Get Mystery Box with random crypto!

በኩር ጋዜጣ Bekur Newspaper

የቴሌግራም ቻናል አርማ bekurnewspaper — በኩር ጋዜጣ Bekur Newspaper
የቴሌግራም ቻናል አርማ bekurnewspaper — በኩር ጋዜጣ Bekur Newspaper
የሰርጥ አድራሻ: @bekurnewspaper
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.53K
የሰርጥ መግለጫ

የሰኞ ጋዜጣዎ

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-13 12:11:38
1.2K views09:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 12:11:11 ፖለቲካችን ሕዝብን እና ሀገርን የሚታደግ ይሁን!
ሐምሌ 4 ቀን 2014 ዓ.ም

ማንነት ተኮር ጭፍጨፋ ቦታ፣ ጊዜ እና ፈፃሚ ብቻ እየቀያየረ መቀጠሉ መቼ ነው የሚቆመው? በተለይ በወለጋ መሬት የሚፈፀመው ደግሞ ዘግናኝነቱ እና ስፋቱ ከቀን ቀን እያደገ ነው። አንዴ በምዕራብ፣ ሌላ ጊዜ በምሥራቅ፣ ቆየት ብሎ በሰሜን ወይም በደቡብ እያለ አቅጣጫ እየቀያየረ መፈፀሙ እስከመቼ ነው ምክንያት እየተደረደረለት የሚቀጥለው? ምክንያቶችንስ አስከ መቼ ነው አምነን የምንቀበለው? መንግሥት የተግባሮቹ ሁሉ የመጀመሪያ የሆነውን የሕዝብን ደኅንነት ማስጠበቅ ተግባርስ በተሟላ መንገድ መፈፀም ለምን ተሳነው? ተመሳሳይ ድርጊቶች ለምን በአንድ አካባቢ ተደጋገሙ? ስንሄድ የመታን እንቅፋት ስንመለስ እየደገመን እስከ መቼ ነው የምንዘልቀው? ሸኔ ንፁኃን አማራዎችንም ሌሎችንም በማንነታቸው ምክንያት እየጨፈጨፈ እንዲቀጥል የተሰጠው ዕድሜ መቼ ነው የሚያበቃው?
የመንግሥት የፀጥታ መዋቅር በቅንጅት እና በቁርጠኝነት ከሰራ፣ ሕዝብን አሳምኖ ማሳተፍ ከቻለ የጉዳቱን መጠን መቀነስ ብቻ ሳይሆን የትኛውንም ሥጋት ማስወገድ፣ ይህን አልፎ የሚከሰት አደጋን መቀነስ ይችላል። ከወለጋውም ይሁን ከአብዛኛዎቹ ጥቃቶች የተረፉ ወገኖች በአብዛኛዎቹ ጥቃት በተፈፀመባቸው አካባቢዎች ‘በቅርብ ርቀት የፌደራል ወይም የክልል የፀጥታ ሀይሎች ነበሩ’ ሲሉ በተደጋጋሚ ይደመጣሉ። ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች የጥቃት ሰለባዎቹን ከጥቃት የመከላከል ሥራን በበቂ መጠን አልሠሩም። እሳት የማጥፋት ሥራ ከነዚህ አካላት አይጠበቅም። ሕዝብ በዋናነት እሳቱ እንዳይፈጠር የሚከላከልለት የመከላከያ፣ የፖሊስ፣ የደኅንነት እና መሰል መዋቅሮችን ነው የሚፈልገው። መንግሥት ለነዚህ ክልላዊም ይሁኑ ሀገራዊ መዋቅሮች ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ከብሔር እና ጎሳ እሳቤ የተላቀቁ፣ ሀገራዊ ፍቅራቸው እና ሕዝባዊ ተዓማኒነታቸው የጎለበተ እንዲሆኑ የማድረግ ሥራን ከመጣንበት በላቀ መንገድ መፈፀም አለበት። እነዚህን አካላት በላቀ ብቃት፣ የሕዝብን ደኅንነት ባስቀደመ ተዓማኒነት አደራጅቶ ተገቢውን ስምሪት በወቅቱ በመስጠት በማንነታቸው ምክንያት ዜጎች እንዳይጨፈጨፉ መሥራት እና በጨፍጫፊዎቹ ላይም ሕጋዊ ርምጃ መውሰድ አለበት፤ የኢትዮጵያንም ሆነ የዜጎቿን ህልውና መታደጊያው መንገድ ይህ ነውና።
የቅርቦቹን የወለጋ ጥቃቶች ለመከላከል ተጠቂዎችን ማሳተፍስ ለምን አልተቻለም? ብሎ መጠየቅ እና በቂ ምላሽ መስጠትም የመንግሥት ግዴታ ነው። በማንነታቸው ምክንያት ጥቃት ሊፈጸምባቸው ይችላል ተብሎ የሚገመቱ ወገኖች ከመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ጋር ተቀናጅተው ራሳቸውን እንዲከላከሉ እና እንዲጠብቁ ማድረግ ቢቻል ጭፍጨፋውን በዚህ መጠን እንዳይፈፀም መቀነሥ ብቻ ሳይሆን ማስቀረትም ይቻላል። በወለጋ የተለያዩ አካባቢዎች የተጨፈጨፉ አማራዎችን እና ሌሎችንም በፀጥታ ማስከበር ሥራዎች ማሳተፍ ቢቻል ተመትቶ እየሸሸ ነው የተባለዉ ሸኔ የጅምላ ፍጅት ፈፃሚ መሆኑ ቀርቶ በየደረሰበት የሚለቀም ባዛኝ መሆን በቻለ ነበር።
አሸባሪዋች ተደመሰሱ የሚሉ ተስፋ የሚሰጡ ዜናዎችን ሰምተን ሳናበቃ የመርዶ ዜና የምንሰማበት ሁነት መነሻው ምንድን ነው? ብሎ መመርመር፤ መዋቅርን ማጥራትም ያስፈልጋል። በአሸባሪነት የተፈረጁ ድርጅቶችን ሕዝብን አሳምኖ ከሕዝብ መነጠል ካልተቻለ በየጊዜው ከውስጥ በሚፈነዳ ችግር መታመስ ማብቂያ አይኖረውም። የቅርቡን አንኳን ብናነሳ ከኦሮሚያ ክልል መንግሥት በተሰጠ መግለጫ በወለጋ የተለያዩ ዞኖች የሚገኙ እና ሸኔ ተቆጣጥሯቸው የነበሩ ወረዳዎች የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የኦሮሚያ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ በቅንጅት ባደረጉት ዘመቻ አብዛኛዎቹ በሸኔ ቁጥጥር ስር የነበሩ በመንግስት ቁጥጥር ስር እንደገቡ ተገልጾ ነበር። ጭፍጨፋ የፈጸሙ የሸኔ ታጣቂዎችም መደምሰሳቸው ተገልጾ ነበር። ከዚህ ሁሉ ዜና በኋላ አሸባሪዉ ሸኔ ዳግም ዘግናኝ ጭፍጨፋ መፈፀሙን መስማት ጥርጣሬን ያነግሳል። መንግሥት ራሱን ቆም ብሎ እንዲፈትሽ ያስገድዳል። መንግሥት መዋቅሩ ውስጥ የመሸጉ የአሸባሪዎች ሀሳብ ተጋሪዎች እና ዓላማ አስፈፃሚዎች አለመኖራቸውን በደንብ መመርመር እና ከታይታ የተላቀቀ ጠንካራ ርምጃ መውሰድ አለበት። በሚያሥተዳድረው ቀበሌ፣ ወረዳ፣ ዞን እና ክልል ተመሳሳይ ጭፍጨፋዎች የሚፈፀሙበት ኃላፊ በልኩ እንዲጠየቅ እና እንዲታረም ማድረግ ይገባል። ኦሮሚያ ይሁን ሶማሌ፣ አማራ ይሁን ደቡብ፣ ጋምቤላ ይሁን ሲዳማ በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች ተመሳሳይ አፈፃፀምም ሊኖረውም ይገባል።
በሌላ ወገን በኢትዮጵያም ሆነ ከኢትዮጵያ ውጭ የምንኖር እውነተኛ ሀገር ወዳዶችም ጠላቶቻችን የሚሰጡንን አጀንዳ እያራገብን ጭፍጨፋን ከማባባስ መቆጠብ አለብን። አሸባሪዎች ወገኖቻችንን ሲገድሉ ቀርፀው የሚልኩልንን መረጃ ልዩነትን ለሚያባብስ ተግባር ልንጠቀምበት አይገባም፤ አንድም ኢትዮጵያዊ እንዳይሞት ለሚያግዝ ትግል መጠቀሙ እንደተጠበቀ ሆኖ። በችግሩ ወላፈን እየተለበለቡ በሚገኙት ወገኖቻችን ጫማ ውስጥ ሆነን ተግባራችንን መመዘንም አለብን። የምንሰጠው መረጃ መንግሥት በሚፈለገው የመንግሥት ቁመና ላይ እንዲሆን የሚያስገድድ እንጂ ተጨማሪ ወገናችንን የሚያስገድል እንዳይሆን ሀላፊነታችንን መወጣት የሀገር ወዳድነት መገለጫ ነው። መንግሥት ውስጡን አጥርቶ የህዝብን ደሕንነት የሚያስጠብቅ እንዲሆን መሞገት፣ ወደ ማስተካከል ተግባር ሲገባም ማገዝ የወገንን ስቀይ፣ መከራና እልቂት መቀነስ ነውና ለነገ ቀጠሮ አንስጥ። ከየትኛውም የሥልጣን እርከን የሕዝብ ደሕንነት የሚቀድምብን፣ የሀገር ደሕንነት የሚያንገበግበን፤ በተግባርም ለዚህ የምንተጋ እንሁን። መንግሥትንም የተጨፈጨፉ ወገኖቻችን በምን ምክንያት እንደተጨፈጨፉ እንዲነግረን ሳይሆን ከጭፍጨፋ እንዲታደጋቸው እንሞግት!

(በቀለ አሰጌ)
በኲር ሐምሌ 4 ቀን 2014 ዓ.ም ዕትም
በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘወትር ሰኞ የምትታተመውን የበኲር ጋዜጣን ሙሉ ፒዲኤፍ
በhttp://www.amharaweb.com/Bekur ላይ ማግኘት ይችላሉ።
1.1K views09:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 12:10:45
746 views09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 12:10:02 በውኃ እጦት ማሳ ላይ የነበሩ አትክልቶች አረዋል፤ አፈሩም ደርቋል። በኬንያ ዋነኛ ምግብ የሆነው የበቆሎ ምርት በ70 በመቶ ቀንሷል። ከድርቁ ጋር የአንበጣ መንጋና የኮሮና ወረርሽኝ መዘዞች ተደምረው ሁኔታውን አባብሰውታል። የማርሳቢት ሀገረ ገዥ ሞሀመድ አሊ ህዝቡን ከተጨማሪ ረሀብ መታደግ ይገባል ይላሉ ።
በምስራቅ አፍሪካ በአጠቃላይ ድርቅ ከፍተኛ ችግር እያደረሰ ይገኛል፤ እስከ 20 ሚሊየን የሚደርሱ ሰዎችን ለረሃብ ሊዳርግ እንደሚችልም የአለም የምግብ ድርጅት መረጃ ያመለክታል::ችግሩን ለመቀነስ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የአዉሮፓ ህብረት የተለያዩ ድጋፎችን እያደረጉ ቢሆንም በቂ ግን አይደለም::

መፍትሄው ምን ይሆን?
ድርቅ በተፈጥሮ አደጋ የሚከሰት ቢሆንም ገደብ የለሽ የሰው ልጆች ተግባራት ደግሞ ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዲባባስ አድርገዋል:: ከሚፈለገዉ በላይ የሆነ የውሃ አጠቃቀም እና ብክነት መኖር፣ የደን መጨፍጨፍ፣ የበካ ጋዝ ልቀት መኖር፣…እና ሌሎችም ከድርቅ አባባሽ ምክንያቶች መካከል ይጠቀሳሉ::
ባለፉት 40 ዓመታት በድርቅ ምክንያት የእፅዋት ውድመት ከእጥፍ በላይ አድጓል፤ በአመት በአማካይ 12 ሚሊየን ሄክታር መሬት በድርቅ ይጠቃል::ይህም ከፍተኛ የሆነ የበረሀማነት መስፋፋት እና የዉሃ እጥረት እንዲከሰት እያደረገ ይገኛል::
ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ እ.ኤ.አ በ2030 700 ሚሊየን ህዝብ ከመኖሪያው ሊፈናቀል ይችላል:: ከ3.2 ሚሊዮን በላይ ሰዎችም ለከፍተኛ የውሃ እጥረት የመጋለጥ እድላቸዉ የሰፋ መሆኑን አርዝ ዶት ኦርግ ድረ ገፅ የተባበሩት መንግሥታት ሪፖርት ዋቢ አድርጎ ያወጣዉ መረጃ ይጠቁማል::
ድርቅ አሁን ባለዉ ሁኔታ ከቀጠለ እ.ኤ.አ በ2050 ሶስት አራተኛዉ የአለም ህዝብ (ሰባ አምስት በመቶዉ) ለተለያዩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ይጋለጣል:: ስለሆነም አፋጣኝ መፍትሄ ማምጣት ለነገ የማይባል ጉዳይ ነዉ::
የተባበሩት መንግሥታት መረጃ እንደሚጠቁመዉ መሬት መልሳ እንድታገግም ማድረግ ቀዳሚዉ መፍትሄ ነዉ:: የአረንጓዴ ልማትን ማስፋፋት፣ ውሃን በቁጠባ መጠቀም፣ በጥቂት መሬት ብዙ ምርት ማምረት የሚያስችል የግብርና ዘዴን መጠቀም፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጅዎችን በመጠቀም በሳተላይት የታገዘ የአካባቢ ቁጥጥር በማድረግ ቅድመ ትንበያ መረጃዎችን ማደራጀት፣ የአፈር ለምነት እና ጤንነትን መከታተልን…የመሳሰሉ እርምጃዎችን መውሰድ የችግሩን ስፋት ለመቀነስ እና የሚያደርሰውን ዘርፈ ብዙ ቀዉስ በእጅጉ ለመቀነስ እንደሚያግዙም የተባበሩት መንግሥታት መረጃ ይጠቁማል::

(አዲሱ አያሌው)
በኲር ሐምሌ 4 ቀን 2014 ዓ.ም ዕትም
በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘወትር ሰኞ የምትታተመውን የበኲር ጋዜጣን ሙሉ ፒዲኤፍ
በhttp://www.amharaweb.com/Bekur ላይ ማግኘት ይችላሉ።
722 views09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 12:10:02 ከሁለት ቢሊዮን በላይ ሕዝብ ለምግብ እጥረት ተዳርጓል
ሐምሌ 4 ቀን 2014 ዓ.ም
በዓለም አቀፍ ደረጃ በተደጋጋሚ ይከሰታል፤ ለአጭር ወይም ለረጅም ዓመታት ሊቆይም ይችላል፤ የሰው ልጆችን ህይወት ከሚቀጥፉ አደጋዎች ውስጥ በቀዳሚነት ይጠቀሳል፤ ድርቅ::
በግንቦት 2022 አ.ኤ.አ ዓለም አቀፍ የድርቅ ቀን ሲከበር “ድርቅ በቁጥሮች ሲገለፅ” በሚል ርዕስ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የቀረበ ጥናታዊ ሪፖርት እንዳመላከተዉ በዓለም አቀፍ ደረጃ በምድር ላይ ከሚደርሱ አደጋዎች መካከል 15 በመቶዉ በድርቅ ምክንያት የሚመጣ ነው::
ድርቅ እ.ኤ.አ ከ1970 እስከ 2019 ድረስ በተፈጥሮ አደጋ ከሞቱ ሰዎች ውስጥ የ45 በመቶውን ድርሻ ይይዛል:: ድርቅ በምጣኔ ሀብት ደረጃም ከፍተኛ ኪሳራ ያደርሳል፤ እ.ኤ.አ ከ1998 እስከ 2017 ድረስ ብቻ እንኳን ዓለም 124 ቢሊዩን ዶላር እንድታጣ ምክንያት ሆኗል::
ድርቅ በሚያስከትለው ጣጣ በአሁኑ ወቅት በዓለም ላይ ሁለት ነጥብ ሦስት ቢሊዮን ሕዝብ ለምግብ እጥረት ተጓልጧል፤ 160 ሚሊዬን ህፃናትም ከዚሁ ጋር በተያያዘ ለሚመጣ ችግር ተጋላጭ መሆናቸውንም ከሪሊፍ ዌብ ዶት ኢንተርናሽናል ድረ ገጵ ያኘነው መረጃ ያመላክታል::
በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰቱ የድርቅ እውነታዎች (1900-2022) ድረቅ ካለፈዉ ምዕተ ዓመት መጀመሪያ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ በ10 ሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት ቀጥፏል፤ በመቶ ቢሊዮኖች የሚገመት ሀብትም እንዲወድምም ምክንያት ሆኗል::
እጅግ ከባድ ድርቅ በተደጋጋሚ ካጠቃቸው አህጉራት መካከል አፍሪካ ቀዳሚ ናት፤ ባለፉት 100 አመታት ከ300 መቶ በላይ የድርቅ ክስተቶች በአህጉሪቱ አጋጥሟል:: ይህም በዓለም ከተከሰቱት ድርቆች 44 በመቶውን የሚይዝ ነው::
ባለፈው ምዕተ ዓመት በአውሮፖ 45 ከፍተኛ የተባሉ የድርቅ ክስተቶች ተመዝግበዋል፤ እነዚህ ክስተቶችም በሚሊዬን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለሞት እና ለተለያዩ ማሕበራዊ ችግሮች ዳርገዋል:: በምጣኔ ሀብት ደረጃም 27 ቢሊየን ዶላር የሚገመት ኪሳራ አድርሷል:: በአሁኑ ወቅትም በአውሮፖ በአመት በአማካይ 15 በመቶዉ የአህጉራቱ መሬት እና 17 በመቶዉ ሕዝብ በድርቅ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሳባቸው ይገኛሉ::
በአሜሪካም እ.ኤ.አ ከ1980 ወዲህ በድርቅ ምክንያት ከፍተኛ የምርት መቀነስ ማለትም 249 ቢሊየን ዶላር የሚገመት ኪሳራ ደርሷል:: ድርቅ በእስያም ከፍተኛውን ሰብዓዊ ኪሳራ ባለፉት አመታት ማድረሱንም የተባበሩት መንግሥታት መረጃ ያመላክታል::

ድርቅና ምስራቅ አፍሪካ
አፍሪካ ከሌሎች አህጉሮች በተለየ መልኩ በድርቅ በተደጋጋሚ ትጠቃላች፤ ቀደም ብለን እንደገለፅነው እ.ኤ.አ ከ1900 እስከ 2022 ድረስ በአህጉሪቱ ከ300 የሚልቁ የድርቅ ክስተቶች ታይተዋል:: እ.ኤ.አ ከ2000 እስከ 2019 ድረስ ደግሞ 134 ክስተቶች ተመዝግበዋል፤ ከዚህ ውስጥ 70 ያህሉ ማለትም ከግማሽ በላይ የሚሆኑት በምስራቅ አፍሪካ የተከሰቱ ናቸው::
ምስራቅ አፍሪካ በተደጋጋሚ ለድርቅ የሚጋለጥ የአፍሪካ ቀጣና ነው:: በዚህም በሚሊየን የሚቆጠሩ ሰዎች ለሞት፣ ለስደትና ለተለያዩ ማሕበራዊ ቀውሶች ተዳርገዋል:: በርካታ የቀንድና የጋማ ከብቶች ሞተዋል እንዲሁም ሌሎች ኢኮኖሚያዊ ኪሳራዎች ደርሰዋል:: ባለፉት ሁለት ዓመታት የያዝነውን ዓመት ጨምሮም ከፍተኛ ድርቅ ተከስቶ ሌላ ራስ ምታት ሆኗል::
የምስራቅ አፍሪካን በተደጋጋሚ በድርቅ መጎዳት ለማሳየት በቅርቡ ዶቼ በሌ ያወጣዉን መረጃ መመልከት በቂ ነዉ:: የተመድ የሰብዓዊ እርዳታዎች ማስተባበሪያ ኮሚሽን በእንግሊዘኛ ምህጻሩ ኦቻ እንዳለው እ.ኤ.አ በ2022 መጀመሪያ ላይ ባወጣው የሰብዓዊ ቀውስ ዘገባ የጠቀሰው የሶማሌ ክልል የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ቢሮ፣ በክልሉ በሚገኙት ሁለት ዞኖች ይመረታል ተብሎ ይጠበቅ የነበረው የሰብል መጠን በእጅጉ ቀንሷል። በኦሮምያ ክልል ቦረና ዞን ደግሞ በርካታ የቀንድ ከብቶች ሞተዋል።
ደቡብና ምስራቅ ኢትዮጵያን በመታው ድርቅ ሰበብ ቢያንስ 6 ሚሊዮን ሰዎች በዚህ ዓመት የህይወት አድን እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። የሶማሌ ክልልን እና ምሥራቅና ደቡብ ኦሮምያን ይበልጥ ባጠቃው በዚህ ድርቅ አብዛኛዎቹ ተጎጂዎች አርብቶ አደሮች ናቸው። በነዚህ አካባቢዎች በሶስት የዝናብ ወቅቶች ዝናብ አልጣለም። ኦቻ እ.ኤ.አ በ2022 መጀመሪያ ላይ ባቀረበው የሰብዓዊ ቀውስ ዘገባ የጠቀሰው የሶማሌ ክልል የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ቢሮ፣ በክልሉ በሚገኙት ፋፋን እና ሲቲ በተባሉት ዞኖች ይመረታል ተብሎ ይጠበቅ የነበረው የሰብል መጠን በእጅጉ ቀንሷል። እንደ ቢሮው ከተጠበቀው የማሽላና የበቀሎ ምርት 70 በመቶው አልያዘም፤ በተመሳሳይ ሁኔታ የስንዴ ምርትም በ30 በመቶ ቀንሷል። በደቡብ ኦሮምያም በአማካይ 70 በመቶ ሰብል መጥፋቱን 267 ሺህ የቀንድ ከብቶች በመኖና በውኃ እጥረት መሞታቸውን አስታውቋል። በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ሌሎች የቀንድ ከብቶች በመኖና ውኃ እንዲሁም በክትባት እጦት ህይወታቸው አደጋ ላይ ነው። በተለይ በኦሮምያ ቦርና ዞን ችግሩ የከፋ ነው።የቦረናን ሁኔታ የኦሮምያ ክልል ግብርና ቢሮ ና የእንሰሳት ሀብት ልማት ዘርፍ ሃላፊ ዶክተር ቃሲም ጉዮ ሰሞኑን ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል።
በድርቁ ምክንያት ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች ከአካባቢያቸው መፈናቀላቸውን ኦቻ በዘገባው አስፍሯል። በሶማሌ ክልል የሚገኙ 2.3 ሚሊዮን በደቡብ ኦሮምያ ደግሞ 870 ሺህ ሰዎች በውኃ ችግር እየተሰቃዩ ነው። ዶክተር ቃሲምም ድርቁ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እያስከተለ መሆኑን በትምህርትም ላይ ተጽእኖ ማድረጉን ተናግረዋል። የውኃና የእንሰሳት መኖ ችግርም ከአቅም በላይ መሆኑን አስረድተዋል።
በኦቻ ዘገባ መሠረት በኢትዮጵያ ድርቅ ባጠቃቸው አካባቢዎች የሚገኙ ከ6.4 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በጎርጎሮሳዊው አዲስ ዓመት የምግብ እርዳታ ይሻሉ።
እንደ ኢትዮጵያም ባይሆን በኬንያም ድርቅ ተመሳሳይ ችግር አስከትሏል። ሰሜን ኬንያ ውስጥ በሚገኘው ማርሳቢት በተባለው ወረዳ የቀንድ ከብቶች እየሞቱ ነው። ፊሊፕ ኤዎቶን ቬልት ሁንገር ሂልፈ የተባለው የእርዳታ ድርጅት ባልደረባ ናቸው። በማርሳቢት ድርቅ ያስከተለውን ጉዳት ለዶቼቬለ ገልጸዋል።
“በየመንደሮቹ የሞቱ እንሰሳት ይታያሉ። በህይወት የሚገኙት ላሞችና ግመሎችን ጨምሮ አንዳንድ እንሰሳት መራመድ አይችሉም። ኅይለኛው ሙቀት ይገድላቸዋል። የሚሞቱትም በቂ ውኃ ስለሌለን ነው። ህብረተሰቡ እነዚህን እንሰሳት ውኃ ለማምጣት ይጠቀምባቸዋል። ውኃ ለማምጣት ረዥም ርቀት መጓዝ አለባቸው። አቅም ስለሌላቸው ግን አብዛኛዎቹ ይህን ማድረግ አይችሉም።”
በማርሳቢት ስጋት የሆነው የአሁኑ ጉዳት ብቻ አይደለም፤ የወደፊቱም እንጂ። በአሁኑ ጊዜ በወረዳዋ የሚገኙ 183 ሺህ ሰዎች የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። ይሁንና ዝናብ ካልዘነበ የእርዳታ ፈላጊዎቹ ቁጥር ከፍ ማለቱ እንደማይቀር ኤዎተን ይሰጋሉ። በአካባቢዉ በሶስት የዝናብ ወቅቶች ዝናብ አልጣለም። እስካሁን በሚታወቀው የአካባቢው የድርቅ ታሪክ ይህን ያህል ጊዜ ዝናብ ሳይጥል የቀረበት ጊዜ እንደሌለ ፊሊፕ ኤዎቶን ገልጸዋል። በኬንያ አንዳንድ ግዛቶች ከ80 እስከ 90 በመቶ የሚሆኑ ግድቦችና የውኃ ማቆሪያዎች ካለፈው ታኅሳስ አንስቶ ደርቀዋል።
594 views09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 11:59:24
584 views08:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 11:58:39 “አንድነት ኀይል ነው የሚባለዉ አባባል ብቻ ሳይሆን የተግባር ብሂል ነው፤ አንድነቱ የተጠበቀን ሕዝብ ማንም አይደፍረውም፣ አያሸንፈውም። ለዚህ ደግሞ የቀደምት የኢትዮጵያዊያንን ታሪክ መጥቀስ ብቻ ሳይሆን በእኛ ትውልድ በቅርቡ ያደረግነው የአንድነት ተጋድሎ (ትሕነግ መቀሌ የተሸኘበት አንድነት) ምስክር ነው። ስለዚህ ከመቼውም ጊዜ በላይ አንድነት ያስፈልገናል” ብለዋል።
አማራ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በተለይ በወለጋ እጅግ ዘግናኝ ጭፍጨፋ እየተደረገበት ነው፤ ይህ ሁሉ ግፍ ደግሞ የክልሉን (አማራ) ጫና ይበልጥ በማባባስ ሕዝብና መንግሥትንም ለማቃቃር እንደ መልካም አጋጣሚ ይጠቀሙበታል። በመሆኑም የክልሉ መንግሥት ይህን ሁሉ ከግምት ውስጥ በማስገባት የሕዝቡን ፍላጎት መሠረት ያደረገ ተግባር ማከናወን እንዳለበት አስገንዝበዋል።
አማራ እየደረሰበት ያለውን ጭፍጨፋ በተመለከተ “የሐዘን መግለጫ ማውጣት የመንግሥት ተግባር መሆን የለበትም” ያሉት አቶ ኃይለሥላሴ ዋነኛ ተግባሩ የዜጎችን ደኅንነት መጠበቅ መሆኑን ጠቁመዋል። መገናኛ ብዙኃን ደግሞ እውነቱን ፈልፍሎ በማውጣት እና ለሕዝቡ ትክክለኛውን መረጃ በማድረስ “አራተኛ የመንግሥት አካልነታቸውን በተግባር ማሳዬት፣ መንግሥት የተሳሳት መንገድ ሲሄድም እንዲያስተካክል ማድረግ፣ የሕዝብ ዐይንና ጆሮ መሆን አለባቸው” ብለዋል።

(ጌትሽ ኃይሌ)
በኲር ሐምሌ 4 ቀን 2014 ዓ.ም ዕትም
በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘወትር ሰኞ የምትታተመውን የበኲር ጋዜጣን ሙሉ ፒዲኤፍ
በhttp://www.amharaweb.com/Bekur ላይ ማግኘት ይችላሉ።
586 views08:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 11:58:39 በየትኛውም አግባብ የሕግ መከበር ጥያቄ ውስጥ መግባት እንደሌለበት የጠቆሙት ነዋሪዉ ይህ ደግሞ ሕግን በተከተለ እና ግልጽነት ባለበት አግባብ ከሕዝብ ጋር በመናበብ ሊሆን እንደሚገባ ተናግረዋል።
በመጨረሻም ወቅቱ ስለ ልዩነት የምናወራበት ሳይሆን አንድነታችንን አጠናክረን የገጠሙንን ችግሮች በአንድነት የምናስወግድበት እንደሆነ ተናግረዋል።
የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዋ ወይዘሮ በላይነሽ አይጠገብ የጎንደር ነዋሪው የሰጡትን ሐሳብ ይጋራሉ፤ የውስጥ ባንዳዎች እና የውጪ ጠላቶቻችን በኢትዮጵያ ላይ መነሳታቸውም የሚገርም እንዳልሆነ ጠቁመዋል። ሐሳቡንም ኢትዮጵያ የውስጥ ችግር ሲገጥማት ጠላቶቿም አብረው እንደሚነሱ ነው የቀደመ ታሪክን አጣቅሰው በምክንያትነት ያብራሩት። ለገጠመን ችግር ዋናው መንስኤ የውስጥ አንድነታችን መጥፋቱ ነው ያሉት ነዋሪዋ ለዓመታት የተዘራው የተሳሳተ ብሔር ተኮር መርዝ “ርስ በርስ እያባላን ነው” ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪም በሕግ ማስከበሩ ምክንያት መንግሥት የሄደበት መንገድ ግልጽነት የተላበሰ እና የሕግ አግባብን የተከተለ መሆን እንዳለበት አስረድተዋል። አጥፊዎችን በማስረጃ ላይ ተመስርቶ በመለዬት ሊሆን እንደሚገባ ተናግረዋል፤ ሕዝብ እና መንግሥት አንድ ሆነው ከሠሩ ደግሞ “ታሪክ ምስክር ነው፤ ለማንም አንደፈርም” ብለዋል።
በሰሜን ወሎ ዞን ግዳን እና ቆቦ ወረዳዎች ያነጋገርናቸው እና ስማቸውን መናገር ያልፈለጉ ነዋሪዎችም አሸባሪው ትሕነግ ከዝግጅት አልፎ ትንኮሳ መጀመሩን ነግረውናል። መንግሥትም ካለበት መዘናጋት በመውጣት ያለፈዉ ችግር እንዳይደገም ሕዝቡን መታደግ እንዳለበት ጠቁመዋል።
አልዓዛር መልካሙ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሠላምና ደኅንነት ጥናት ተቋም የፕሮግራም እና ፕሮጀክቶች ባለሙያ ናቸው፤ ለዓመታትም በፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት በመምህርነት አገልግለዋል። በአሁኑ ወቅትም በዚሁ ተቋም ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካ ይበጃሉ የተባሉ ሠላምና ደኅንነትን የተመለከቱ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ለችግሮችም መፍትሔ አመላካች ተግባራትን ያከናውናሉ። አቶ አልዓዛር እንዳሉት ኢትዮጵያ ጊዜ ዐይተው የሚወጓት ታሪካዊ ጠላቶች አጥታ አታውቅም። በአሁኑ ወቅት ያለው የሀገራችን ችግርም እየባሰበት ነው። ችግሮቹም “ከድጡ ወደ ማጡ ሆነዋል” ብለዋል።
ኢትዮጵያን ክፉ ቀን ጠብቀው ከሚወጓት መካከል ሱዳን አንዷ መሆኗን ያነሱት ምሁሩ ለአሸባሪዉ የትግራይ ወራሪ ቡድን አመራሮች እና አባላት ከለላ በመስጠት በወልቃይት በኩል ተደጋጋሚ ትንኮሳ መፈጸሟን አውስተዋል። ሳምሪ የተሰኘው የወራሪው ቡድን አባላት በሱዳን እንደሚሰለጥን ልብ ይሏል። ከሰሞኑ ደግሞ ይህ ወራሪ ቡድን እና የሱዳን ወታደሮች በኢትዮጵያ ላይ ጥቃት ሞክረዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ታዲያ ‘ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል’ እንዲሉ የሱዳን መንግሥት ኢትዮጵያን ከሷል።
ከዚህ በተጨማሪም በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ታጣቂዎች የሚያደርሱት ጥቃት እና በኦሮሚያ ክልል ወለጋ ውስጥ ሸኔ የጨፈጨፋቸው አማራዎች እና አሁንም ድረስ የቀጠለው ጥቃት የኢትዮጵያን ችግር ያባባሱ ምክንያቶች መሆናቸውን አቶ አልዓዛር አብራርተዋል። እነዚህ ሁሉ ችግር አባባሽ ስጋቶች ደግሞ ለአማራ ክልል ይበልጥ ስጋት መሆናቸውን አመላክተዋል። ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ክልሉ ካለው የድንበር ተጋሪነት እና እነዚህ የኢትዮጵያ ጠላቶችም አማራን በተለዬ የጠላትነት ስሜት የሚመለከቱ በመሆናቸው ነው።
በክልሉም አንዱ በአንዱ ላይ የሚያደርገው መጠቋቆም ተገቢ እንዳልሆነም ያነሳሉ። በየትኛውም መንገድ ሕግን ማስከበር እና የዜጎችን ደኅንነተት መጠበቅ የመንግሥት ግዴታ መሆኑን ያነሱት አቶ አልዓዛር ሕግ ሲከበር ትክክለኛ የሕግ ሂደትን መከተል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
አቶ አልዓዛር ከላይ የተነሱትን ችግሮች ታሳቢ በማድረግ እንደ ሀገርም እንደ ክልልም ከገጠመን ስጋት ለመውጣት “ተደማምጦ መሥራት ግድ የሚልበት ወቅት ላይ ነን” ብለዋል። ከዚህ ጋር በተያያዘም መንግሥት ሁልጊዜም ፓርቲ የሚፈልገውን ሳይሆን ሕዝብ የሚፈልገውን ብቻ መሥራት እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ የፌዴራሉ እና የአማራ ክልል መንግሥታት ማድረግ የሚገባቸውን የመፍትሔ ምክረ ሐሳቦችን ዘርዝረዋል። በክልሉ ከሕግ ማስከበር ዘመቻዉ ጋር ተያይዞ መንግሥት እየወሰድኩት ነው ካለው ርምጃ ጋር በተያያዘ ጉራማይሌ ስሜት እንዳለ የተናገሩት አቶ አልዓዛር ጉዳዩን በሰከነ መንፈስ በማየት ወደ አንድነት መምጣት እንደሚገባ ተናግረዋል። በመሆኑም ችግሩን ቆም ብሎ በማሰብ ውስጣዊ አንድነትን የሚያጠናክር ሥራ መሥራት ለነገ የማይባል አንገብጋቢ ተግባር እንደሆነ አስምረውበታል።
ለዚህ አብነት ደግሞ የአማራን ሕዝብ በጠላትነት ፈርጀው በወለጋ አማራዎችን እየጨፈጨፉ የሚገኙትን የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎችን እና በራያ እና በወልቃይት በኩል ጦርነት እየከፈተ የሚገኘውን አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ቡድን ወቅት እየጠበቁ የሚያደርጉትን የጠላትነት ድርጊት አንስተዋል። በመሆኑም በተለይ የአማራ ክልል መንግሥት በክልሉ ውስጥ የሚታየውን የመንግሥት እና የሕዝብ አንድነት ለማረጋገጥ ፖለቲካዊ መፍትሔ በመስጠት አንድነቱን ማጠናከር ይገባዋል ብለዋል። ሕዝብ እና መንግሥት እየተናበቡ በአንድነት ከሠሩ ክልሉ የገጠመውን ስጋት ከመቀልበስ ባሻገር እንደ ሀገር ከገጠመን ችግር ለመወጣት ቁልፍ ጉዳይ እንደሆነ አስረድተዋል።
አቶ አልዓዛር ለሕዝቡም “ይበጃል” ያሉትን ምክረ ሐሳብ አቅርበዋል፤ “የሚታወቅበትን አንድነቱን ማጠናከር አለበት፤ ሕዝቡ ኢትዮጵያዊ ስሜቱ ጠንካራ እስከሆነ ድረስ አንድነቱን ለማምጣት አይቸግረውም” ብለዋል። አንድነቱን በማጠናከር ኢትዮጵያን ከገጠማት ችግር ማላቀቅ የሚታወቅበት ምግባሩ መሆኑንም ጠቁመዋል፤ “ሕዝቡ አንድነቱን ያጠናክር፣ መንግሥትም ፖለቲከኞች ወይም ፓርቲ የሚፈልገውን ሳይሆን ሕዝቡ የሚፈልገውን ይሥራ” ብለዋል። ለዚህ ደግሞ መንግሥት ቆም ብሎ ራሱን መመርመር፣ ሕዝቡ የሚፈልገውስ ምንድነው ብሎ በመጠየቅ ለሕዝብ በመሥራት በተግባር ማረጋገጥ እንዳለበት አብራርተዋል።
አቶ አልዓዛር እንዳሉት እንደ ሀገር ከለውጡ በፊት ወደነበርንበት ክፉ ጊዜ እየተመለስን ነው፤ ችግሮችን ለመፍታት የመንግሥትን ዳተኝነት እና መሰል ማሳያዎችን አንስተዋል። በመሆኑም የፌደራሉ መንግሥት ከዚህ ችግር በመውጣት አፋጣኝ ርምጃ መውሰድ እንዳለበት ጠቁመዋል። በተመሳሳይ መልኩ የሰሞኑን የወለጋውን ጭፍጨፋ እና ከዚያ በፊት የተፈጸሙ አሳዛኝ ድርጊቶችን በማንሳት “የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ራሱን ሊፈትሽ ይገባል፤ ባለስልጣናት ራሳቸውን ማጥራት አለባቸው” ብለዋል።
በተመሳሳይ “ወቅቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ አንድነት የሚያስፈልግበት ነው” ያሉት ደግሞ በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የሕግ መምህሩ ኃይለሥላሴ አዲሴ ናቸው። የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥ ተገቢ ብቻ ሳይሆን ግዴታ መሆኑንም ያነሳሉ፤ ነገር ግን ከሕግ ማስከበሩ ጋር ተያይዞ ሕዝቡ እና መንግሥት ጥርጣሬ ውስጥ መግባታቸውን ጠቁመዋል። ይህ ደግሞ የውስጥ እና የውጭ ጠላቶች ሁሌም የሚጠብቁት መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ተናግረዋል። በመሆኑም መንግሥት ቆም ብሎ የሕዝብን ስሜት ማዳመጥ እንዳለበት ምክረ ሐሳብ አቅርበዋል። በዴሞክራሲ ዓለም ሕዝብ እና መንግሥት አንድ መሆናቸውን ያነሱት ምሁሩ መንግሥት ደግሞ የመንግሥትነት መሠረት የሆነውን ሕዝብ የማዳመጥ ግዴታ እንዳለበት ተናግረዋል።
580 views08:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 11:58:38 የሰላም ድርድሩ፣ የጠላት ዳግም ወረራ እና ሀገራዊ ዝግጁነት ሲፈተሽ
ሐምሌ 4 ቀን 2014 ዓ.ም
አሸባሪው ትሕነግ ለትግራይ ሕዝብ ሰብዓዊ እርዳታ ለማስገባት የተሰጠውን የእፎይታ ጊዜ (የተናጠል ተኩስ አቁም) ተጠቅሞ በተደጋጋሚ የጦርነት ነጋሪት ጎስሟል፤ ከዚያም አልፎ በአዲአርቃይ፣ በጠለምት፣ በሑመራ እና በቆቦ በኩል ተደጋጋሚ ትንኮሳ አድርጓል፤ እየተነኮሰም ይገኛል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ሁልጊዜም የኢትዮጵያን ክፉ ቀን የሚጠብቁት እነ ሱዳን እና የአሸባሪው ትሕነግ ተጋላቢ ፈረሶች (ሸኔ፣ ጋህነግ፣ የጉሙዝ ታጣቂ፣ ...) በንጹሃን ላይ ጭፍጨፋ እና ወረራ ፈጽመዋል። ይህን መነሻ በማድረግ የኢትዮጵያ መንግሥት በተለይ የጥቃት ማዕከል ሊሆን የሚችለው የአማራ ክልል ዝግጁነትን በተመለከተ እና መደረግ ስላለባቸው ወቅታዊ ተግባራት የሠላም እና ደኅንነት እና የሕግ ምሁራንን አነጋግረናል፤ የነዋሪዎችን ሐሳብም አካተናል።

ወራሪ ቡድኑ እና የመንታ ምላስ ታሪኩ በሠላም ድርድር መነጽር
ሐሳባቸውን ያካፈሉን ነዋሪዎች እንዳሉን ሠላም የሁሉም ነገር መሠረት ነው፤ ነገር ግን አሸባሪዉ የትግራይ ወራሪ ቡድን እና የኋላ ታሪኩ በክህደት የተሞላ እና የራሱን የትግል አጋሮች ሳይቀር ሲረሽን የቆዬ ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚሰማውን የሠላም ድርድር በሩን መዝጋት ባያስፈልግም በልዩ ጥንቃቄ ማዬት እንደሚገባ ተናግረዋል። የጎንደር ከተማ ነዋሪዉ ከፋለ እውነቱ የሠላም ድርድር በሚነገርበት በዚህ ወቅት አሸባሪዉ የትግራይ ወራሪ ቡድን ግን የጦርነት ዝግጅቱን ከማጠናቀቅ አልፎ ትንኮሳ መጀመሩን ተናግረዋል፤ የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዋ በላይነሽ አይጠገብም የአቶ ከፋለን ሐሳብ ሙሉ በሙሉ ተጋርተዋል። በዚህ ሁሉ ደግሞ ይበልጥ ተጎጅ የሚሆነው አማራ በመሆኑ መዘናጋት እንደማይገባ ጠቁመዋል። ነዋሪዎቹ ለስጋታቸዉ ደግሞ ከሰሞኑ የአሸባሪዉ ቡድን ያወጣቸውን ርስ በርስ የሚጣሉ መግለጫዎች ነው ያነሱት።
በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የሕግ መምህሩ ኃይለሥላሴ አዲሴ ከበኩር ጋር በነበራቸዉ ቆይታ እንዳሉት ሠላም ከሁሉም ነገር ቅድሚያ የሚሰጠዉ ነው። የዓለም ታሪክ እንደሚያሳየውም የማንኛውም ጦርነት መቋጫ ድርድር ነው፤ ይሁን እንጅ የአሸባሪዉ የትግራይ ወራሪ ቡድን (ትሕነግ) የኋላ ታሪክ ከሠላም የራቀ ነው።
ከዚህ ጋር በተያያዘ ጦርነቱን በሠላም ለመቋጨት በፌደራል መንግሥቱ በኩል የኮሚቴ አባላት ተመርጠዋል። በሌላ በኩል አሸባሪዉ የትግራይ ወራሪ ቡድን በአንድ በኩል ለዳግም ጦርነት መዘጋጀቱን ይናገራል፤ በተቃራኒዉ ደግሞ ለድርድር ዝግጁ መሆኑን በአፈ ቀላጤዎቹ በኩል ተናግሯል። ይካሄዳል ተብሎ የሚታሰበዉ ድርድር “ትሕነግ ካለው ባሕርይ አንጻር ጥያቄ ውስጥ ነው፤ ለጦርነቱ መንስኤ የሆኑ ጉዳዮች እንዴት መፈታት እንዳለባቸው ካልተለዬ ያስቸግራል” ብለዋል ምሁሩ።
እንደ አቶ ኃይለሥላሴ ማብራሪያ ምንም እንኳን ጦርነቱ የሰሜን ዕዝ ላይ በተደረገ ጥቃት መነሻነት ቢካሄድም ዋናው ጉዳይ ግን ከአማራ ታሪካዊ ግዛቶች (ወልቃይትና ራያ) ጋር ይያያዛል፤ በመሆኑም ድርድሩ ይህን መሠረት ያደረገ ካልሆነ ትርጉም አይኖረውም። መንግሥት ራሱን ለድርድር ዝግጁ ማድረጉን እንደማይቃወሙ የተናገሩት የሕግ ምሁሩ ሀገሪቱ ካለችበት ውጥረት አኳያም የድርድሩን መልካም ጎን አንስተዋል። “ዋናዉ ጉዳይ ግን ስምምነት ላይ ለመድረስ የእነ ወልቃይትና ራያ ጉዳይ፣ የወሰን ጉዳይ፣ ... ሁሉ በልዩ ጥንቃቄ ካልተያዘ አስቸጋሪ ነው” ብለዋል። በመሆኑም መንግሥት በተለይ የአማራ ክልል ነገሩን በባለቤትነት በልዩ ትኩረት ሊከታተለዉ እንደሚገባ እና ከላይ ለተነሱት ጉዳዮች አቅጣጫ መቀመጥ እንዳለበት አስረድተዋል።
ድርድሩን በተመለከተ ትሕነግ እርስ በርሱ የተጣላ ሐሳብን እያስተጋባ ነው፤ ለአብነትም ቃል አቀባያቸዉ ጌታቸው ረዳ በሰሞኑ መግለጫ አማራ ክልል ላይ በግልጽ የስድብ ናዳ ሲያወርድ ተሰምቷል። በሌላ በኩል የወታደራዊዉ ክንፍ አዛዣቸዉ ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ የዳግም ጦርነቱን አይቀሬነት ተናግሯል። መግለጫውን መነሻ አድርገው ማብራሪያ የሰጡን አቶ ኃይለሥላሴ “አማራን እና አማራ ክልልን እያብጠለጠሉ ከፌደራል መንግሥት ጋር መሻሻል አለ ቢሉ ትርጉም የለሽ ነው። ይህ እና ታሪኩ የሚያሳየውም ትሕነግ ለሠላም የተዘጋጀ አለመሆኑን ነው” ብለዋል። ለይስሙላ ስለ ሠላም የሚናገሩትም ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ለማደናገር እና በዓለም ሀገራት እና መንግሥታት በኩል ሠላም ፈላጊ መስሎ ለመታዬት እንደሆነ የቡድኑን ታሪክ በመጥቀስ አስገንዝበዋል። በመሆኑም የሠላም በሮች መዘጋት ባይኖርባቸውም “መዘናጋት ግን ፍጹም ተገቢ አይደለም፤ ያለፈው ስህተት ተደግሞ ዳግም እልቂት እንዲከሰት ዕድል መስጠት አይገባም” ብለዋል። የሰሞኑ የአሸባሪ ቡድኑ መግለጫም “ምን ያክል ጦርነት ናፋቂ መሆናቸውን ያሳያል፤ የመጡበት ታሪክም ይህን ያሳያል” ነው ያሉት።
የአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች አሁንም በአሸባሪ ቡድኑ እንደተያዙ ይገኛሉ፤ ዜጎች እጅግ ፈታኝ ኑሮን እየገፉ ነው። ድርድሩም ይህን ሁሉ ችግር ከዘነጋ አስቸጋሪ እንደሚሆን አመላክተዋል። የሕዝቡን ጥቅም በሚያስጠብቅ አግባብ ድርድሩ ከተካሄደ ደግሞ “ሠላምን ማን ይጠላል! ሁሉም ይቀበለዋል” ብለዋል። የሠላም በሮች ሳይዘጉ ሊመጣ የሚችልን ጥቃት ለመመከት ዝግጁ መሆን፣ ከባለፈዉ ጊዜ መዘናጋት መውጣት እና ራስን ከማንኛውም ጥቃት ለመከላከል ዝግጁ መሆን እንደሚገባ ተናግረዋል።

ለነገ የማይባል ቀጠሮ - አንድነት
የጎንደር ከተማ ነዋሪው አቶ ከፋለ እውነቱ ወቅቱ የኢትዮጵያን ክፉ ቀን የሚጠብቁ ጠላቶች የኢትዮጵያን እና የኢትዮጵያዊያንን ሠላም ለማናጋት በጋራ የቆሙበት መሆኑን ይናገራሉ፤ ችግሩም “በተለይ ለአማራ ክልል የበለጠ ስጋት የፈጠረ ነው” ብለዋል። ለዚህ ደግሞ የጥፋት ኀይሎቹ (ትሕነግ፣ ሸኔ፣ የጉሙዝ ታጣቂ፣ ...) አማራን በጠላትነት የፈረጁ መሆናቸውን በምክንያትነት አንስተዋል።
በሌላ በኩል ሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር ጥሳ በመግባት ከዓመት በላይ ይዛ መቆየቷ ሳያንሳት ከሰሞኑ ደግሞ ወረራውን በማስፋፋት ጦርነት ከፍታለች። ይህም እንደ ሀገር ኢትዮጵያ ላይ የተቃጣ አደጋ ቢሆንም ለአማራ ክልል ደግሞ የከፋ ነው። የተወረረው መሬት የአማራ ክልል በመሆኑ እና ክልሉም ከሱዳን ጋር ቀጥተኛ የድንበር ተጋሪ መሆኑን አቶ ከፋለ ተናግረዋል።
ከዚህ ችግር ለመውጣት ዋና መፍትሄው “አንድነት፣ አንድነት፣ አንድነት ነው” ብለዋል። “ችግር ለእኛ ለኢትዮጵያዊያን አዲሳችን አይደለም” ያሉት ነዋሪዉ ሁሉንም ችግሮች በአንድነት መሻገራችንን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት የገጠመንን ችግርም በአንድነት መወጣት ይገባል ነው ያሉት። ከዚህ ጋር በተያያዘ ነዋሪው እንዳሉት ጠላቶቻችን የተነሱብን በውስጥ የገጠመንን ፈተና ተመልክተው ነው። አንድነታችን ከጠነከረ ደግሞ ጠላትን እስከ እሳቤው በማስወገድ ችግሩን መሻገር “ለእኛ አዲስ አይደለም” ብለዋል።
አንድነትን ለማጠናከርም ሕዝብና መንግሥት ተናበዉ መሥራት ግድ እንደሚላቸዉ ጠቁመዋል፤ “መንግሥት ሕዝብን ማስጨነቅ ሳይሆን የሕዝብን ስሜት ማዳመጥ አለበት፤ ለውስጥ ባንዳዎችም (ሸኔ፣ የጉሙዝ ታጣቂ፣ ...) ትዕግስት አያስፈልግም” ብለዋል።
611 views08:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 11:58:06
637 views08:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ