Get Mystery Box with random crypto!

'ናፊባ' ክፍል ~ ዘጠና ሦሥት~ በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888 'መረጃውን አትሰማም የሚል እም | የዮቶር ልጅ - አምባዬ ጌታነህ

"ናፊባ"
ክፍል ~ ዘጠና ሦሥት~
በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888
"መረጃውን አትሰማም የሚል እምነት በግሌ የለኝም።ምክንያቱም በስአታት ልዩነት ነው የዋሽንግተን ፖስት ያንተንና የልጆችህን ምስል ከፊት አድርጎ ለዜና ያበቃው" ብሎ ስካይፑን እየነካካ ሳለ የመልስ ደወል ጠራ። በፍጥነት ነክቶ የስካይፑን ምስል አደብዝዞ የቤቱን ከለር ወደ አረንጓዴነት የሚቀይረውን ማብሪያ ማጥፊያ በመጫን አንስቶ ድምፁን ጨመረው። ሜላት ነበረች። ፍፁም የሆነ ሰላም እየተሰማው እፎይ አለና ሸዋንግዛውን እንዲያወራ ብቻውን ትቶት ወጣ። የተለመደ ስጋቷን ያለምንም እረፍት እያዥጎደጎደችለት ትንፋሽ አሳጣችው። ሸዋንግዛውም ሁኔታዋ ስለገባው በፈገግታና በስስት ይመለከታት ጀመር። "አሁን ምንም አትጨነቂ ያለሁበት ቦታ አስተማማኝ ነው። ስለዚህ ተረጋግተሽ ስራሽን መስራት ትችያለሽ!"
ፕሮፌሰር እስጢፋኖስ የኋላሸት ውጪ ላይ እየተንጎራደደ እጆቹን ወደ ኋላ አድርጎ እርምጃውን የሚቆጥር በሚመስል ማቀርቀር ውስጥ ሆኖ አንድ ሀሳብ መጣለትና በሩን ከፍቶ በመግባት ወደ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ጆሮ ጠጋ ብሎ "ማንኛውም ሰው ደውሎ እንዳገኘችህ እንዳትናገርእና የሚጠይቃት ካለ ምንም እስካሁን እንዳልደወልክላት እንድትናገር አድርጋት " ብሎት ወጣ። ሸዋንግዛውም አፍታም ሳይጠብቅ "የኔ ፍቅር እንዳወራሁሽ ለማንም አትናገሪ እሺ ያው መንግስት ሊያስረኝ ሲል ነው እነዚህ ሰዎች ቀድመው ደርሰው የጠበቁኝ እና ማንም ሰው እኔን እንዳገኘሽኝ ከጠየቀሽ ጭንቀት ላይ እንደሆንሽ በማሳየትና በጭራሽ እንዳልደወልኩልሽ በሁኔታሽ አስረጃቸው። በኤምባሲው በኩል ክትትል ሊደረግብሽ ስለሚችልና ንግግርሽ ሊቀዳ ስለሚችልም ላልተወሰነ ጊዜ አንደዋወልም። በጭራሽ ስጋት እንዳይገባሽ። ልጆቹም ፍፁም ደህና ናቸው። ይህን የተደዋወልንበትንም አጥፊው" አለና ተሰናበታት። ሜላት ሁኔታውን በትንሹም ቢሆን ስለተረዳችው ልትጫነው አልፈለገችም። ግን ደግሞ እስከመቼ ነው እንዲህ የሚቀጥለው? የሚል ጥያቄ ራሷን እየጠየቀች ነበር።
ኢንስፔክተር ሸዋንግዘው በትንሹም ቢሆን የፈራው ፍርሃት ለቀቀው።አሁን አንድ ሀሳብ ብቻ ቀርቶታል።እሱም የማያ ወላጆች ናቸው። ደህንነቱን ካላወቁ በጭንቀት የሚሞቱ መሠለው። " i think you are fine now!" አለ ፕሮፌሰር እስጢፋኖስ የኋላሸት ሜላትን ስላገኛት ጭንቀቱ ሙሉ ለሙሉ የጠፋ መስሎት "አዎ በትንሹ ግን ፕሮፌሰር የልጆቼ አያቶች የእኔንም ሆነ የልጆቹን ደህንነት ካላረጋገጡ በጣም ይጨነቃሉ።ስለዚህ የምትችል ከሆነ እንደው ብትተባበረኝ!!" አለ " ok የማያ ወላጆች! ኦሺ የሆነ መፍትሔ እናበጅለታለን የአካባቢውን ሁኔታ አጥንተን አንድ ልጅ ልኬ እንዲያገናኝህ አደርጋለሁ!!" አለና ቀለል አድስጎ መለሰለት። "በጣም አመሰግናለሁ!!" በማለት ከአንገቱ ጎንበስ በማለት ምስጋናውን ችሮ ተቀመጠ። በብዙ ሀገራዊ ጉዳዮችና የጋራ ፍላጎቶች ላይ ከተግባቡ በኋላ "ከዚህ በኋላ ማን ማን ስጋት እንደሆነብን ማን በዚህ ምስጢራዊ ተልዕኮ ተዋናይ እንደሆነ ማወቅ ይኖርብናል። ስለዚህ እሱን አንተ ተመራመርበት እንዲሁም የማን እጅ ከጀርባው እንዳለም ማወቅ ያስፈልጋል። ስለዚህ የናፊባን ጉዳይ በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ አዲስ ነገር እንደምታገኝ ተስፋ እያደረኩ ለሚኖርህ ማንኛውም ጥያቄና አስተያየት ካለ በማንኛውም ጊዜ መጥተህ ልታናግረኝ ትችላለህ "ጨለና ፍፁም በሆነ ፈገግታ እጁን ዘርግቷ ሰላም ካለው በኋላ በክብር ወደ ክፍሉ እየሸኘው እያለ "ፕሮፌሰር እነዚህ ምስሎች በጣም ነው ልብ የሚነኩት። እጅግ ማራኪዎች ከመሆናቸውም በላይ ነብስን በሀሴት ያረሰርሳሉ"አለ ኢንስፔክተር ሸዋንግዘው። "አየህ እዚች አገር ላይ በርካታ ሀብቶች አሉ።ሁሉም በሚባል ደረጃ ሙሉ ነው። ኢትዮጵያዊያን ሀብታቸው ላይ ተኝተው ነው የሚለምኑት። ምዕራባዊያን ደግሞ ያለህን ሀብት እንድትጠቀም ሳይሆን የእነሱን ስንዴና ገንዘብ እንድትለምን በሀገርህ ሰርተህ እንደምታድግ ሁኔታዎችን ከማመቻቸት ይልቅ ወደ ሀገራቸው ሄደህ እንድታገለግላቸው ነው የሚያደርጉት። ለዚህ ነው እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ እነዚህን ሀገሮች የምጠላቸው። ለምሳሌ ምዕራባዊያን እርዳታ ሲያደርጉ ብር ብቻ ነው የሚሰጡህ። ቻይናና ራሺያ ግን ብር አይደለም የሚደግፉት ህንፃ ወይም መንገድ ወይም ድልድይ ማሰሪያ ከሆነ የሚያስፈልገው ያን ህንፃ ድልድይና መንገድ ሰርተው ነው በብድር የሚያፅፉት።አሜሪካና የምዕራቡ ዓለም ግን እንደዛ አይደሉም። እና እኔም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ እነዚህ የምትመለከታቸውን ምስሎች በቅርብ እርቀትና በየቦታው የሰቀልኳቸው ሰርክ ባየኋቸው ቁጥር የባከነው ፍቅራችን የባከነው ሀብታችን ያለቦታው የተዘራው ወጋችን በደንብ ሳናጌጥበት የጠፋውን ስልጣኔያችንን እንዲያስታውሰኝና እነዚህን ውብ ሀብቶቻችንን በመመለስ ታላቋን ኢትዮጵያ መስራት ስለሆነ ነው" ሸዋንግዛው የተለመደውን የአድናቆት ምልከታ እየተመለከተ ክፍሉ እስኪደርስ ድረስ እያዳመጠው ነበር።
ራዕይ የሰውን ልጅ በዓላማ እኖዲኖር የሚያደርግ ቀጥተኛ መንገድ ነው።የሰው ልጅ ወደዚህ ምድር የመጣበትን ዓላማ በፀሎት መጠየቅ ይኖርበታል ሁሉም እንደየእምነቱ ባለው ጥንካሬ ሊማፀን ይገባል። ምክንያቱም ፈጣሪ መቼም ያለምንም ነገር ተፈጥረን ይቺን አለም እንድንቀላቀላት አያደርግምና። ያን ዓላማ ሰዎችንና ፈጣሪያችንን በምን እንድናገልግል እንደፈጠረን አንድ ጊዜ ጠይቀን ከዛ በኋላ በምስጋና እንዲገልፅልን ማድረግ ይኖርብናል። አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ራዕያቸውን በግልፅ ሳያስቀምጡ ፈጣሪ የሆነ ታዕምር እንዲፈጥርላቸው ይሻሉ። ይህ ስህተት ነው መሆን የለበትም። ላስቀመጣችሁት ራዕይ የሚሆን ገንዘብም ሆነ ሀብት በግልፅ ካስቀመጣችሁ በኋላ በየቀኑ ያን ራዕይ የምትመለከቱበት ቦታ ሰቅሎ ለአእምሯችን ፕሮግራም ማስደረግ ነው። አአምሯችን በተደጋጋሚ የሚመለከተውንና የሚያየውን ነገር የመቀበልና ይሆናል የማለት ከዛም የማድረግ አቅም አለው። ፕሮፌሰር እስጢፋኖስ የኋላሸትም ያደረገው ይሄን ነው። የሚፈልጋትን ኢትዮጵያ ለመስራት ካሰበ በኋላ የሚፈልጋትን ኢትዮጵያ የሚገልፁለትን ምስሎች በየግድግዳው በመስቀል በየቀኑ ለአእምሮው እየነገረ የሚሰራው። ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ለነበራቸው ቆይታ አመሰግኖ ወደ ክፍሉ ሊገባ ሲል "ለልጆቹም የሚሆን ቦታ ስላለ አታስብ እዚህ የምርምር እውቀታቸውን ሀ ብለው የሚጀምሩበት ቦታ ይሆናል።የፍላጎታቸውን አዝማሚያ ተመልክተን እንዳይጨናነቁ አእምሯቸውን ዘና ሊያደርጉ የሚችሉ የሶፍትዌር ፈጠራዎች በአፕሊኬሽን መሠረት ስላሉ ልጄ በሚገባ ያሳያቸዋል። ስለዚህ ስለ እነሱም ሳታስብ ሙሉ ጊዜህን ስራው ላይ ብቻ ትኩረት አድርግ። ስለተሕሚድ መጀመሪያ ስሰማ ተገርሜ ነበር።እዚህ እኛ ጋር የሚሰራ አንድ ልጅ አለ በእሱ በኩል ነበር ስለ እሱ ያወቅነው። እና ጥሩ እያገዘህ እንደነበር በሚገባ እናውቃለን። እርሱም ለጥበብ ቅርብ ስለሆነ ብዙ ነገሮች ላይ ሀሳብ ያዋጣልሀል ብዬ አስባለሁ።ለማንኛው አንተ በፈለከውና በሚመችህ መንገድ ስራ። ብቻ ዋናው በፍጥነት ሰርተን የኢትዮጵያን አረሞች ዳግም እንዳይበቅሉ አድርገን መንቀል ነው።" ብሎ እጁን ትከሻው ላይ ደገፍ አድርጎ አንገቱን ከነቀነቀ በኋላ ወደ ቢሮው ተመለሰ።

@amba88
@amba88