማራገብ በመቆጠብ በሰከነ መንገድ ወቅታዊ ሁኔታውን መመልከት ተገቢነትን የሚጠይቅበት ጊዜ ላይ እንገኛለን:: ህዝብ ከመንግሥትና ከፀጥታ ሀይሉ ጋር ተገቢውን መናበብ በመፍጠር የአሸባሪ ቡድኑን ዳግም ጥቃት የህልውናው ፍፃሜ ማድረግ የሚጠይቅበት ወሣኝ ወቅት ላይ መገኘታችን ልብ ሊባል ይገባዋል:: በተባበረ ክንድ ኢትዮጵያ ጠላቶቿን ድልነስታ እንደምትቀጥል አንጠራጠርም! ::

(ኤልያስ ሙላት)
በኲር ነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም ዕትም
በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘወትር ሰኞ የምትታተመውን የበኲር ጋዜጣን ሙሉ ፒዲኤፍ
በhttp://www.amharaweb.com/Bekur ላይ ማግኘት ይችላሉ።
1.1K views03:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 06:05:06
707 views03:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 06:04:31 ለዚህ ደግሞ የሀብት ምንጮች ልየታ ጎን ለጎን እየተሠራበት መሆኑን ጠቁመዋል። ከዚያም ወደ ትግበራ የሚገባ ይሆናል:: የትግበራ ሥራው በተቋማት በኩል የሚከናወን መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር አባተ የተቋቋመው ጽ/ቤት ደግሞ በዋናነት የማስተባበር ኃላፊነቱን እንደሚያከናውን ጠቁመዋል። የሚገኘው ገንዘብም በአንድ የገቢ ቋት ብቻ ገቢ ይደረጋል ብለዋል።
የሀብት ማሰባሰብን በተመለከተም “ጋን በጠጠር ይደጋፋል ነውና ሁላችንም የምንችለውን እንደግፍ፤ ገንዘብ ያለን በገንዘብ፣ ሐሳብ ያለን በሐሳብ እንደግፍ” ብለዋል:: ዶክተር አባተ አያይዘው እንዳሉት የትግበራ ሥራው በሦስት ደረጃዎች ተከፍሏል፤ በረዥም፣ በመካከለኛ እና በአጭር ጊዜ (በአምስት ዓመታት) የሚከናወኑ ተግባራትን በመለየት ችግሮቹን ለመፍታት ይሠራል፤ የወደሙ ተቋማትንም ቀደም ከነበራቸው በተሻለ ለመገንባት እንደሚሠራ በማንሳት “ከዚህ በተጨማሪም ዋናው ነገር ችግሩ እንዳይደገም ማድረግ ነው፤ ለዚህም በልዩ ትኩረት ይሠራል” ብለዋል::

ትምህርት ሚኒስቴርም ሆኑ ጤና ሚኒስቴር በጦርነቱ የወደሙ ተቋማትን በተሻለ መንገድ መልሶ ለመገንባት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል፤ ለአብነትም የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ብርሃኑ ነጋ በተገኙበት በደቡብ ወሎ ዞን ትምህርት ቤቶችን መልሶ ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ ተቀምጧል። የጤና ተቋማትም እንደ ጉዳት መጠናቸው ጥገና ተደርጎላቸው ወደ ሥራ ተመልሰዋል፤ የወደሙትን ደግሞ መልሶ ለመገንባት በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ ተጠቁሟል። የመልሶ ግንባታ ሂደቱ በየደረጃው ሕዝብ እንዲያውቀው ይደረጋል። “እናግዛችሁ ብለው የመጡ አሉ - ምስጋናችን የላቀ ነው። የወደሙትን ተባብረን በተሻለ መንገድ እንገነባለን” ብለዋል ዶክተር አባተ::

(ጌትሽ ኃይሌ)
በኲር ነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም ዕትም
በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘወትር ሰኞ የምትታተመውን የበኲር ጋዜጣን ሙሉ ፒዲኤፍ
በhttp://www.amharaweb.com/Bekur ላይ ማግኘት ይችላሉ።
705 views03:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 06:04:31 መልሶ ግንባታዉ እንዴት እየሄደ ነው?

ነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም
አሸባሪዉ የትግራይ ወራሪ ቡድን የከፈተውን ጦርነት ተከትሎ በአማራ ክልል በቁሳዊ ውድመት (በዋናነት ማኅበራዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት) ብቻ ከ292 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን በሺዎች የሚቆጠሩ አጥኝዎች የተሳተፉበት የጥናት ውጤት ያሳያል፤ የማኅበራዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ውድመት ደግሞ ሚሊዮኖችን ለከፋ አደጋ አጋልጧል። ለመሆኑ የወደሙ እና ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን ተቋማት መልሶ ለመገንባት ምን እየተሠራ ነው? ምንስ ታስቧል? የሚሉና ተያያዥ ጥያቄዎችን አንስተን የሚመለከታቸውን አካላት አነጋግረን ሐሳቡንም እንደሚከተለው ለንባብ አብቅተነዋል::

በአማራ ክልል በጦርነቱ የወደሙ ተቋማትን መልሶ ለመገንባት ጽ/ቤት ተቋቁሞ ከሐምሌ ወር 2014 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሥራ ገብቷል፤ ዶክተር አባተ ጌታሁን ደግሞ በአማራ ክልል በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ማቋቋም እና ግንባታ ፈንድ ጽ/ቤት ኃላፊ ናቸው። ዶክተር አባተ ከጥናት ቡድኑ የተገኘውን ውጤት ዋቢ አድርገው እንደተናገሩት በጦርነቱ ከሰብአዊ ጉዳቱ ባሻገር መጠነ ሰፊ ቁሳዊ ውድመት ደርሷል። በጥናቱ እንደተረጋገጠውም ከሰኔ ወር 2013 ዓ.ም እስከ ታህሳስ ወር 2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በነበረው ጦርነት በስምንት ዞኖች የሚገኙ 89 የአማራ ክልል ወረዳዎች (945 ቀበሌዎች) ጉዳት ደርሶባቸዋል::

ዶክተር አባተ እንዳብራሩት ጉዳቱን የሚያጠናው (ያጠናው) ቡድን ከአራት ሺህ አምስት መቶ በላይ አባላትን ያካተተ ነው፤ አባላቱም ዩኒቨርሲቲዎችን እና የፌደራል ተወካዮችን ጨምሮ ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጡ ናቸው። ይህ መሆኑም በጦርነቱ የደረሰውን ውድመት በትክክል ለማወቅ ያስቻለ ነው። በተካሄደው ጥናት እንደተረጋገጠውም ከ292 ቢሊዮን ብር በላይ ቁሳዊ ውድመት ደርሷል፤ ይህ የውድመት መጠን በወራሪዉ ቡድን ተይዘው የተለቀቁ ቦታዎችን የጉዳት መጠን ብቻ የሚያሳይ መሆኑን ዶክተር አባተ ተናግረዋል። የተወሰኑ የአማራ ክልል ወረዳዎች አሁንም ድረስ በጠላት ሥር እንዳሉ የሚታወቅ ሲሆን የደረሰው የውድመት መጠንም ከጠላት ነጻ ሲሆኑ በጥናት የሚታወቅ እንደሚሆንም ጠቁመዋል::

ዶክተር አባተ እንዳሉት ጦርነቱ ያደረሰው ውድመት በሦስት ዘርፎች የሚታይ ሲሆን እነዚህም ሰብአዊ፣ ሥነ ልቦናዊ እና ቁሳዊ ውድመት ናቸው። በጥናቱ መሠረትም በቁሳዊ ጉዳት ደረጃ ከ292 ቢሊዮን ብር በላይ ውድመት እንደደረሰ ቢታወቅም ውድመቱ ከዚህ በላይ ሊልቅ እንደሚችል ነው አሁናዊ ተጨማሪ መረጃዎችን በማንሳት ያስታወቁት። የቁሳዊ ጉዳቱ ደግሞ ከሃያ በላይ መሥሪያ ቤቶች ላይ ተከስቷል።

ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ከጥናት ቡድኑ በተጨማሪ የደረሰውን ውድመት እና ስለ ቀጣይ ተግባራት ጉዳት ከደረሰባቸው መሥሪያ ቤቶች ጋር እየሠሩ እንደሆነ ነው የተናገሩት:: በሌላ በኩል በጦርነቱ ሕይወታቸውን ካጡት ባሻገር 12 ሚሊዮን የሚጠጉ የአማራ ክልል ነዋሪዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ይህም የሥነ ልቦና ጉዳትን ያካትታል። በጥናቱ የተገኘውን የውድመት መጠን የዓለም ሕዝብ እንዲያውቀው ይደረጋል ብለዋል ዶክተር አባተ። ከድረ ገጽ ባሻገርም ለሕትመት በማብቃት በመጽሐፍ ተዘጋጅቶ ተደራሽ እንደሚሆንም ተናግረዋል::

ለመልሶ ግንባታዉ ምን እየተሠራ ነው?
ዶክተር አባተ እንዳብራሩት ጥናቱን መሠረት በማድረግ የደረሰውን ውድመት መልሶ ለመገንባት ወደ ሥራ ተገብቷል፤ ለስኬቱም ገለልተኛ ጽ/ቤት (በአማራ ክልል በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ማቋቋም እና ግንባታ ፈንድ ጽ/ቤት) ተቋቁሞ ከሐምሌ ወር 2014 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። በዚህም የአምስት ዓመታት ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ትግበራ ለመግባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል::
ዶክተር አባተ እንዳሉትም ተቋማቱ መልሰው የሚገነቧቸውን ከተቋቋመው ጽ/ቤት ጋር በመናበብ የሀብት ብክነት እንዳይኖር ክትትል እና ቁጥጥር ይደረጋል። ከሁሉም ተቋማት ጋርም የጋራ ዕቅድ ተይዟል:: በጦርነቱ መጠነ ሰፊ ጉዳት ካስተናገዱ ተቋማት መካከል የትምህርት እና የጤና ተቋማት በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ። ለአብነትም በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት ከአርባ በላይ ሆስፒታሎች እና ከአምስት መቶ በላይ ጤና ጣቢያዎች፣ በርካታ ጤና ኬላዎችን ጉዳት እንደደረሰባቸው ከአማራ ክልል ጤና ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል::

በጤና ሚኒስቴር የጤና መሠረተ ልማት ዳይሬክተሩ ኢንጂነር ታደሰ የማነ እንዳሉት በሀገሪቱ ካሉት የጤና ተቋማት የሚበዙት የተሟላ መሠረተ ልማት የላቸውም፤ በጦርነቱ ምክንያት በርካታ የጤና ተቋማት መውደማቸው (መጎዳታቸው) ደግሞ ችግሩን አባብሶታል። በጦርነት ጉዳት የደረሰባቸውን የጤና ተቋማት መልሶ መገንባት እና ደረጃ ማሻሻል የ2015 ዓ.ም ትኩረት መሆኑን ጠቁመዋል::

ኢንጂነር ታደሰ እንዳሉት ከላይ የተዘረዘሩት የአዲሱ በጀት ዓመት ትኩረቶች በሁለት ዙሮች (Phases) ይከናወናሉ፤ በጦርነቱ ከፍተኛ ውድመት የደረሰባቸው አማራ እና አፋር ክልሎች በመጀመሪያው ዙር የመልሶ ግንባታ ሥራ ይከናወንላቸዋል። ለዚህም የጉዳት መጠኑን በማወቅ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የመለየት ሥራ መከናወኑን ተናግረዋል።

ለተግባሩ ከሁለት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ ገልጸው ሦስት መቶ ያህል የጤና ተቋማትን ደረጃቸውን በጠበቀ መንገድ መልሶ ለመገንባት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። መንግሥት፣ የዓለም ባንክ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ደግሞ ዋና የገንዘብ ምንጮች ናቸው::

በአማራ ክልል ጤና ቢሮ የጤና መሠረተ ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኢንጂነር ዘሩ በለጠ እንደተናገሩት በጦርነቱ ምክንያት ከአርባ በላይ ሆስፒታሎች፣ ከአምስት መቶ በላይ ጤና ጣቢያዎች፣ በርካታ ጤና ኬላዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ የጉዳት መጠኑም በጥናት ቡድኑ መለየቱን እና ለሚመለከተው ክፍል እንዲደርስ መደረጉን ተናግረዋል:: ይህ በእንዲህ እንዳለ ጉዳቱን መሠረት በማድረግ በቢሮዉ አቅም መከናወን የሚችሉትን በመሥራት ጉዳት የደረሰባቸው ብዙ የጤና ተቋማት ወደ ሥራ እንዲመለሱ ተደርገዋል። ከቢሮዉ አቅም በላይ የሆኑትን ደግሞ ለሚመለከተው በማሳወቅ ገንዘብ እየተፈላለገ ይገኛል። በዚህም መልካም ውጤት መገኘቱን ኢንጂነር ዘሩ ተናግረዋል።

ለአብነት ያነሱት ደግሞ በጤና ሚኒስቴር በኩል ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተከናወነ ያለውን ተግባር ነው:: በተመሳሳይ ከአራት ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶች ውድመት እና ጉዳት እንደደረሰባቸው ሰሞኑን በወልድያ ከተማ ከተካሄደው ክልል አቀፍ የትምህርት ውይይት ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።

ከዚህ ውስጥም ከአንድ ሺህ በላዩ ሙሉ በሙሉ የወደሙ ናቸው። ከውድመቱ ጋር ተያይዞ ሁለት ሚሊዮን ያህን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ መፈናቀላቸው ተነግሯል፤ ችግሩን መሠረት በማድረግ ተቋማቱ (የትምህርት ሚኒስቴርን ጨምሮ) ለመልሶ ግንባታዉ በትኩረት እየሠሩ እንደሚገኙ ተጠቁሟል::

በአማራ ክልል በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ማቋቋም እና ግንባታ ፈንድ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶክተር አባተ ጌታሁን እንዳብራሩት መልሶ ግንባታዉ በተቋማት በኩል እየተሠራ ነው፤ ጽ/ቤቱም ከተቋማቱ ጋር በመነጋገር እየሠራ ይገኛል። ሁሉን አካታቹ ዕቅድ እንደተጠናቀቀም (በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም መጨረሻ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል) ሀብት የማፈላለግ ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል።
620 views03:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 06:02:37
572 views03:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 06:02:03 ትክክለኛው መስመር ለማስገባት መሞከር ግን ያስቸግራል:: ስለዚህ በራስ እቅድ፣ በራስ ፖለቲካዊ እሳቤ እና በራስ ተቋም ከመመራት ባለፈ አጠናክሮ ብልጫ ወስዶ ሕወሓትን ልክ ማስገባት ተገቢ ነው ባይ ናቸው መምህሩ::
በድሬድዋ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር የሆኑት መምህር በፀሎት አዲሱ በበኩላቸው ሕወሓት ድርድርን እና ሰጥቶ የመቀበል መርህን የማይቀበል የፖለቲካ ታሪክ ያለው ድርጅት ነው ይሉታል። በልጦ እንጂ እኩል ሆኖ መቀመጥ ለሕወሓት ጭቆና ነው የሚሉት መምህሩ ለዚህ ደግሞ ከሕወሓት የበለጠ ተገዳዳሪ ሆኖ መገኘት አስፈላጊ ስለመሆኑ ይናገራሉ፡። ሕወሓት ለመወያየት ያቀረባቸው ቅድመ ሁኔታዎች በገሀዱ ዓለም የማይሆኑ እና አፍራሽ ናቸው። ይህም ሕወሓት ለሰላም ሳይሆን ለጦርነት ስለመዘጋጀቱ ማሳያ ነበር ይላሉ::
መምህሩ “በሕወሓት ጉዳይ መዘናጋት አስፈላጊ አልይደለም፣ አሁንም ፈፅሞ መዘናጋት ተገቢ አያስፈልግም” ይላሉ። የውይይት ጊዜን እንደ ጦር መዘጋጃ፣ የትግራይን ሕዝብ መራብ እንደ ፖለቲካ መነገጃ እና እንደ ዲፕሎማሲ ማሸነፊያ ይጠቀምበታል።
አቶ በጸሎት ሕወሓት በጦርነቱ ከገፋ አቁስሎ ሳይሆን ሕልውናውን አጥፍቶ ለትግራይ ሕዝብም ሆነ ለመላው ኢትዮጵያ እረፍት እና ሰላምን መስጠት የችግሩ ቁልፍ መፍትሄ አድርገው ያቀርቡታል::
የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ኤታማጆር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ኢትዮጵያ ሚዲያ ሰርቢስ ለተባለ በይነ መረብ በሰጡት ቃለመጠይቅ “ሕወሓት ሁሌ አንደኛ እና የመጀመሪያ መሆንንን ብቻ የሚመርጥ ባለበት የቆመ ቡድን ነው” ብለውታል:: አሁን በአዲስ የከፈተው የውጊያ ስልትም በ17 እና 18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የቀረ በሰው ኀይል ማጥለቅለቅ እና የመቆጣጠር ስልት ሲሆን ይህም ሕወሓት ለራሱ ትውልድ ያለማሰቡ ማሳያ ነው ብለውታል:: ነሃሴ 17 ቀን 2014 ዓ.ም “አንቶኖቭ 26” የተባለ የጦር አውሮፕላን ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ በሁመራ አድርጎ ወደ መቀሌ ሲሄድ በኢትዮጵያ አየር ኀይል ተመቶ ወድቋል:: አውሮፕላኑ በሱዳን የአየር ክልል አልፎ የመጣ በመሆኑ ሱዳን ለምን ይሄን እንደፈቀደች ንግግር ይደረጋልም ብለዋል::
የዓለም ምግብ ፕሮግራም ድርጅትም 570 ሺ ሊትር ነዳጅ በመቀሌ ሐምሌ 18 ቀን 2014 ዓ.ም በሕወሓት መዘረፉን ይፋ አድርጎ፣ በሕወሓት ድርጊት ማዘኑን ገልጿል:: የአፍሪካ ሕብረትም ሆነ የአውሮፓ ሕብረት አሜሪካን ጨምሮ ሕወሓት ዳግም በጀመረው ጦርነት አዝነው አስቸኳይ የተኩስ አቁም ስምምነት እና የሰላም አማራጮች እንዲጀመር ጠይቀዋል::

(የሺሃሳብ አበራ)
በኲር ነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም ዕትም
በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘወትር ሰኞ የምትታተመውን የበኲር ጋዜጣን ሙሉ ፒዲኤፍ
በhttp://www.amharaweb.com/Bekur ላይ ማግኘት ይችላሉ።
618 views03:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 06:02:02 የሀገር ሉዓላዊነትን እና ህልውናን የማስጠበቅ ግዳጅ
ነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም
በተኩስ አቁሞ ስምምነት ለወራት ከግጭት ርቆ የቆየዉ የሕወሓት እና የመንግሥት ግንኙነት በንግግር ወደ ሰላም አማራጭ ይሄዳል የሚል ተስፋ ነበር።
የኢትዮጵያ መንግሥትም በየትኛም ቦታ እና ጊዜ በምንም ሁኔታ ለንግግር ዝግጁ እንደሆነ አቋሙን ገልፆ ነበር። መንግሥት ያለቅድመ ሁኔታ ለመደራደር ፍላጎቱን ከመግለፁ በተጨማሪ፣ የታሰሩ የሕወሓት አባላት እና ደጋፊዎች እንዲፈቱ አድርጓል። የሰብዓዊ እርዳታዎች ተደራሽ እንዲሆኑ፣ የትግራይ ክልል 12 ቢሊየን ብር እንዲበጀትለት፣ በትግራይ ክልል ለወደሙ መሰረተ ልማቶች ግንባታ የሚውል ወደ ሦስት መቶ ሚሊየን ዶላር በዓለም ባንክ በኩል ተመድቦ እንዲሠራ ተወስኖም ነበር።
ሕወሓት ግን ወደ ውጤት የማያመጣ ቅድመ ሁኔታ አስቀመጠ። ይኸውም ወልቃይት እና ራያ መጀመሪያ ይመለስልኝ፣ ካሳ ይሰጠኝ፣ ሕዝበ ውሳኔ ይመቻችልኝ፣ ጦሬ እንደታጠቀ ይቀጥል፣ በትግራይ ክልል ሰብዓዊ ጥፋት ያደረሱ ይጠየቁ፣… የሚል ቅድመ ሁኔታ አዘጋጀ። ይሄን ቅድመ ሁኔታ ይዞም የምደራደረው በአፍሪካ ህብረት አይደለም የሚል ሐሳብ አነሳ። የምሥራቅ አፍሪካ የአፍሪካ ህብረት ወኪሉን ናይጀሪያዊዉን ኦሊሴጎን ኦባሳንጆን ለመንግሥት ያደላሉ ሲል ወቀሰ። በመሆኑም ከአፍሪካ ህብረት ይልቅ አውሮፓ እና አሜሪካን፣ ከአፍሪካ ሀገራት ደግሞ ኬኒያ እና የቀድሞ ፕሬዝዳንቷን ኡሁሩ ኬኒያታን መረጠ።
እንዲህ እና እንዲህ እያለ የቀጠለው የሕወሓት እና የመንግሥት ግንኙነት ነሀሴ 18 ቀን 2014 ዓ.ም በይፋ የተኩስ አቁሙ ስምምነት መሻሩ ታወጀ። ሕወሓት በሌሊቱ በራያ በኩል ተኩለሽ በተባለ የሰሜን ወሎ አካባቢ ሀይሉን አንቀሳቅሶ ወረራውን መጀመሩን አወጀ። ራሱ ወሮ ተኩለሽ ራያ አካባቢ ሆኖ ተወረርኩ ብሎም ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሌባ አይነደረቅ እንዲሉ አስተጋባ። ሕወሓት ከሰው ማጀት ገብቶ ሌባ ገባ ብሎ ጮኸ:: የኢትዮጵያ መንግሥት በኮሙኒኬሽን አገልግሎት በኩል ሕወሓት ወረራ ስለመጀመሩ እና የተኩስ አቁሙን እንደጣሰው ይፋ አድርጓል።
ሀገር፣ ሕዝብ፣ ሕግን ለማስጠበቅ እና ታሪካዊ እንዲሁም ሞራላዊ ግዴታየን ለመወጣት ሲል አፀፋዊ እርምጃ እንደሚወስድ መንግሥት የገለፀ ሲሆን፣ ከዚያ በፊት የትግራይ ሕዝብ ሕወሓትን እንዲያወግዝ፣ ዓለምአቀፉ ማህበረሰብም የሕወሓትን ጦር ቀስቃሽነት እንዲያወግዝ፣ የኢትዮጵያ ህዝብም ሁኔታውን በአፅንኦት እንዲከታተል ጥሪ ቀርቧል።

ከጦርነቱ መራዘም ጀርባ
በጦርነቱ መራዘም እና በአጠቃላይ በጦርነቱ ድባብ ዙሪያ አስተያይታቸውን ለበኩር ጋዜጣ የሰጡት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የፌዴራሊዝም እና ሕግ መምህር የሆኑት አይተነው ፈንታ እንደተናገሩት ጦርነት እንዲራዘም እና በኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት ላይ አየር እንዲገባ በማድረግ በኩል የውጭ እጆችም አሉበት። ሕወሓት ለድርድር በሩን ዘግቶ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ያቀረበውን ነዳጅ ዘርፎ ለጦርነት ተሰማርቷል። የሚገርመው ለሰብዓዊ እርዳታ የሚቀርበውን ምግብ እና ነዳጅም ለጦርነት በመጠቀም ፣ ለትግራይ ሕዝብ የረሀብን እና ስቃይን ዕድሜ አራዝሞበታል።
መምህር አይተነው “ሕወሓት የታሪካዊ ጠላቶችን እሳቤ ተሸክሞ ሀገረ መንግሥቱን አዳክሞ፣ ራሱን አውራ ማድረግን አልሟል።” የሚል አመክንዮ ያነሳሉ:: ለዚህ ማሳያ ደግሞ የውጭ ሚዲያዎች ፕሮፖጋንዳ እና የኢትዮጵያን አየር ክልል ጥሶ የገባው አውሮፕላን ነው። ይህ አንቶኖቭ የተባለ የጦር አውሮፕላን ነሐሴ 17 ቀን ከሌሊቱ 4፡00 በሁመራ በኩል ወደ መቀሌ ሲሄድ በኢትዮጵያ አየር ኃይል ተመቶ ወድቋል።
በሌላ በኩል ጦርነቱ ከተጀመረበት ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ሕወሓት የጦርነቱ እቅድ መሪ መሆኑ ጦርነቱን አራዝሞታል ይላሉ መምህር አይተነው። ይህንንም በማሳያ ሲያቀርቡ ሕወሓት ትንኮሳ ይከፍታል፣ መንግሥት መከላከል ያደርጋል። ሕወሓት በአማራ በኩል ዘመቻ ይከፍታል፣ መንግሥትም በአማራ በኩል ለአጻፋ ይሰማራል። ሕወሓት ውጊያ ያቆማል። መንግሥትም አብሮ ያቆማል። ከዚህ አንፃር የጦርነቱ ዕቅድ የሚመራው በሕወሓት ሆኗል፤ መንግሥት መከላከልን መሰረት ያደረገ ውጊያን ይከተላል። ይህ በመሆኑ በውጊያው ሕወሓት የበለጠ ሕዝቡን እያነቃነቀ ወደ ጦርነት እንዲማግድ፣ ጊዜም እንዲገዛ፣ እስከመጨረሻው የሚዘልቅ የማጥቃት እርምጃ እንዳይወሰድበት አድርጎታል።
ለዚህ አብነት ለማንሳት ያህል ባለፈው ታህሳስ 2014 ዓ.ም የመጀመሪያዉ ምዕራፍ ዘመቻ የተጠናቀቀው በአፋርም፣ በአማራም የተወሰኑ ግዛቶች በሕወሓት እንደተያዙ ነበር። መንግሥት ለሠላም ብየ ነው በሚል መከላከያ ወደ ትግራይ ክልል አይገባም ብሎ አወጀ። ሕወሓት በአንፃሩ የተኩስ አቁሙን ተጠቅሞ ለሰባዊ እርዳታ የሚገባውን ሁሉ አሟጦ የራሱን ታጣቂ ለማደራጀት በማዋል አሁንም ወደተለመደ የጥፋት ስምሪቱ ዙሯል። መምህር አይተነው እንዳብራሩት ጦርነቱ ሶስት ምዕራፎችን ይዟል። የመጀመሪያው ምዕራፍ ከጥቅምት 24 እስከ ሕዳር 15 ቀን 2013 ዓ.ም መቀሌ መያዝ እና ሕወሓት ከመንግሥትነት ወደ ጫካ ሽፍታነት የተቀየረበት ሲሆን፣ ሁለተኛዉ ምዕራፍ ደግሞ መንግሥት ከትግራይ ክልል የጦር ሀይሉን ያስወጣበትና ሕወሓት በጫካ ተደራጅቶ ዳግም ወደ መቀሌ የገባበት ከሰኔ 21 ቀን 2013 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 2014 ዓ.ም ያለው የጦርነት ምዕራፍ ነው። በዚህ ሂደት ሕወሓት ወደ አፋር እና አማራ ክልሎች በመስፋፋት ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ውድመት አድርሶ ተመልሷል። በአንደኛዉ እና በሁለተኛዉ ምዕራፍ መካከል የስምንት ወር አንፃራዊ ጦርነት የቆመበት ጊዜ ነበር። ይሁን እንጂ በዚህ ጊዜ ሕወሓት ወጣቱን እያደራጀ፣ በጫካ ታጣቂ ሲመለምል፣ በአንፃሩ በመንግሥት በኩል ሕወሓት ተኗል፣ ዱቄት ሆኗል በሚል አንፃራዊ መዘናጋት ነበር ማለት ይቻላል።
እንደመምህር ዓይተነዉ ገላፃ በወቅቱ በትግራይ ክልልም የፖለቲካ ሥራ በመሥራት ሕዝቡን ከፌዴራል መንግሥት ጋር እንዲናበብ፣ በትግራይ ክልል ተቋማት ወደ አገልግሎት ተመልሰው ከሕወሓት ውጭ እንዲሆኑ፣ ትጥቅ በፌዴራል መንግሥት ቁጥጥር ሥር እንዲሆን ወዘተ ባለመሠራቱ ሕወሓት ወጣቱን እንዲሰበስብ እና የድጋፍ መሠረቱ እንዳይሟሽሽ፣ በሌላ መልኩ ደግሞ መከላከያ ማህበረ መሰረቱ በትግራይ ክልል እንዲላላ አድርጓል።
ይህም ከሰኔ መጨረሻ ጀምሮ ሕወሓት ወደ አማራ እና አፋር ክልሎች እንዲስፋፋ ዕድል ከፍቶለታል።
ሕዝባዊ አንድነቱ መጎልበቱ፣ በፍጥነት የፀጥታ ኃይል በማሰልጠን በቂ ኃይል መፍጠር መቻሉ፣ ሕወሓት የፖለቲካ ቅቡልነት በማጣቱ እና መከላከያ የቴክኖሎጂ ብልጫ በመውሰዱ ሕወሓት ሰሜን ሸዋ ደብረሲና አካባቢ ቢደርስም ተመቶ ተመልሷል። ከደብረሲና ተመትቶ የተመለሰው ሕወሓት አሁንም በድጋሜ ከነሐሴ 18 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ይፋዊ ጦርነት ጀምሯል። መንግሥትም አጸፋዊ ምላሽ እየሰጠ ነው።
የሕወሓትን ጉዳይ በዘላቂነት እልባት ለመስጠት በራስ እቅድ መመራት እና የፀጥታ ኃይልን ከማጠናከር እኩል የጎለበተ የፖለቲካ እሳቤ እና አሠራር ያስፈልጋል ይላሉ መምህር አይተነው። መምህሩ አክለው እንደተናገሩትም የተሻለ እና ተቀባይነት ያለው ፖለቲካ በጦርነት ለማሸነፍም ሆነ በዲፕሎማሲዉ ለመርታት የተሻለ ነው ፣ ሕወሓትን ለማሸነፍ ከሕወሓታዊ ተቋማዊ ውቅር እና ሥርዓት መውጣት አስፈላጊ ስለመሆኑ ያሰምሩበታል። ይህ ሲሆን ሕወሓት የጨዋታ ሜዳው ስለሚቀየርበት አጥቂም ሆነ ተከላከይ ለመሆን ልምድ ያንሰዋል:: በራሱ የፖለቲካ እሳቤ፣ ተቋም እና ሥርዓት እየተመሩ ሕወሓትን ወደ
937 views03:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 06:10:16
2.2K views03:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 06:09:42 (ስማቸው አጥናፍ)
በኲር ነሐሴ 16 ቀን 2014 ዓ.ም ዕትም
በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘወትር ሰኞ የምትታተመውን የበኲር ጋዜጣን ሙሉ ፒዲኤፍ
በhttp://www.amharaweb.com/Bekur ላይ ማግኘት ይችላሉ።
1.9K views03:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ