Get Mystery Box with random crypto!

የዮቶር ልጅ - አምባዬ ጌታነህ

የቴሌግራም ቻናል አርማ amba88 — የዮቶር ልጅ - አምባዬ ጌታነህ
የቴሌግራም ቻናል አርማ amba88 — የዮቶር ልጅ - አምባዬ ጌታነህ
የሰርጥ አድራሻ: @amba88
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.75K
የሰርጥ መግለጫ

እኛ ከዮቶር፦
☞ የጥበብ ምሳሌን
☞ የአስተሳሰብ ውጤትን
☞ የፍልስፍና ዳራን
☞የአመራር ብቃትን
☞የአኗኗር ዘይቤን
ተምረናል!!!
ስለዚህ ሁላችንም የዮቶር ልጆች ነን ማለት ነው።
ለአስተያየት ና ሀሳብ via creater
@Adwa1888 [አምባዬ ጌታነህ]
YouTube
https://youtube.com/channel/UCTQKMrpvRybbd9C552bMVQQ

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-15 22:03:49 ለሚቀጥሉት 30 ቀናት ማለትም ከነገ 9/10/2014 ዓ.ም ጀምሮ ከማህበራዊ ሚዲያ ማለትም(ከቲክቶክ፣ፌስቡክ፣ኢንስታግራም፣ቴሌግራም ዩቲዩብ ) ለመራቅ በዚህ ስአት ከራሴ ጋር ስምምነት ፈፅሚያለሁ።ይህ ውሳኔዬም ለወደፊት ከ 60 ዓመት በላይ ለሚኖረኝ ዕድሜ የሚያገለግለኝ አቅጣጫ ይሆናል። የአንድ ሀገር ምሁራን ለሚመጣው ትውልዳቸው የልዕልና ሀብት ለማካበት እንደሚያቅዱት ሁሉ እኔም በእኔ ውስጥ ለሚወለድ አዲስ ትውልድ የሚበጅ እሳቤ ያስፈልገኛልና ከማህበራዊ ሚዲያ ሱስ በቅድሚያ ማገገም አንዱ ተግባር እንደሆነ በማወቄ እና ራሴን ከምፈልገው ማንነት ጋር ድጋሚ ለመውለድ ስል ይህን ወርቃማ ውሳኔ ወስኛለሁ። ውሳኔዬ አስደንጋጭም አስፈርጣጭም ለሚመስላችሁ ወዳጆቼ ግን ለሚመጡባችሁ ጥያቄዎችና መልሶች ተገዥ እንዳትሆኑ ለማሳሰብ እወዳለሁ።

For the next 30 days, starting tomorrow, October 9, 2014, E.C I agree with myself that I will stay away from social media (Tiktok, Facebook, Instagram, Telegram YouTube). Just as the scholars of a country plan to accumulate wealth and wealth for the next generation, I have made this golden decision because I know that recovery from social media addiction is one of the first steps and I need to think of something better for the next generation. I would like to remind my friends that you do not seem to be paying attention to the questions and answers that come your way.

@Adwa1888 አምባዬ ጌታነህ
3.5K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 19:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 17:14:29 አየህ ይች ሀገር ህዝብ አላት! ሰው ግን የላትም! እንጨት ብቻውን ቆሞ ቤት አይሰራም! ማገር ያስፈልገዋል፡፡ ህዝብም ብቻውን ሀገር አይሆንም፡፡ አንድነትን የሚጠብቁ ካስማዎች ያስፈልጉታል፡፡ የዚች ሀገር ካስማዎች እነ ቴዎድሮስ፣ እነ ሚኒሊክ አሁን የሉም፡፡ አንተ እነሱን መሆን አትችልም? ራዕያቸውን ብትጋራ ግን እነሱን ትተካቸዋለህ፡፡ እነሱን ለመተካት ደግሞ ግዴታ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት መሆን አይጠበቅብህም!.....››
(ቃለ ዲዲሞስ፣ ዴርቶጋዳ)

@amba88
3.2K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 14:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-11 18:47:21 https://addismaleda.com/archives/28065
7.7K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 15:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-08 21:10:35 የጠፋሁት ትንሽ አመም አድርጎኝ እና ስራ በዝቶብኝ ነው እሺ!
4.3K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 18:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-05 21:25:54
ጅብ አይበላሽ ጫማ-በቡትቶ ጨርቆች
ከካብ ተደርድራ በማገር ከቆመች
ቋሚዋም ጣራዋም ፍቅር ፍቅር ሚሸት
ከተከዜ ወዲህ
ከሎሚው ወደዚያ አለች ውብ የሳር ቤት
በዚያች የሳር ጎጆ
ችግር ያጠቆረው ወዝ ደምቆ ይታያል
ርሀብ በፈገግታ
በሳት ዳር ጨዋታ በሳቅ ይታለፋል
የእናት ተስፋና ቃል
እንደ ሙሴ በትር
የኑረትን ባህር ከፍሎ ያሻግራል
የተስፋ ምናቦች
የህልም ሀሳቦች በወግ ተሰድረው
ነፍስን በሚያሞቁ
ቀልብን በሚወስዱ ቃላቶች ታጅበው
ለልጅ ልጅ የሚተርፍ
የፅናት ውብ ዋጋ ይተረክበታል
የትዕግስትን ጥግ
በኑሮ መሠላል ዜማ ተቀምሮ ይዘመርበታል
እታተይ ማጀቱን
አባባ ማሳውን
እህቴም እንደ ልጅ
የእንጨት ሰበራውን
ወንድሜም እንደ ልጅ
በግ እረኝነትን
እኔ ያስኮላውን
በቀልድ የተዋዛ ሞቅ ያለ ጨዋታ
የልጅነት ታሪክ የፍቅር ትዝታ
የእቃቃ ሚስትነት
የእቃቃ ባልነት
በትዝታ ተረክ በፍቅር ተጠቅሶ ከማዕድ ይቀርባል
የልጅነት ጊዜ ያፍላ ፍቅር ወጎች ይተረኩበታል።

አምባዬ ጌታነህ @Adwa1888
5.0K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 18:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 21:07:22 "ናፊባ"
ክፍል ~ ዘጠና አራት~
በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888
"መኖር የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ድርሻው ብቻም ሳይሆን
ኃሴት እንዲያገኝ የሚያደርገው እጣ ፈንታው ነው።
ረሀብና በሽታ ብቻ ሰውን አይገለውም።
ቤት የሌላቸው በርካታ ሰዎች ቢኖሩም አንተ ግን....."
" አንተ እስክትመጣ ድረስ በተደጋጋሚ እያነበብኩት ነበር። ፍፁም አልገባህ አለኝ። የሆነ ትርጉም ግን እንዳለው ልቤ ይነግረኛል።ብዙ የቅኔ አመስጣሪዎች ሀሳባቸውን በስነግጥም እና በስድ ንባብ ያስቀምጣሉ። እንዲሁም የሀገራችን ላቃውንትም ምስጢርን በብራና ሀሳብ ጥቅል ከይነው ለትውልድ ያስቀምጣሉ። ያን ቁልፍ የሚያገኝበት በርካታ ጥቅሎችም ይቀመጡለታል። ይህም ልክ እንደ ዴርቶጋዳ ላይ እንደተቀመጠው የሎሬት ግጥም ላይ እንዳለ የምስጢር ሀሳብ ነው። እና የውጮቹ ሰላዮችና ጠቢባን በርካታ ከያኒያን እና የደህንነት ሰዎች ሳይቀሩ እንቆቅልሾችን ይጠቀማሉ። ለምሳሌ row and column puzzle በሚባል እንቆቅልሽ ያስቀምጣሉ።በዛ መሠረት ከሁሉም አራፍተነገሮች የመጀመሪያ የመጀመሪያ ቃሎቹን ወስጄ ደረደርኩ
መኖር
ኃሴት
ረሃብና
ቤት
ብሎ ቁልቁል በመፃፍ ለኢንስፔክተር ሸዋንግዛው አሳየው "እኔ እንደሚመስለኝ እነዚህ ሰዎች የሚኖሩት እና ከመኖርም በላይ ኃሴት የሚያገኙት ረሀብ በተጠናወታቸው ሰዎች ነው። ለዚህም ስለቤት አያስቡም።ምክንያቱቤ ቤት የሌላቸው በርካታ ሰዎች ቢኖሩም አንተ ግን... ይላል።ይህም ማለት ቤታቸውን ጥለቅ በረሃብ ምክንያት ይሰደዳሉ። በዚህ ሀሳብ ላይ የተሰናሰለ ይመስለኛል"አለ ተሕሚድ።ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ግን አንዱንም ያለውን አልሰማውም ነበር። አእምሮውና ልቡ የተደረደሩት ቃላት ላይ ነበር። ተሕሚድ የሸዋንግዛውን ምንም አለማለት እና ከእርሱ ጋር አለመሆኑን የተረዳው በኋላ ነበር። "ፍቅሬ አጎቴ ሌላ ሀሳብ ውስጥ ገብቷል እኮ ዝም ብለህ ነው ስትደክም የነበረው"ብላ ሳቀች።
"አገኘኋት!!! መ..ኃ..ረ..ቤ!" አለ ሸዋንግዛው። ተሕሚድ በቀጥታ ያወጣቸውን ቃሎች ተመልክቶ የመጀመሪያ የመጀመሪያ ቃላቸውን ወስዶ ሲደረድር ኢንስፔክተር የተናገረውን ስም አገኘ። መኃረቤ!!! "የሰው ስም ነው?" አለ። "በሚገባ እንጅ ለዛውም የመጀመሪያው ሟች ኄኖክ የቤት ሰራተኛ ከዛ በኋላም እዛ አትሆንም ብለን ትላንት የሞተው የዋና ሳጅን አክሊሉ የቤት ሰራተኛ ሆና ነበር። ነገር ግን ከወራት በፊት ተሰወረችብን"አለና በምናብ ወደ ኋላ ሄዶ ሒዎትን በኄኖክ እና ዮዳሔ ግድያ ተጠርጥራ ለምርመራ በነበረችበት የኄኖክ ሰራተኛ በመሆኗ እንደምታውቃት እና መረጃ እንድትሰጥ መኃረቤ ስትጠየቅ በጣም ደንግጣ ነበር። በምላሿም ጥርጣሬ እንደገባውና ግን ምን አልባት የዛኑ እለት አስፈራርታት ቢሆንስ ብሎ ያሰበው ትዝ ብሎት"ራሱን በመነቅነቅ ቀጥታ ወጥቶ ወደ ፕሮፌሰር እስጢፋኖስ በመሄድ ስለ መኃረቤ ሁሉንም ሲነግረው። ከተሽከርካሪው ወንበር ቀስ ብሎ ተነሳና ፈገግ ብሎ "የሼክስፔር ተዋናይት ናታ?" አለ "ማለት አልገባኝም!" አለ ሸዋንግዛው እንዲያብራራለት " የእንግሊዞች የጥበብ ጣኦት ሼክስፔር ነው። እጅግ በሚባል ደረጃ በጣም ይወዱታል። የሱን ስራዎች ከሰራው በላይ በዓለም እንዲዳረስና እንዲስተጋባ አድርገዋል። እና አርት በጣም ያስደስታየዋል ድርሰትና ትወጣ ስራቸውን ከሚያቀሉላቸው ነገሮች ቀዳሚዎቹ ናቸው። ለዚህም ሰላዮቻቸውን በከፍተኛ ጠሰንቃቄና ብቃት የትወና ጥበብን ያስተምሯቸዋል።በየሀገሩ የሚልኳቸውና ተልዕኳቸውን የሚያስፈፅሙሏቸው ሰዎች የትወና በቃታቸው በጣም ትልቅ ነው። አንተን ያሳምኑሀል። በቃ ከምነግርህ በላይ በጥበባቸው የአንተን ደካማ ጎንና የማመን ሀይልህን ይቆጣጠሩብሀል። ደግሞ እኛ ኢትዮጵያዊያን ለማዘንና ለሰዎች በጎ ነገር ማሰብ ቀዳሚው ተግባራችን እንደሆነ ስለሚታወቅ ይህን እንደ ትልቅ ግበአት ይጠቀሙበታል። ስለዚህ የእንግሊዞች መሣሪያ አሉ ማለት ነው። በርግጥ እንግሊዝ ከአሜሪካ የበለጠች አደገኛና መሠሪ የሆነች አገር ስለመሆኗ የክሪሚላን ፖለቲከኞች ሳይቀሩ ይናገራሉ።በራሺያውያን ራሱ በቀዳሚ በሚባል ደረጃ የሚጠሉት እንግሊዞች ናቸው።
*************
መንግስት ከጠበቀው በላይና ሊቆጣጠረው ከሚችለው በላይ ሲሆንበትና የማህበራዊ ሚዲያው ተቃውሞ ሲበዛበት የዳታ አገልግሎቱን በማቋረጥ ለማርገብ ሞከረ። በዚህ ድርጊት የተቆጡ አዲሳበባዊያን በተለያዩ አጋጣሚዎች በመቀሳቀስ ተቃውሟቸውን ለመግለፅ በአደባባይ ወጥተዋል። ህዝቡ በተመሳሳይ ስሜት ውስጥ ሆኖ በየቦታው በተመሳሳይ ስአት በመገንፈል የአዲስ አበባ ጎዳናዎችን በሰላማዊ ሰልፈኛ ተቃዋሚዎች ተጥለቀለቀች። ከፈረንሳይ የመጣው ሰላማዊ ሰልፈኞ ከሽሮሜዳ በከሉ በመነን አድርጎ በስድስትኪሎ ዩኒቨርሲቲ አድርጎ ስድስት ኪሎ ሰማዕታት ሀውልት ላይ ተገናኝተው ቁልቁል በአምስትኪሎ አድርገው ሲወርዱ መንግስት ከቅድስተማርያም በታች እንዳያልፉ ከፍተኛ የሆነ ሀይል አሰማርቶ መንገዱን ዘጋ። ነገር ግን ሰልፈኛው በቅድስተማርያም በኩል አድርጎ በሰባ ደረጃ በመታጠፍ ወደ ፒያሳ ነጎደ። ከቀጨኔ ከ አዲሱ ገበያ፣ እና ከገዳም ሰፈር በኩል የመጡት ሰልፈኞች ደግሞ ምኒሊክ ሀውልት ላይ ተገናኙ። ከጳውሎስ መድኃኒዓለም እና ዩሐንስ በኩል የመጡትም በአቡነጴጥሮስ ሀውልት አድርገው ምኒሊክ ሀውልት ላይ ተገናኙ ከአቧሪ ካዛንቺስ መገናኛ በኩል የመጣው ሰልፈኛ ደግሞ ወደ መስቀል አደባባይ እየተመመ ነው። ከልደታ በኩል ከሳሪስ ከጎተራ ከጠመንጃ ያዥ በቅሎ ቤት ከጨርቆስ አውቶብስ ተራ ከሜክሲኮ ልደታ ከተክለሀይማኖት አብነት የጎረፈው ህዝብም በለገሀር አድርጎ በስታዲዮም ብቅ ብሎ ከወደፒያሳ የተሰባሰበው ህዝባዊ ሀይልም በቴዎድሮስ አደባባይ በኩል በቸርችል ጎዳና ወርዶ በአምባሳደር አድርጎ በጊዮን ሆቴል ብቅ ብሏል።ከቦሌ መስቀል ፋለወር በኩል የመጣውም ሰው በቀይ ሽብር በኩል አሰፍስፎ ወደ መስቀል አደባባይ እንዳይገቡ በሚከለክሉ መንግስታዊ ሀይሎች ጋር ተፋጧል። በመጨረሻ ተቃውሞው እየበዛና የህዝቡ ቁጣ እያየለ ሲሄድ ብረት ለበሶቹ የፌደራል ፖሊሶች አስለቃሽ ጭስ ለመጠቀም ተገደዱ። ዳሩ ግን የነሱ አስለቃሽ ጭስ የህዝቡን ንዴት ጨመረው እንጅ ፈርተው እንዲያፈገፍጉ አላደረጋቸውም። መንግስት ለዚህ ሰልፍ ሀላፊነት የወሰደ ሰው ባለመኖሩና ምንም አይነት ህጋዊ ማረጋገጫ ሰነድ ስለሌለው ማንንም መጠየቅ እንዳለበት እና ማንን ማሰር እንዳለበት ግራ ገብቶት አብዝሀኛዎቹን በጅምላ ዝም ብሎ ወደ መኪና እንዲጫኑ ሊያደርግ ሲል ሰልፈኛው ሆ ብሎ እንደ ንብ ይወጣባቸዋል። ከዛ ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ከላይ በወረደ ትዕዛዝ ብረት ለበሶቹ ፌደራል ፖሊሶች ስፍራውን ለቀው ወጡ። "ይህ መንግስት ለሆዱ እንጅ ለህዝብ አያስብም!" "በንፁሀን ደም መቀለድ እስከየትም አያደርስም!" "ኢንስፔክተር ሸዋንግዛውን ልቀቁት! እርሱን በማሰር የህዝቡን ፍላጎት ልታስቆሙ አትችሉም።! የሞቱት እህት ወንድሞቻችንን ገዳይ እንፈልጋለን!" በማለት የተቃውሞ መፈክራቸውን በማሰማት ቀጥሉ። በዚህ ህዝባዊ ማዕበል አንድም ሰው ወጥቶ የተናገረም ሆነ ማይክ በመጠቀም የሁላቸውንም ድምፅ ለማስተጋባት የሞከረ አልነበረም። ምክንያቱም ምንም የተዘጋጀ ሳውንድ ሲስተም ስላልነበረ። ይህ እንዳይሆን መንግስት ቀድሞ በየቀበሌው ተናጋሪዎች ናቸው የተባሉ ወጣቶችን አስሯቸዋል።

@amba88
@amba88
4.2K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 20:48:48 "ናፊባ"
ክፍል ~ ዘጠና ሦሥት~
በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888
"መረጃውን አትሰማም የሚል እምነት በግሌ የለኝም።ምክንያቱም በስአታት ልዩነት ነው የዋሽንግተን ፖስት ያንተንና የልጆችህን ምስል ከፊት አድርጎ ለዜና ያበቃው" ብሎ ስካይፑን እየነካካ ሳለ የመልስ ደወል ጠራ። በፍጥነት ነክቶ የስካይፑን ምስል አደብዝዞ የቤቱን ከለር ወደ አረንጓዴነት የሚቀይረውን ማብሪያ ማጥፊያ በመጫን አንስቶ ድምፁን ጨመረው። ሜላት ነበረች። ፍፁም የሆነ ሰላም እየተሰማው እፎይ አለና ሸዋንግዛውን እንዲያወራ ብቻውን ትቶት ወጣ። የተለመደ ስጋቷን ያለምንም እረፍት እያዥጎደጎደችለት ትንፋሽ አሳጣችው። ሸዋንግዛውም ሁኔታዋ ስለገባው በፈገግታና በስስት ይመለከታት ጀመር። "አሁን ምንም አትጨነቂ ያለሁበት ቦታ አስተማማኝ ነው። ስለዚህ ተረጋግተሽ ስራሽን መስራት ትችያለሽ!"
ፕሮፌሰር እስጢፋኖስ የኋላሸት ውጪ ላይ እየተንጎራደደ እጆቹን ወደ ኋላ አድርጎ እርምጃውን የሚቆጥር በሚመስል ማቀርቀር ውስጥ ሆኖ አንድ ሀሳብ መጣለትና በሩን ከፍቶ በመግባት ወደ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ጆሮ ጠጋ ብሎ "ማንኛውም ሰው ደውሎ እንዳገኘችህ እንዳትናገርእና የሚጠይቃት ካለ ምንም እስካሁን እንዳልደወልክላት እንድትናገር አድርጋት " ብሎት ወጣ። ሸዋንግዛውም አፍታም ሳይጠብቅ "የኔ ፍቅር እንዳወራሁሽ ለማንም አትናገሪ እሺ ያው መንግስት ሊያስረኝ ሲል ነው እነዚህ ሰዎች ቀድመው ደርሰው የጠበቁኝ እና ማንም ሰው እኔን እንዳገኘሽኝ ከጠየቀሽ ጭንቀት ላይ እንደሆንሽ በማሳየትና በጭራሽ እንዳልደወልኩልሽ በሁኔታሽ አስረጃቸው። በኤምባሲው በኩል ክትትል ሊደረግብሽ ስለሚችልና ንግግርሽ ሊቀዳ ስለሚችልም ላልተወሰነ ጊዜ አንደዋወልም። በጭራሽ ስጋት እንዳይገባሽ። ልጆቹም ፍፁም ደህና ናቸው። ይህን የተደዋወልንበትንም አጥፊው" አለና ተሰናበታት። ሜላት ሁኔታውን በትንሹም ቢሆን ስለተረዳችው ልትጫነው አልፈለገችም። ግን ደግሞ እስከመቼ ነው እንዲህ የሚቀጥለው? የሚል ጥያቄ ራሷን እየጠየቀች ነበር።
ኢንስፔክተር ሸዋንግዘው በትንሹም ቢሆን የፈራው ፍርሃት ለቀቀው።አሁን አንድ ሀሳብ ብቻ ቀርቶታል።እሱም የማያ ወላጆች ናቸው። ደህንነቱን ካላወቁ በጭንቀት የሚሞቱ መሠለው። " i think you are fine now!" አለ ፕሮፌሰር እስጢፋኖስ የኋላሸት ሜላትን ስላገኛት ጭንቀቱ ሙሉ ለሙሉ የጠፋ መስሎት "አዎ በትንሹ ግን ፕሮፌሰር የልጆቼ አያቶች የእኔንም ሆነ የልጆቹን ደህንነት ካላረጋገጡ በጣም ይጨነቃሉ።ስለዚህ የምትችል ከሆነ እንደው ብትተባበረኝ!!" አለ " ok የማያ ወላጆች! ኦሺ የሆነ መፍትሔ እናበጅለታለን የአካባቢውን ሁኔታ አጥንተን አንድ ልጅ ልኬ እንዲያገናኝህ አደርጋለሁ!!" አለና ቀለል አድስጎ መለሰለት። "በጣም አመሰግናለሁ!!" በማለት ከአንገቱ ጎንበስ በማለት ምስጋናውን ችሮ ተቀመጠ። በብዙ ሀገራዊ ጉዳዮችና የጋራ ፍላጎቶች ላይ ከተግባቡ በኋላ "ከዚህ በኋላ ማን ማን ስጋት እንደሆነብን ማን በዚህ ምስጢራዊ ተልዕኮ ተዋናይ እንደሆነ ማወቅ ይኖርብናል። ስለዚህ እሱን አንተ ተመራመርበት እንዲሁም የማን እጅ ከጀርባው እንዳለም ማወቅ ያስፈልጋል። ስለዚህ የናፊባን ጉዳይ በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ አዲስ ነገር እንደምታገኝ ተስፋ እያደረኩ ለሚኖርህ ማንኛውም ጥያቄና አስተያየት ካለ በማንኛውም ጊዜ መጥተህ ልታናግረኝ ትችላለህ "ጨለና ፍፁም በሆነ ፈገግታ እጁን ዘርግቷ ሰላም ካለው በኋላ በክብር ወደ ክፍሉ እየሸኘው እያለ "ፕሮፌሰር እነዚህ ምስሎች በጣም ነው ልብ የሚነኩት። እጅግ ማራኪዎች ከመሆናቸውም በላይ ነብስን በሀሴት ያረሰርሳሉ"አለ ኢንስፔክተር ሸዋንግዘው። "አየህ እዚች አገር ላይ በርካታ ሀብቶች አሉ።ሁሉም በሚባል ደረጃ ሙሉ ነው። ኢትዮጵያዊያን ሀብታቸው ላይ ተኝተው ነው የሚለምኑት። ምዕራባዊያን ደግሞ ያለህን ሀብት እንድትጠቀም ሳይሆን የእነሱን ስንዴና ገንዘብ እንድትለምን በሀገርህ ሰርተህ እንደምታድግ ሁኔታዎችን ከማመቻቸት ይልቅ ወደ ሀገራቸው ሄደህ እንድታገለግላቸው ነው የሚያደርጉት። ለዚህ ነው እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ እነዚህን ሀገሮች የምጠላቸው። ለምሳሌ ምዕራባዊያን እርዳታ ሲያደርጉ ብር ብቻ ነው የሚሰጡህ። ቻይናና ራሺያ ግን ብር አይደለም የሚደግፉት ህንፃ ወይም መንገድ ወይም ድልድይ ማሰሪያ ከሆነ የሚያስፈልገው ያን ህንፃ ድልድይና መንገድ ሰርተው ነው በብድር የሚያፅፉት።አሜሪካና የምዕራቡ ዓለም ግን እንደዛ አይደሉም። እና እኔም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ እነዚህ የምትመለከታቸውን ምስሎች በቅርብ እርቀትና በየቦታው የሰቀልኳቸው ሰርክ ባየኋቸው ቁጥር የባከነው ፍቅራችን የባከነው ሀብታችን ያለቦታው የተዘራው ወጋችን በደንብ ሳናጌጥበት የጠፋውን ስልጣኔያችንን እንዲያስታውሰኝና እነዚህን ውብ ሀብቶቻችንን በመመለስ ታላቋን ኢትዮጵያ መስራት ስለሆነ ነው" ሸዋንግዛው የተለመደውን የአድናቆት ምልከታ እየተመለከተ ክፍሉ እስኪደርስ ድረስ እያዳመጠው ነበር።
ራዕይ የሰውን ልጅ በዓላማ እኖዲኖር የሚያደርግ ቀጥተኛ መንገድ ነው።የሰው ልጅ ወደዚህ ምድር የመጣበትን ዓላማ በፀሎት መጠየቅ ይኖርበታል ሁሉም እንደየእምነቱ ባለው ጥንካሬ ሊማፀን ይገባል። ምክንያቱም ፈጣሪ መቼም ያለምንም ነገር ተፈጥረን ይቺን አለም እንድንቀላቀላት አያደርግምና። ያን ዓላማ ሰዎችንና ፈጣሪያችንን በምን እንድናገልግል እንደፈጠረን አንድ ጊዜ ጠይቀን ከዛ በኋላ በምስጋና እንዲገልፅልን ማድረግ ይኖርብናል። አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ራዕያቸውን በግልፅ ሳያስቀምጡ ፈጣሪ የሆነ ታዕምር እንዲፈጥርላቸው ይሻሉ። ይህ ስህተት ነው መሆን የለበትም። ላስቀመጣችሁት ራዕይ የሚሆን ገንዘብም ሆነ ሀብት በግልፅ ካስቀመጣችሁ በኋላ በየቀኑ ያን ራዕይ የምትመለከቱበት ቦታ ሰቅሎ ለአእምሯችን ፕሮግራም ማስደረግ ነው። አአምሯችን በተደጋጋሚ የሚመለከተውንና የሚያየውን ነገር የመቀበልና ይሆናል የማለት ከዛም የማድረግ አቅም አለው። ፕሮፌሰር እስጢፋኖስ የኋላሸትም ያደረገው ይሄን ነው። የሚፈልጋትን ኢትዮጵያ ለመስራት ካሰበ በኋላ የሚፈልጋትን ኢትዮጵያ የሚገልፁለትን ምስሎች በየግድግዳው በመስቀል በየቀኑ ለአእምሮው እየነገረ የሚሰራው። ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ለነበራቸው ቆይታ አመሰግኖ ወደ ክፍሉ ሊገባ ሲል "ለልጆቹም የሚሆን ቦታ ስላለ አታስብ እዚህ የምርምር እውቀታቸውን ሀ ብለው የሚጀምሩበት ቦታ ይሆናል።የፍላጎታቸውን አዝማሚያ ተመልክተን እንዳይጨናነቁ አእምሯቸውን ዘና ሊያደርጉ የሚችሉ የሶፍትዌር ፈጠራዎች በአፕሊኬሽን መሠረት ስላሉ ልጄ በሚገባ ያሳያቸዋል። ስለዚህ ስለ እነሱም ሳታስብ ሙሉ ጊዜህን ስራው ላይ ብቻ ትኩረት አድርግ። ስለተሕሚድ መጀመሪያ ስሰማ ተገርሜ ነበር።እዚህ እኛ ጋር የሚሰራ አንድ ልጅ አለ በእሱ በኩል ነበር ስለ እሱ ያወቅነው። እና ጥሩ እያገዘህ እንደነበር በሚገባ እናውቃለን። እርሱም ለጥበብ ቅርብ ስለሆነ ብዙ ነገሮች ላይ ሀሳብ ያዋጣልሀል ብዬ አስባለሁ።ለማንኛው አንተ በፈለከውና በሚመችህ መንገድ ስራ። ብቻ ዋናው በፍጥነት ሰርተን የኢትዮጵያን አረሞች ዳግም እንዳይበቅሉ አድርገን መንቀል ነው።" ብሎ እጁን ትከሻው ላይ ደገፍ አድርጎ አንገቱን ከነቀነቀ በኋላ ወደ ቢሮው ተመለሰ።

@amba88
@amba88
3.3K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-31 20:57:31 "ናፊባ"
ክፍል ~ ዘጠና ኁለት~
በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888
" ጤና ይስጥልኝ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው" በማለት በቀኝ እጁ ሰላምታን ከሰጠው በኋላ በግራ እጁ እንዲቀመጥ አመላከተው። የሰውዬውን አክብሮትና ፈገግታ ከልቡ እየተቀበለ ከአንገቱ ዝቅ በማለት ለአክብሮቱ ምስጋና በማቅረብ ተቀመጠ። " እንግዲህ በዚህ መንገድ ስለ ተዋወቅን በጣም ይቅርታ እጠይቃለሁ" በማለት ሁለት እጁቹን አገናኝቶ ወደ ግንባሩ በማቅረብ እንደ ህንዶቹ ምስጋናና ይቅርታ ቡራኬ አቀረበ።ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ያለምንም ቃል አንገቱን ሰበር በማድረግ ብቻ እሺታውን ገለፀለት። "ጥሩ እንግዲህ ጊዜ ለሁሉም ነገር አመላካች መስታውት ነውና አንተን የመሰለ ኢትዮጵያዊ በማወቄ በማግኘቴም ደስተኛ ነኝ። " ኢንስፔክተር በፅሞናና በዝምታ ብቻ እያዳመጠው ነው። "እኔ ሀሳብህንና ፍላጎትህን መጋራት ብቻ ሳይሆን ማራመድ የምፈልግ ግለሰብ ነኝ። ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው በአንተ እድሜ እያለሁ ትንታግና ቁጡ እልኸኛ ነበርኩ።እና አንተን ስመለከት በእያንዳንዱ ሁኔታህና ድርጊትህ ራሴን የምመለከት ነበር የሚመስለኝ።ሀቀኝነትህን ታማኝነትህን ከምንም በላይ እወድልሀለሁ አከብርልሀለሁ። ለብዙ ጊዜ ከተከታተልኩህ በኋላ ነበር ልረዳህ እንደሚገባ ያመንኩት። አሁን አጉል ታሪክ አንስቼ በማውራት ጊዜያችንን አልገድልም። ምክንያቱም እዚህ በምናባክናት ደቂቃ ውስጥ እንኳ ብዙ ሰቆቃ ላይ ያሉ ዜጎቻችን ስላሉ። ስለዚህ ስለ እኔ ሙሉ ነገር ባይሆንም ግርታህን ለማንሳት ያህል የተወሰነ ልንገርህ ፕሮፌሰር እስጢፋኖስ የኋላሸት እባላለሁ። ለበርካታ አመታት በራሺያ ዜኒትስ በርግ በምርምር ስራዎች ስሳተፍ እና ስሰራ የነበርኩ ሰው ነኝ። አንተን አለቃዬ እየፈለገህ ነው ብሎ ወደ እኔ ያመጣህ ልጄ ነው። የመጀመሪያ ድግሪውን በሞስኮ ቶሎስቶይ ዩኒቨርሲቲ በኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ የተመረቀ ሲሆን ሁለተኛ ዲግሪውን ደግሞ እዛው በሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ሰርቷል። ለብዙ አመታት ኑሯችንን እዛው ብናደርግም ዳሩ አይናችንም ልባችንም እዚች ታሪካዊት ሀገር ነበር። እዛው ሀገር እያለሁ ነበር ይሄን አካባቢ በህጋዊ መንገድ አስፈላጊውን ካሳ ለባሎቦታዎቹ ሰዎች ከፍዬ የገዛሁት። ከዛም ቀጥታ ወደዚህ የህንፃ ግንባታ ገባሁ።መንግሥት ይሄን ልዩ የሆነ ምስጢራዊ የሆነ ድብቅ ቦታ እንዳያየው በከፍተኛ ጥንቃቄና በራሺያ መንግስት ድጋፍ ልሰራ ቻልኩ። ያው መቼም ስለ ራሺያ ብዙ ነገር ታውቃለህ።ኢንስፔክተር እንደመሆንህ የቀድሞዋን ሶብዬት ሕብረት ታሪካዊና ፖለቲካዊ ዳራ ሳትጎረጉር አትቀርም። እናም የአሜሪካን ፍላጎት ብቻ የሚያንፀባርቀውን አሻንጉሊት የኢትዮጵያን መንግስት ለማስወገድ ያለን አማራጭ በረጅም አመት እቅድ በዚህ መልኩ መደራጀትና ቀስ በቀስ ማስወገድ ነበር። የምዕራቡ ዓለም እና የአሜሪካ አካሄድ ህገወጥ ወረራና ዘመናዊ የባርነት ቀንበር ያነገበ ፍልስምና በተመለከትኩና ባየሁ ጊዜ ይቺን መልዕክተ ዮሐንስ ብዬ የእወቀት አድማሴን ያሰፋሁባትን የፊደልን ቅጠል የዘነጠፍኩባትን፣ የአእዋፋትን ዝማሬ እየሰማሁ የንጋትን ደዎል ባወጀኩባት ሀገር ሌሎች ላይ የሆነው እንዲሆን ባለመፍቀድ አንድ ታላቅ ራዕይ በማንገብ ሀገሬን ከነዚህ ሰይጣኖች መታደግ ሆነ። ለዚህ ዓላማዬም ይረዱኝ ዘንድ በርካታ ተማሪዎችን ከየትምህርት ቤቱ በመልቀም ላለፉት አስር አመት በራሺያ በማሰልጠን የዚህ ምስጢራዊ ተልዕኮ ቡድን አባል አድርጌ በተንኳቸው። በየህዝቡ ላይ ተሰግስገው አስፈላጊውን መረጃ እንዲሰበስቡ በማድረግ ስራዬን በጥንቃቄ እየቀጠልኩ ለልጆቹ እንደ ወጣት ጎልማሳ ጎደኛም እንደ የእውቀት አባትም በመሆን ስራችንን እየሰራን ባለንበት አንድ ምስጢራዊ ቡድን ደግሞ በሌላ ፅንፍ እየተንቀሳቀሰ እንደሆን ተረዳሁ። በዚህም በቂ ክትትል በማድረግ መረጃዎችን በመሰብሰብ አንድ አብሯቸው ይሰራ የነበረን ልጅ በተለያዩ አባላቶቻችን በሰው በሰው በማድረግ አስፈላጊውን ምርመራ ስናደርግበት ልጁም ስራቸውን ለማገለጥ እንደሚፈልግና ነገር ግን ይሄን ምስጢር ቢያወጣ እጣፈንታው ሞት እንደሆነ በፍርሃቴ ውስጥ ሆኖ አጫወተን። ከዛ ምስጢራዊው ቡድንም እኛ እንድናርፍባት የምንፈልግባትን ኢትዮጵያ ትርጉም ያዘለ "ናፊባ"የተሰኘች የምስጢራዊ ተልዕኳቸውን ማስፈፀሚያና መከተያ ህግ ያዘለች።አጠቃላይ ስለቡድኑ ምንነትም በሚገባ የምትገልፅ መፅሐፍ እንደሆነች ከልጁ በወሰድነው መረጃ መሠረት አንዳንድ መረጃዎችን ስናሰባስብና በዚህ ቡድን ላይ መንግስት የራሱን ፍላጎት ለማሟላት እና ህዝቡን ለማስፈራራት የሚጠቀምበት የአሸባሪ ቡድን እንደሰራ በመገመት ማጣሪያዎችን ስናደርግ።ይህን ቡድን መንግስትም እንደማያውቀው ተረዳን። ከዛም ባለስልጣናቶች ይኖሩበት ይሆናል በሚል ፍርሃት መረጃውን ለማንም እግዳይደርስ ካደረግን በኋላ ስለ አንተ በጎ ስራና ጥሩ ስነምግባር ስናውቅ በህዝቡም መልካም የሆነ ቅቡልነት በመማረካችን እኛስ ከህዝቡ ወገን አይደለን በማለት አንተን መርዳት ዋናኛ ተግባራችን አደረግን። ይህን ስራችንንም የአንተን የምርመራ ጥበብ ለመጨመር ብዙም በማይከብዱ እንቆቅልሾች እያደረግን እስከዚህ አደረስንህ። ነገር ግን በተደጋጋሚ በአንተ ስሜታዊነት የተነሳ ከመንግስት ሀላፊዎች ጋር ቅሬታ እየገባህ ስትሄድ ሁኔታህ አሳስቦን ቀድመን ልንሰውርህ እያሰብን ባለበት መንግስት ቀደመን።ከዛ በኋላ የሆነው ይሄው ነው። ከምንም በላይ የአንተና የልጆችህ የሁላችሁም ሕይወት በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኑ ነው።" አለና ንግግሩን ገታ አድርጎ ነጭና ጥቁር የተቀላቀሉበትን ፂሙን ይነካካ ጀመር። ቀልጣፋና ንቁ የሆነ ሰው መሆኑን እየተመለከ ለረጅም ደቂቃ ሲያዳምጠው ከቆየ በኋላ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው " በጣም የሚገርም ነው ፕሮፌሰር።በቅድሚያ ከእኔ በላይ የተከበረ ሙያዎን ትተው ለትውልድ ሀገረዎ በማሰብ ያደረጉትን ነገር በሙሉ አደንቃለሁ። አከብራለሁ። ለዚህ ውለታችሁም ታሪክ የሚዘክራችሁ ይሆናል። በዚህ ደረጃ በመደራጀታችሁም በጣም ነው የተገረምኩት። ይህ የሚያሳየው ድንበር አልባ ሀገር እንዳለችን ነው። የእናንተስ ለመልካም ነገር የተቋቋመ ምስጢራዊ ቡድን ነው። ለሌላ ችግር የተቋቋመ ምስጢራዊ ቡድን በዚህ መልኩ ስለመደራጀቱም ጥርጥር የለኝም።ምክንያቱም የሀገሪቱ ደህንነት ምን ያህል የዘቀጠ እንደሆነ ያሳያል"በማለት በቁጭትና በንዴት አንገቱን አወዛወዘ። "አሁን እሱን ማሰቡ በእሱ መነመደዱ እርባቢስ ነው። የሚጠቅመው ቀጣይዋ ኢትዮጵያን በደህንነቱም በጥበቃውም ረቂቅ ንስር ካሜራዎቿን በመግጠም መቆጣጠር የምንችልበትን ስራ መስራት ነው። ስለዚህ አንተ አሁን የምትሰራው ስራ የናፊባ ምስጢራዊ ቡድን ማንነት እንድታጣራ እንድትመረምር ነው። በመቀጠል የደህንነት ስጋት ያለባቸው ዘመዶች በቅርበት ካሉህ እንድናመጣቸው ነው።"አለ ፕሮፌሰር ቆፍጠን በማለት። "ማንም የለም። ባለቤቴ ግን ስለ እኔ የሆነ ዜና ከሰማች በቀጥታ ልምጣ ማለቷ አይቀርም" አለ ሸዋንግዛው። ፕሮፌሰሩ በድንጋጤ በርገግ ብሎ "የት ነው የምትኖረው?" " አሜሪካ" ሸዋንግዛው በፍጥነት መልሶ የፕሮፌሰሩን የፊት ገፅ ተመለከተ። " ምንም ችግር የለም። ዜናው ሁሉም ጋር ስለተዳረሰ ባለቤትህ እዛ መሆኑን በፍፁም ረስቼዋለሁ። እሺ አሁኑኑ እንደውልላታለን "አለና ስልኳን ተቀብሎ ፊት ለፊቱ ባለው ስክሪን ተች ላይ ፅፎ ደወለላት። በተደጋጋሚ ቢሞክሩም አልነሳ አላቸው። "በቃ እንደታፈንኩ ከሰማች መንገድ ትጀምራለች ። ከዚህ በላይም ብቻ ባለቤቴ በጣም ነው የምትጨነቀው " አለ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው፣ ፕሮፌሰሩ መደወሉን አላቆመም......

@amba88
@amba88
2.7K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 17:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-30 21:17:32 "ናፊባ"
ክፍል ~ ዘጠና አንድ
በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888
የራሺያው Russian Times ጋዜጣና የአሜሪካው Washington Post የኢንስፔክተር ሸዋንግዛውን መታፈን የዜና አርዕስታቸው በማድረግ የእርሱንና የልጆቹን ምስል የፊት ገፅ በማድረግ ከሰፊ ሀተታ ጋር ለንባብ አበቁ። የኢትዮጵያ መንግስት በፍጥነት እየተሰራጨ ላለው የኢንስፔክተሩ አፈና ይህን ያህል አጥጋቢ መልስ ባይሆንም አፈናውን እንደሚቃወምና መንግስት አስፈላጊውን ሀይል በመጠቀም ወንጀለኞችን ለፍርድ እንደሚያቀርብና ኢንስፔክተሩን ነፃ እንደሚያወጣ ዝቷል። ነገር ግን ዜጎቹ ደግሞ በተደጋጋሚ የመንግስትን ለዘብተኝነትን እየተቸ ከአንድ ጊዜም ሁለት ጊዜ የመንግስትን የተሳሳተ አካሄድ ስለሚቃወም ኢንስፔክተሩን ያፈነው ራሱ መንግስት ነው ባይ ናቸው። ይህንን የህዝቡን ፍላጎት የሚያራምዱ በርካታ ተከታይ ያላቸው የማህበረሰብ አንቂዎችም በስፋት እያስተጋቡት ይገኛሉ። በሌላ በኩል ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው በኃላፊነት የሚሠራበት ዋና የግድያ ወንጀል ክፍል ያሉ ባልደረቦች በኢንስፔክተሩ መታፈን ዙሪያ የመንግስት እጅ ይኖርበታል በማለት ጥርጣሪያቸውን ያልደበቁ አባላቶች እንዳሉ አንዳንድ የማህበረሰብ አንቂዎች የተለያዩ ማስረጃዎችን ዋቢ በማድረግ በማህበራዊ ትስስር ገፆቻቸው ሰንደዋል። የኢንስፔክተሩ መታፈን ታላቅ ፖለቲካዊ ኪሳራ ነውና በኢንስፔክተሩ ጉዳይ መንግስት የወሰደው አቋም ካለ ባስቸኳይ ማብራሪያ መስጠት አለበት ሲል የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ይገልፃል"በማለት የፕሬዚዳንቱን ሙሉ ሀሳብ ያሰፈረውን ዜና በስፋት ያትታል። በአንፃሩ የሩሲያ ታየምሱ ዜና ደግሞ "መንግስት የህዝቡን ስሜትና ፍላጎት በሚገባ ሊረዳና ሊያከብር ይገባል። በማንኛውም ዓለም የመንግስት ጠመንጃ ያዥ ሀይሎች እውነትንና ፍትሕን በሚሹ አቢዮተኞች ድል ተደርገዋልና መንግስት ከወዲሁ የህዝቡን ተቃውሞ በጠመንጃ እፈታለሁ ብሎ የሚያስበውን ከመጀመሪያው እንዳይጀምር ከጥልቅ ምሳሌና ማብራሪያ ጋር የሩሲያን የውጪ ጉዳይ ምኒስቴር ቃለ አቀባይ ዋቢ በማድረግ አስፍሯል። በአንድ ጀንበር የአለምን የዜና ሽፋን የተቆጣጠረው የኢንስፔክተሩ መሰወር የኢትዮጵያ መንግስትን ክፉኛ ከማስቆጣትም በላይ አስፈርቶታል። ህዝቡ ደግሞ ከቀፎው ወጥቶ የመንግስት ሁነኛ ቦታዎች ላይ ተቃውሞ ለማስነሳት በመንጋ ለመውጣት የልባቸውን ደወል ብቻ እየተጣበበቁ ይገኛሉ። ውጤት አልባው የፓርላማና የምኒስቴሮች ስብሰባ አሁንም በጭንቀትና በግራ መጋባት ያለ ስአታቸው ቀድመው ወንበራቸውን ይዘው በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።የጦር አዛዦችና የመከላከያ አባላትም በዚህ ልዩ የሆነ ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ በጊዜ ተገኝተዋል። በዚህ አስቸኳይ ስብሰባም የጦር ውሳኔዎች ሳይቀሩ ይተላለፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። የኢትዮጵያ መንግሥት አይንና ጆሮ ነው የሚባለው የቴሌቪዥን ጣቢያ ዋና አስተዳዳሪም በስብሰባው ላይ ተገኝቷል።
**********
"አለቃ ይሄ ነገር በጣም እየተስፋፋ ነው። ምንም የምናደርገው ነገር የለም?" "የምናደርገው ነገርማ አለ አሁን ነው ወደ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው መሄድ ያለብኝ።"በማለት በፈገግታ ታጅቦ ቀጥታ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ወዳረፈበት ክፍል ሊገባ ሲል ከእንደገና ሀሳቡን በመቀዬር "አይ ጥሩ አይደለም ወደ እኔ ክፍል እሱ ቢመጣ የተሻለ ነው። ልጆቹ ፊት ማናገሩ ጥሩ አይደለም። ምን አልባት ፍርሃት ሊያድርባቸው ይችላል። ስለዚህ እናንተ አምጡልኝ" በማለት ወደ ዋና ቢሮው የሚወስደውን ኮሪደር ይዞ መሄድ ጀመረ። ምድራዊው ሰፊ ነፀብራቅ።በርካታ ኮምፒወተሮችና ካሜራዎች የሚበዙበት ይህ ከምድር በታች የተሰራ ህንፃ ፍፁም እጅግ በሚማርኩ ጌጣጌጦችና የቀለም ቅቦች ዲዛይኖች የተዋበ ሲሆን በየግድግዳዎቹም ላይ የኢትዮጵያን መልክና ገፅ የሚያንፀባርቁ ስዕሎች ተሰቅለውበታል። ለአብነት ያህል የአልነጃሺ መስጊድ፣የንግስተ ሳባ ደንገጡሮችና ሎሌዎች እንዲሁም ንጉሱ ሰለሞንን ለመጎብኝት ወደ እየሩሳሌም በመሄድ ላይ እያለች የሚያሳይ ምስል፣ የቅኔ ተማሪዎችና ቁምጣ ለብሰው በረባሶ ጫማቸውን ተጫምተው ራሳቸው ላይ በእዳይት የተጠለፈ ጉኒና በማድረግ ከመርጌቶች ትምህርታቸውን በዋሸራ ሲከታተሉና ሲያጠኑ የሚያሳይ ምስል ይታያል እንዲሁም ወሎ ወረባቦና ሀራ ላይ ታላቅ ሊቅ ዑለማዎች ደረሳቸውን ቁራዕን ሲያስቀሩ የሚያሳይ ምስል፣ በሌላኛው ኮሪደር ደግሞ በሬዎቹን እያረሰ ከኋላው የምታጎለጉለውን ሚስቱን ዞሮ ሲመለከት የሚያሳይ ምስል፣ በሌላኛው ግድግዳ ደግሞ የገደሉ አፋፍ ላይ ተቀምጦ ከፊት ለፊቱ ማዶ ላይ የሚወርደውን የፏፏቴ ድምፅ እየሰማና ጭሱን እየተመለከተ በዋሽንቱ ተፈጥሮን በትንፋሹ የሚዘክር ድንቅ እረኛ ይታያል። ይህ ምስል ድምፅ ሲያወጣ ነፍስን በዋሽንቱ ዜማ ሲያመንን ከምስል አልፎ በድምፀም የሚያጋባ ነው። በሌላኛው ገፅ ደግሞ አንዲት አቅመ ደካማ የምትመስል ሴት አንገቷን ወደ ግራ ጠንዘል አድርጋ ወፍጮ ስትፈጭ ያሳይና ከእሷ አናት ላይ ደግሞ ዶሮዎች የቤቱ ምሰሶ ላይ ቆመው ያሳያል። ይች የተንጋደደች የገጠር ጎጆ ውስጥ የሚታይ ምስልም ሌላኛው ትልቅ ሀሳብ የተንፀባረቀበት ምስል ነው። እነዚህነና ሌሎችም በርካታ አይነት ምስሎች ያሉበትን ቦታ አልፎ ወደ ቢሮው ሊገባ ሲል በሩ ላይ በትልቅ ሸራ የሚታየው ምስል ይበልጥ ኢትዮጵያን የሚገልፅ ይመስላል ሁለት መርጌቶችና ሼሆች በሀሴት ፈገግ ብለው የሚታዩበት ምስል ሲሆን ከጎኑም በርካታ ሰዎች የሚገበያዩበት የገበያ ቦታ ይታያል። ምስሉ የድሮ መልክ እንዲኖረው black &white ቀለምን ተጎናፅፏል።በሩን ከፍቶ በቀጥታ ኮቱን አውልቆ የኮት ማስቀመጫው ላይ አስቀምጦ ወንበሩ ላይ ተቀመጠ። ወንበሩን ወደ ኋላና ወደፊት እያደረገ አንድ ክብ የሚሆን ከተሽከረረከ በኋላ ከመሳቢያው አንድ ሪሞት አውጥቶ የቀይ መብራቷን ሲነካ ፊት ለፊቱ የተቀመጠው ባለ 45 inch የቴሌቪዥን እስክሪን ተከፍቶ በጥሩ ጥራት እያንዳንዱ ኮሪደር ላይ ያሉ እና ውጪ ላይ የተገጠሙ ካሜራዎቸን ይመለከት ጀመር።
ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው የልጆቹን ፀጉር እያሻሸ ባለበት ወደ ጆሮው ጠጋ ብሎ" አለቃዬ አሁን ሊያገኝህ ይፈልጋል። ለአንተና ለልጆችህ ባለው ፍቅርና አክብሮት የተነሳ ወደ ክፍልህ መጥቶ ሊያገኝህ ነበር ሀሳቡ ነገር ግን ልጆችህ እንዳይፈሩ በማሰብ ወደ ቢሮው እንድትመጣ ይፈልጋል" አለ ቀልጠፍ ያለና ፊቱ ላይ የፈገግታ ፅንፍ የማይለየው ወጣት። ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው በፅሞና ካዳመጠው በኋላ በወጣቱ ሀሳብ በመስማማት አንገቱን ነቀነቀና ልጆቹን በቀስታ አስተኝቶ ተነስቶ ይከተለው ጀመር። ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው የግድግዳ ምስሎቹን ሲመለከት ፍፁም የሆነ አግራሞትን ፈጥሮበታል። በዛን ስአት በርካታ ጥያቄዎችን ራሱን እየጠየቀ ስለሰውዬው ሀገራዊ ፍቅር ለመገመት አፍታ አልፈጀበትም።ስዕሎቹ እንኳን የሀገር ፍቅር የሚሰማውን አንድ ኢትዮጵያዊ ይቅርና የሌላ ሀገር ዜግነት ያለውን ሰው ሳዬቀር የሚያማልሉና ሆድ የሚያባቡ ናቸው።ፍፁም ሰላማዊ ና እረፍት እንዲሰማ የሚያደርጉ ኢትዮጵያዊነትንና ኢትዮጵያዊያንን የሚገልፁ በመሆናቸው ኩራትም ሀሴትም ተሰምቶታል። ምስሎቹን ለመመልከትና በደንብ ለማጤን ዘግየት ሲል ከፊት ለፊት ሆኖ የሚመራው ወጣት ቆም ብሎ ሲጠብቀው ከእንደገና እየጠበቀው መሆኑን ሲመለከት ሲከተለውና ሲተያዩ በፈገግታ እየተሸነጋገሉ ዋና ቢሮው ደረሱ።

@amba88
@amba88
2.7K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 18:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 21:14:07 ሰላም እንደምን አመሻችሁ ዮቶራዊያን እስኪ ዛሬ በአንድ ወሳኝ ሀሳብ ላይ እንመካከር።

ስለ ራዕይ እናውራ። ራዕይ ምን ማለት ነው? ለምንስ ያስፈልጋል?
2.7K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ