Get Mystery Box with random crypto!

'ናፊባ' ክፍል ~ ዘጠና ኁለት~ በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888 ' ጤና ይስጥልኝ ኢንስፔክተር | የዮቶር ልጅ - አምባዬ ጌታነህ

"ናፊባ"
ክፍል ~ ዘጠና ኁለት~
በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888
" ጤና ይስጥልኝ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው" በማለት በቀኝ እጁ ሰላምታን ከሰጠው በኋላ በግራ እጁ እንዲቀመጥ አመላከተው። የሰውዬውን አክብሮትና ፈገግታ ከልቡ እየተቀበለ ከአንገቱ ዝቅ በማለት ለአክብሮቱ ምስጋና በማቅረብ ተቀመጠ። " እንግዲህ በዚህ መንገድ ስለ ተዋወቅን በጣም ይቅርታ እጠይቃለሁ" በማለት ሁለት እጁቹን አገናኝቶ ወደ ግንባሩ በማቅረብ እንደ ህንዶቹ ምስጋናና ይቅርታ ቡራኬ አቀረበ።ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ያለምንም ቃል አንገቱን ሰበር በማድረግ ብቻ እሺታውን ገለፀለት። "ጥሩ እንግዲህ ጊዜ ለሁሉም ነገር አመላካች መስታውት ነውና አንተን የመሰለ ኢትዮጵያዊ በማወቄ በማግኘቴም ደስተኛ ነኝ። " ኢንስፔክተር በፅሞናና በዝምታ ብቻ እያዳመጠው ነው። "እኔ ሀሳብህንና ፍላጎትህን መጋራት ብቻ ሳይሆን ማራመድ የምፈልግ ግለሰብ ነኝ። ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው በአንተ እድሜ እያለሁ ትንታግና ቁጡ እልኸኛ ነበርኩ።እና አንተን ስመለከት በእያንዳንዱ ሁኔታህና ድርጊትህ ራሴን የምመለከት ነበር የሚመስለኝ።ሀቀኝነትህን ታማኝነትህን ከምንም በላይ እወድልሀለሁ አከብርልሀለሁ። ለብዙ ጊዜ ከተከታተልኩህ በኋላ ነበር ልረዳህ እንደሚገባ ያመንኩት። አሁን አጉል ታሪክ አንስቼ በማውራት ጊዜያችንን አልገድልም። ምክንያቱም እዚህ በምናባክናት ደቂቃ ውስጥ እንኳ ብዙ ሰቆቃ ላይ ያሉ ዜጎቻችን ስላሉ። ስለዚህ ስለ እኔ ሙሉ ነገር ባይሆንም ግርታህን ለማንሳት ያህል የተወሰነ ልንገርህ ፕሮፌሰር እስጢፋኖስ የኋላሸት እባላለሁ። ለበርካታ አመታት በራሺያ ዜኒትስ በርግ በምርምር ስራዎች ስሳተፍ እና ስሰራ የነበርኩ ሰው ነኝ። አንተን አለቃዬ እየፈለገህ ነው ብሎ ወደ እኔ ያመጣህ ልጄ ነው። የመጀመሪያ ድግሪውን በሞስኮ ቶሎስቶይ ዩኒቨርሲቲ በኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ የተመረቀ ሲሆን ሁለተኛ ዲግሪውን ደግሞ እዛው በሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ሰርቷል። ለብዙ አመታት ኑሯችንን እዛው ብናደርግም ዳሩ አይናችንም ልባችንም እዚች ታሪካዊት ሀገር ነበር። እዛው ሀገር እያለሁ ነበር ይሄን አካባቢ በህጋዊ መንገድ አስፈላጊውን ካሳ ለባሎቦታዎቹ ሰዎች ከፍዬ የገዛሁት። ከዛም ቀጥታ ወደዚህ የህንፃ ግንባታ ገባሁ።መንግሥት ይሄን ልዩ የሆነ ምስጢራዊ የሆነ ድብቅ ቦታ እንዳያየው በከፍተኛ ጥንቃቄና በራሺያ መንግስት ድጋፍ ልሰራ ቻልኩ። ያው መቼም ስለ ራሺያ ብዙ ነገር ታውቃለህ።ኢንስፔክተር እንደመሆንህ የቀድሞዋን ሶብዬት ሕብረት ታሪካዊና ፖለቲካዊ ዳራ ሳትጎረጉር አትቀርም። እናም የአሜሪካን ፍላጎት ብቻ የሚያንፀባርቀውን አሻንጉሊት የኢትዮጵያን መንግስት ለማስወገድ ያለን አማራጭ በረጅም አመት እቅድ በዚህ መልኩ መደራጀትና ቀስ በቀስ ማስወገድ ነበር። የምዕራቡ ዓለም እና የአሜሪካ አካሄድ ህገወጥ ወረራና ዘመናዊ የባርነት ቀንበር ያነገበ ፍልስምና በተመለከትኩና ባየሁ ጊዜ ይቺን መልዕክተ ዮሐንስ ብዬ የእወቀት አድማሴን ያሰፋሁባትን የፊደልን ቅጠል የዘነጠፍኩባትን፣ የአእዋፋትን ዝማሬ እየሰማሁ የንጋትን ደዎል ባወጀኩባት ሀገር ሌሎች ላይ የሆነው እንዲሆን ባለመፍቀድ አንድ ታላቅ ራዕይ በማንገብ ሀገሬን ከነዚህ ሰይጣኖች መታደግ ሆነ። ለዚህ ዓላማዬም ይረዱኝ ዘንድ በርካታ ተማሪዎችን ከየትምህርት ቤቱ በመልቀም ላለፉት አስር አመት በራሺያ በማሰልጠን የዚህ ምስጢራዊ ተልዕኮ ቡድን አባል አድርጌ በተንኳቸው። በየህዝቡ ላይ ተሰግስገው አስፈላጊውን መረጃ እንዲሰበስቡ በማድረግ ስራዬን በጥንቃቄ እየቀጠልኩ ለልጆቹ እንደ ወጣት ጎልማሳ ጎደኛም እንደ የእውቀት አባትም በመሆን ስራችንን እየሰራን ባለንበት አንድ ምስጢራዊ ቡድን ደግሞ በሌላ ፅንፍ እየተንቀሳቀሰ እንደሆን ተረዳሁ። በዚህም በቂ ክትትል በማድረግ መረጃዎችን በመሰብሰብ አንድ አብሯቸው ይሰራ የነበረን ልጅ በተለያዩ አባላቶቻችን በሰው በሰው በማድረግ አስፈላጊውን ምርመራ ስናደርግበት ልጁም ስራቸውን ለማገለጥ እንደሚፈልግና ነገር ግን ይሄን ምስጢር ቢያወጣ እጣፈንታው ሞት እንደሆነ በፍርሃቴ ውስጥ ሆኖ አጫወተን። ከዛ ምስጢራዊው ቡድንም እኛ እንድናርፍባት የምንፈልግባትን ኢትዮጵያ ትርጉም ያዘለ "ናፊባ"የተሰኘች የምስጢራዊ ተልዕኳቸውን ማስፈፀሚያና መከተያ ህግ ያዘለች።አጠቃላይ ስለቡድኑ ምንነትም በሚገባ የምትገልፅ መፅሐፍ እንደሆነች ከልጁ በወሰድነው መረጃ መሠረት አንዳንድ መረጃዎችን ስናሰባስብና በዚህ ቡድን ላይ መንግስት የራሱን ፍላጎት ለማሟላት እና ህዝቡን ለማስፈራራት የሚጠቀምበት የአሸባሪ ቡድን እንደሰራ በመገመት ማጣሪያዎችን ስናደርግ።ይህን ቡድን መንግስትም እንደማያውቀው ተረዳን። ከዛም ባለስልጣናቶች ይኖሩበት ይሆናል በሚል ፍርሃት መረጃውን ለማንም እግዳይደርስ ካደረግን በኋላ ስለ አንተ በጎ ስራና ጥሩ ስነምግባር ስናውቅ በህዝቡም መልካም የሆነ ቅቡልነት በመማረካችን እኛስ ከህዝቡ ወገን አይደለን በማለት አንተን መርዳት ዋናኛ ተግባራችን አደረግን። ይህን ስራችንንም የአንተን የምርመራ ጥበብ ለመጨመር ብዙም በማይከብዱ እንቆቅልሾች እያደረግን እስከዚህ አደረስንህ። ነገር ግን በተደጋጋሚ በአንተ ስሜታዊነት የተነሳ ከመንግስት ሀላፊዎች ጋር ቅሬታ እየገባህ ስትሄድ ሁኔታህ አሳስቦን ቀድመን ልንሰውርህ እያሰብን ባለበት መንግስት ቀደመን።ከዛ በኋላ የሆነው ይሄው ነው። ከምንም በላይ የአንተና የልጆችህ የሁላችሁም ሕይወት በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኑ ነው።" አለና ንግግሩን ገታ አድርጎ ነጭና ጥቁር የተቀላቀሉበትን ፂሙን ይነካካ ጀመር። ቀልጣፋና ንቁ የሆነ ሰው መሆኑን እየተመለከ ለረጅም ደቂቃ ሲያዳምጠው ከቆየ በኋላ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው " በጣም የሚገርም ነው ፕሮፌሰር።በቅድሚያ ከእኔ በላይ የተከበረ ሙያዎን ትተው ለትውልድ ሀገረዎ በማሰብ ያደረጉትን ነገር በሙሉ አደንቃለሁ። አከብራለሁ። ለዚህ ውለታችሁም ታሪክ የሚዘክራችሁ ይሆናል። በዚህ ደረጃ በመደራጀታችሁም በጣም ነው የተገረምኩት። ይህ የሚያሳየው ድንበር አልባ ሀገር እንዳለችን ነው። የእናንተስ ለመልካም ነገር የተቋቋመ ምስጢራዊ ቡድን ነው። ለሌላ ችግር የተቋቋመ ምስጢራዊ ቡድን በዚህ መልኩ ስለመደራጀቱም ጥርጥር የለኝም።ምክንያቱም የሀገሪቱ ደህንነት ምን ያህል የዘቀጠ እንደሆነ ያሳያል"በማለት በቁጭትና በንዴት አንገቱን አወዛወዘ። "አሁን እሱን ማሰቡ በእሱ መነመደዱ እርባቢስ ነው። የሚጠቅመው ቀጣይዋ ኢትዮጵያን በደህንነቱም በጥበቃውም ረቂቅ ንስር ካሜራዎቿን በመግጠም መቆጣጠር የምንችልበትን ስራ መስራት ነው። ስለዚህ አንተ አሁን የምትሰራው ስራ የናፊባ ምስጢራዊ ቡድን ማንነት እንድታጣራ እንድትመረምር ነው። በመቀጠል የደህንነት ስጋት ያለባቸው ዘመዶች በቅርበት ካሉህ እንድናመጣቸው ነው።"አለ ፕሮፌሰር ቆፍጠን በማለት። "ማንም የለም። ባለቤቴ ግን ስለ እኔ የሆነ ዜና ከሰማች በቀጥታ ልምጣ ማለቷ አይቀርም" አለ ሸዋንግዛው። ፕሮፌሰሩ በድንጋጤ በርገግ ብሎ "የት ነው የምትኖረው?" " አሜሪካ" ሸዋንግዛው በፍጥነት መልሶ የፕሮፌሰሩን የፊት ገፅ ተመለከተ። " ምንም ችግር የለም። ዜናው ሁሉም ጋር ስለተዳረሰ ባለቤትህ እዛ መሆኑን በፍፁም ረስቼዋለሁ። እሺ አሁኑኑ እንደውልላታለን "አለና ስልኳን ተቀብሎ ፊት ለፊቱ ባለው ስክሪን ተች ላይ ፅፎ ደወለላት። በተደጋጋሚ ቢሞክሩም አልነሳ አላቸው። "በቃ እንደታፈንኩ ከሰማች መንገድ ትጀምራለች ። ከዚህ በላይም ብቻ ባለቤቴ በጣም ነው የምትጨነቀው " አለ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው፣ ፕሮፌሰሩ መደወሉን አላቆመም......

@amba88
@amba88