Get Mystery Box with random crypto!

'ናፊባ' ክፍል ~ ዘጠና አራት~ በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888 'መኖር የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ድ | የዮቶር ልጅ - አምባዬ ጌታነህ

"ናፊባ"
ክፍል ~ ዘጠና አራት~
በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888
"መኖር የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ድርሻው ብቻም ሳይሆን
ኃሴት እንዲያገኝ የሚያደርገው እጣ ፈንታው ነው።
ረሀብና በሽታ ብቻ ሰውን አይገለውም።
ቤት የሌላቸው በርካታ ሰዎች ቢኖሩም አንተ ግን....."
" አንተ እስክትመጣ ድረስ በተደጋጋሚ እያነበብኩት ነበር። ፍፁም አልገባህ አለኝ። የሆነ ትርጉም ግን እንዳለው ልቤ ይነግረኛል።ብዙ የቅኔ አመስጣሪዎች ሀሳባቸውን በስነግጥም እና በስድ ንባብ ያስቀምጣሉ። እንዲሁም የሀገራችን ላቃውንትም ምስጢርን በብራና ሀሳብ ጥቅል ከይነው ለትውልድ ያስቀምጣሉ። ያን ቁልፍ የሚያገኝበት በርካታ ጥቅሎችም ይቀመጡለታል። ይህም ልክ እንደ ዴርቶጋዳ ላይ እንደተቀመጠው የሎሬት ግጥም ላይ እንዳለ የምስጢር ሀሳብ ነው። እና የውጮቹ ሰላዮችና ጠቢባን በርካታ ከያኒያን እና የደህንነት ሰዎች ሳይቀሩ እንቆቅልሾችን ይጠቀማሉ። ለምሳሌ row and column puzzle በሚባል እንቆቅልሽ ያስቀምጣሉ።በዛ መሠረት ከሁሉም አራፍተነገሮች የመጀመሪያ የመጀመሪያ ቃሎቹን ወስጄ ደረደርኩ
መኖር
ኃሴት
ረሃብና
ቤት
ብሎ ቁልቁል በመፃፍ ለኢንስፔክተር ሸዋንግዛው አሳየው "እኔ እንደሚመስለኝ እነዚህ ሰዎች የሚኖሩት እና ከመኖርም በላይ ኃሴት የሚያገኙት ረሀብ በተጠናወታቸው ሰዎች ነው። ለዚህም ስለቤት አያስቡም።ምክንያቱቤ ቤት የሌላቸው በርካታ ሰዎች ቢኖሩም አንተ ግን... ይላል።ይህም ማለት ቤታቸውን ጥለቅ በረሃብ ምክንያት ይሰደዳሉ። በዚህ ሀሳብ ላይ የተሰናሰለ ይመስለኛል"አለ ተሕሚድ።ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ግን አንዱንም ያለውን አልሰማውም ነበር። አእምሮውና ልቡ የተደረደሩት ቃላት ላይ ነበር። ተሕሚድ የሸዋንግዛውን ምንም አለማለት እና ከእርሱ ጋር አለመሆኑን የተረዳው በኋላ ነበር። "ፍቅሬ አጎቴ ሌላ ሀሳብ ውስጥ ገብቷል እኮ ዝም ብለህ ነው ስትደክም የነበረው"ብላ ሳቀች።
"አገኘኋት!!! መ..ኃ..ረ..ቤ!" አለ ሸዋንግዛው። ተሕሚድ በቀጥታ ያወጣቸውን ቃሎች ተመልክቶ የመጀመሪያ የመጀመሪያ ቃላቸውን ወስዶ ሲደረድር ኢንስፔክተር የተናገረውን ስም አገኘ። መኃረቤ!!! "የሰው ስም ነው?" አለ። "በሚገባ እንጅ ለዛውም የመጀመሪያው ሟች ኄኖክ የቤት ሰራተኛ ከዛ በኋላም እዛ አትሆንም ብለን ትላንት የሞተው የዋና ሳጅን አክሊሉ የቤት ሰራተኛ ሆና ነበር። ነገር ግን ከወራት በፊት ተሰወረችብን"አለና በምናብ ወደ ኋላ ሄዶ ሒዎትን በኄኖክ እና ዮዳሔ ግድያ ተጠርጥራ ለምርመራ በነበረችበት የኄኖክ ሰራተኛ በመሆኗ እንደምታውቃት እና መረጃ እንድትሰጥ መኃረቤ ስትጠየቅ በጣም ደንግጣ ነበር። በምላሿም ጥርጣሬ እንደገባውና ግን ምን አልባት የዛኑ እለት አስፈራርታት ቢሆንስ ብሎ ያሰበው ትዝ ብሎት"ራሱን በመነቅነቅ ቀጥታ ወጥቶ ወደ ፕሮፌሰር እስጢፋኖስ በመሄድ ስለ መኃረቤ ሁሉንም ሲነግረው። ከተሽከርካሪው ወንበር ቀስ ብሎ ተነሳና ፈገግ ብሎ "የሼክስፔር ተዋናይት ናታ?" አለ "ማለት አልገባኝም!" አለ ሸዋንግዛው እንዲያብራራለት " የእንግሊዞች የጥበብ ጣኦት ሼክስፔር ነው። እጅግ በሚባል ደረጃ በጣም ይወዱታል። የሱን ስራዎች ከሰራው በላይ በዓለም እንዲዳረስና እንዲስተጋባ አድርገዋል። እና አርት በጣም ያስደስታየዋል ድርሰትና ትወጣ ስራቸውን ከሚያቀሉላቸው ነገሮች ቀዳሚዎቹ ናቸው። ለዚህም ሰላዮቻቸውን በከፍተኛ ጠሰንቃቄና ብቃት የትወና ጥበብን ያስተምሯቸዋል።በየሀገሩ የሚልኳቸውና ተልዕኳቸውን የሚያስፈፅሙሏቸው ሰዎች የትወና በቃታቸው በጣም ትልቅ ነው። አንተን ያሳምኑሀል። በቃ ከምነግርህ በላይ በጥበባቸው የአንተን ደካማ ጎንና የማመን ሀይልህን ይቆጣጠሩብሀል። ደግሞ እኛ ኢትዮጵያዊያን ለማዘንና ለሰዎች በጎ ነገር ማሰብ ቀዳሚው ተግባራችን እንደሆነ ስለሚታወቅ ይህን እንደ ትልቅ ግበአት ይጠቀሙበታል። ስለዚህ የእንግሊዞች መሣሪያ አሉ ማለት ነው። በርግጥ እንግሊዝ ከአሜሪካ የበለጠች አደገኛና መሠሪ የሆነች አገር ስለመሆኗ የክሪሚላን ፖለቲከኞች ሳይቀሩ ይናገራሉ።በራሺያውያን ራሱ በቀዳሚ በሚባል ደረጃ የሚጠሉት እንግሊዞች ናቸው።
*************
መንግስት ከጠበቀው በላይና ሊቆጣጠረው ከሚችለው በላይ ሲሆንበትና የማህበራዊ ሚዲያው ተቃውሞ ሲበዛበት የዳታ አገልግሎቱን በማቋረጥ ለማርገብ ሞከረ። በዚህ ድርጊት የተቆጡ አዲሳበባዊያን በተለያዩ አጋጣሚዎች በመቀሳቀስ ተቃውሟቸውን ለመግለፅ በአደባባይ ወጥተዋል። ህዝቡ በተመሳሳይ ስሜት ውስጥ ሆኖ በየቦታው በተመሳሳይ ስአት በመገንፈል የአዲስ አበባ ጎዳናዎችን በሰላማዊ ሰልፈኛ ተቃዋሚዎች ተጥለቀለቀች። ከፈረንሳይ የመጣው ሰላማዊ ሰልፈኞ ከሽሮሜዳ በከሉ በመነን አድርጎ በስድስትኪሎ ዩኒቨርሲቲ አድርጎ ስድስት ኪሎ ሰማዕታት ሀውልት ላይ ተገናኝተው ቁልቁል በአምስትኪሎ አድርገው ሲወርዱ መንግስት ከቅድስተማርያም በታች እንዳያልፉ ከፍተኛ የሆነ ሀይል አሰማርቶ መንገዱን ዘጋ። ነገር ግን ሰልፈኛው በቅድስተማርያም በኩል አድርጎ በሰባ ደረጃ በመታጠፍ ወደ ፒያሳ ነጎደ። ከቀጨኔ ከ አዲሱ ገበያ፣ እና ከገዳም ሰፈር በኩል የመጡት ሰልፈኞች ደግሞ ምኒሊክ ሀውልት ላይ ተገናኙ። ከጳውሎስ መድኃኒዓለም እና ዩሐንስ በኩል የመጡትም በአቡነጴጥሮስ ሀውልት አድርገው ምኒሊክ ሀውልት ላይ ተገናኙ ከአቧሪ ካዛንቺስ መገናኛ በኩል የመጣው ሰልፈኛ ደግሞ ወደ መስቀል አደባባይ እየተመመ ነው። ከልደታ በኩል ከሳሪስ ከጎተራ ከጠመንጃ ያዥ በቅሎ ቤት ከጨርቆስ አውቶብስ ተራ ከሜክሲኮ ልደታ ከተክለሀይማኖት አብነት የጎረፈው ህዝብም በለገሀር አድርጎ በስታዲዮም ብቅ ብሎ ከወደፒያሳ የተሰባሰበው ህዝባዊ ሀይልም በቴዎድሮስ አደባባይ በኩል በቸርችል ጎዳና ወርዶ በአምባሳደር አድርጎ በጊዮን ሆቴል ብቅ ብሏል።ከቦሌ መስቀል ፋለወር በኩል የመጣውም ሰው በቀይ ሽብር በኩል አሰፍስፎ ወደ መስቀል አደባባይ እንዳይገቡ በሚከለክሉ መንግስታዊ ሀይሎች ጋር ተፋጧል። በመጨረሻ ተቃውሞው እየበዛና የህዝቡ ቁጣ እያየለ ሲሄድ ብረት ለበሶቹ የፌደራል ፖሊሶች አስለቃሽ ጭስ ለመጠቀም ተገደዱ። ዳሩ ግን የነሱ አስለቃሽ ጭስ የህዝቡን ንዴት ጨመረው እንጅ ፈርተው እንዲያፈገፍጉ አላደረጋቸውም። መንግስት ለዚህ ሰልፍ ሀላፊነት የወሰደ ሰው ባለመኖሩና ምንም አይነት ህጋዊ ማረጋገጫ ሰነድ ስለሌለው ማንንም መጠየቅ እንዳለበት እና ማንን ማሰር እንዳለበት ግራ ገብቶት አብዝሀኛዎቹን በጅምላ ዝም ብሎ ወደ መኪና እንዲጫኑ ሊያደርግ ሲል ሰልፈኛው ሆ ብሎ እንደ ንብ ይወጣባቸዋል። ከዛ ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ከላይ በወረደ ትዕዛዝ ብረት ለበሶቹ ፌደራል ፖሊሶች ስፍራውን ለቀው ወጡ። "ይህ መንግስት ለሆዱ እንጅ ለህዝብ አያስብም!" "በንፁሀን ደም መቀለድ እስከየትም አያደርስም!" "ኢንስፔክተር ሸዋንግዛውን ልቀቁት! እርሱን በማሰር የህዝቡን ፍላጎት ልታስቆሙ አትችሉም።! የሞቱት እህት ወንድሞቻችንን ገዳይ እንፈልጋለን!" በማለት የተቃውሞ መፈክራቸውን በማሰማት ቀጥሉ። በዚህ ህዝባዊ ማዕበል አንድም ሰው ወጥቶ የተናገረም ሆነ ማይክ በመጠቀም የሁላቸውንም ድምፅ ለማስተጋባት የሞከረ አልነበረም። ምክንያቱም ምንም የተዘጋጀ ሳውንድ ሲስተም ስላልነበረ። ይህ እንዳይሆን መንግስት ቀድሞ በየቀበሌው ተናጋሪዎች ናቸው የተባሉ ወጣቶችን አስሯቸዋል።

@amba88
@amba88