Get Mystery Box with random crypto!

የዮቶር ልጅ - አምባዬ ጌታነህ

የቴሌግራም ቻናል አርማ amba88 — የዮቶር ልጅ - አምባዬ ጌታነህ
የቴሌግራም ቻናል አርማ amba88 — የዮቶር ልጅ - አምባዬ ጌታነህ
የሰርጥ አድራሻ: @amba88
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.75K
የሰርጥ መግለጫ

እኛ ከዮቶር፦
☞ የጥበብ ምሳሌን
☞ የአስተሳሰብ ውጤትን
☞ የፍልስፍና ዳራን
☞የአመራር ብቃትን
☞የአኗኗር ዘይቤን
ተምረናል!!!
ስለዚህ ሁላችንም የዮቶር ልጆች ነን ማለት ነው።
ለአስተያየት ና ሀሳብ via creater
@Adwa1888 [አምባዬ ጌታነህ]
YouTube
https://youtube.com/channel/UCTQKMrpvRybbd9C552bMVQQ

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-27 21:00:05 "ናፊባ"
ክፍል ~ ዘጠና ~
በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888
"ይሄን ሁሉ ድራማ የፃፉት ግን እነማን ናቸው?"ስትል ራሷን ብትጠይቅም ዳሩ ግን ለእሷ ትልቅ እፎይታን ፈጥሮላታል።ከሁሉም ነገር ገሸሽ ያደረጋት በመሆኑ ትልቅ ደስታን አጎናፅፏታል። ያለውን ነገር ለማጣራት ለወንድሟ በተደጋጋሚ ብትደውልለትም ስልክ ሊያነሳላት ባለመቻሉ በፈገግታ ውስጥ ሆና "ምነው አንተ እንደዚህ ጠፋህ የመጨረሻሽ ነው ተደርሶብሻል ምናምን እያልክ ስታቅራራ አልነበረም እንዴ ምነው ዝም አልክ?"የሚል ስላቅ የበዛበት መልዕክት ብትልክለትም አንድም ምላሽ ባለማግኘቷ የሆነ ሀሳብ ነገር ገብቷታል። ምን አልባት ተንኮል እየሸረበ ይሆን? ወይንም እዚህ ሁሉ ግብግብ እጁ ይኖርበት ይሆን? አዎ ሊኖርበት ይችላል።ያው የኢንስፔክተሩ ደጋፊ አይደል። እኔ ላስገድለው እንደሆነ ገብቶታል ማለት ነው!።ነገር ግን ያልገባኝ የመንግስት ሀይሎች ለምን ባልተጠበቀ መንገድ እንደዛ ሊጠብቁት በድንገት ፈለጉ? ትንሽ ጥያቄ የሚያጭረው እሱ ነው!" አለችና ስልኳን አንስታ ለአንድ ታማኝ የመረጃ ምንጯ ደውላ ስትጠይቅ ሁሉንም ነገር አጫወታት።ራሷን በፈገግታ እየነቀነቀች "በቃ አንድ አረም ነቀልኩ።ከዚህ በኋላ መንግስት ለራሱ ሲል ይከታተለዋል።እናም ወደተቀዛቀዘው ስራዬ ሙሉ ለሙሉ በመዞር አቅሜን ና ሀብቴን በመጠቀም ያለምንም ሰቀቀን መስራት እችላለሁ" በማለት ተንጠራራችና ስልኳን ከፍታ ስትመለከት ሶሻል ሚዲያው በሸዋንግዛው ፎቶ ተጥለቅልቋል። የተፃፈውን የመንግስትን አፈናም ስትመለከት ድንግጥ አለች።በፍፁም መንግስት ራሱ ያስረዋል የሚል ግምት አልነበረባትም። ሁሉም ሰው በስአት በሚባል ደረጃ አጥለቅልቆታል።
**********
"በጣም የሚገርም ነው። ሶሻል ሚዲያ ለካ መሳሪያ ያልታጠቀ ወታደር የሚኖርበት ቦታ ነው። በዚህ ስአት ብቻ ከሁለትመቶ ሺህ ሰው በላይ ተደራሽ ሆኗል። ኢንስፔክተሩን ፕሮፋይል በማድረግ ከወዲሁ "እኔ ከሸዋንግዛው ጎን ነኝ!" የሚል ሀሽታግ እየተጠቀሙ ከጠበቅነው በላይ ነገሩን አግለውታል። በራሪ ወረቀቱም በሚገባ ነው ስራውን የሰራው።አሁን ህዝቡ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ የደረሰ ይመስላል። ወትሮም ይሄን መንግስት የታገሱት በኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ከመጠን ያለፈ እምነት ስላላቸው ነው እንጅ መንግስቱ ቋቅ ብሏቸዋል።" "በጣም አሪፍ ታዲያ እኛስ የምንፈልገው ይሄን ስርአት መቀየር አይደል?!"አለና በፈገግታ። " አየህ ወዳጄ ሀገር ዝም ብላ አትመራም በህዝብ ይሁንታና እሺታ እንጅ። ህዝብ የወደደው መሪ ምንም አይሆንም ከማንም እና ከምንም ነፃ ይሆናል። ሸዋንግዛውን ተመልከት ሀብቱ ስልጣኑና ገንዘቡ ሳይሆን ህዝቡ ነው። በህዝቡ ውስጥ ደግሞ ዝም ብሎ አይደለም የገባው። በቀላል ስራ ብቻ።ስራውን አክብሮ በሀቀኝነት ስለሰራ ነው። ለምሳሌ የቱርኩን ፕሬዚዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ብንመለከት መፈንቅለ መንግስት ሊካሄድበት ሲል እናቶች ናቸው ታንክ ስር ሆነው ነፍሳቸውን ሳይሰስቱ በመስጠት ነፍሱን ያዳኑት።ከአሜሪካ ባርነትም ህዝቡ ራሱ የሚፈልገውን መሪ በመጠበቅ አሁን ለደረሰችበት ደረጃ ደርሳለች። እኔም የምፈልገው ሀገሬን እንዲህ አይነት የህዝብ ልጅ የሆነ መሪ እንዲመራት ነው። የህዝቡን ደህንነት የሚጠብቅ ችግሩን በሚገባ ተረድቶ ለችግራቸው እውቅና ብቻ ሳይሆን መፍትሔ የሚለግስ መሪ እንዲኖር። የትግሌ ራዕይ ይሄ ነው። እናንተ ገና ልጆች ናችሁ ከእናንተ በታች ያሉት ደግሞ ይበልጥ ልጆች ናቸው። ሀሳባቸው የሰላም እና የምግብ እጦት መሆን የለበትም። ከማንም ጣልቃ ገብነት የተገለለች የማንም ቡችላ ነጭ እንደፈለገ ሀሳብ የማይሰጥባትን ሀገር መገንባት ነው።ለዚህም ነው ትልቅ ዋጋ የምከፍለው።"አለና ትከሻውን መታ መታ አድርጎት የምድሩን አሳንሱር ነክቶ ወደላይ ወደ አፓርትመንቱ የሚያስወጣውን ቁልፍ ተጫነ "ግን እስካሁን እኮ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛውን አልጎበኘኸውም" አለ "ገና ነው የምጎበኘው አሁን አይደለም ልጅ። ጊዜው ራሱ ሲደርስ እኔ እሄዳለሁ።አሁን ከራሱና ከልጆቹ ጋር ጊዜ እንዲያሳልፍ እንተወው።አሁን ከምንም በላይ የሚያስፈልገው እኔን ማወቅ ሳይሆን ልጆቹ ጋር ጊዜ ማሳለፉ ነው" በማለት ስቆ ወደ ላይ ይወጣ ጀመር።
********
መንግስት በሶሻል ሚዲያው በከፈተው አብዮት በጣም ደንግጧል።ሁሉም ነገር ሊቆጣጠረው ከሚችለው በላይ ሆኖበታል።ባሰበው መንገድ ሳይሆን ባልጠበቀበትና ጭራሽ ፈፅሞ ባልገመተው አካሄድ በመሄዱ ጭንቀት የወለደው መግለጫ በመንግሥት ኮምኒኬሽን ክፍል በኩል ተከታዩን መግለጫ ሰጠ።" የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ህዞቦች ከምንም እና ከማንም በላይ እናንተ ዜጎቻችን አምናችሁን በመረጣችሁን መሠረት ሀገራችንን እያገለገልነበት ባለበት በዚህ ጊዜ ለወራት የቀጠለው የግድያ ተግባር በመቀጠሉ ከምንም በላይ በሀዘን የተቀጣን ብንሆንም ነገር ግን አንዳንድ ግለሰቦች ደግሞ የእነዚህን አሸባሪ ሰዎች እኩይ ተግባር ለማስፈፀም የሚታትሩ እንዳሉ እናውቃለን።ወንጀለኞችንም ለፍትህ ለማቅረብ ተግተን እየሰራንበት ባለበት በዚህ አጣብቂኝ ወቅት አንዳንድ ሰዎች የመንግስትን አደረጃጀት ጥላሸት በመቀባትና ያለስም ስም በመስጠት ላይ ሲሆኑ ለዚህም ማሳያቸው በሬ ወለድ ትርክታቸው በመሆኑ ከሰሞኑም በእናንተው ልጅ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ጉዳይ የተለመደ ውሸታቸውን እና የፈጠራ ታሪካቸውን በዚህ በሶሻልሚዲያ እያስተጋቡ ይገኛሉ። የእኛ የጥበቃ ሀይሎች ከሰሞኑ የዋና ሳጅን አክሊሉ የሺህዋስ ሞት በኋላ በተፈጠረ ስጋት የኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ጉዳይም ስጋት ስለጣለን ከመንግስት ጋር በመነጋገር ልዩ ኮማንዶዎችን ለደህንነቱ በቤቱ አቅራቢያ ለጥበቃ ብናሰማራም ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች ተኩስ ተከፍቶ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛውንና መላ ቤተሰቡን ይዘው የተሰወሩ ሲሆን ለዚህ እኩይ ተግባራቸውም ራሳቸውን ከሳሽ አድርገው መንግስትን እየወቀሱ ይገኛሉ።ምንም እንኳ ህዝባችን ይህንን መረዳት አይችልም ብለን ባናስብም ውሸት ሲደጋገም እውነት ይሆናልና ከዚህ የድግግሞሽ የበሬወለድ ዜና ራሳችሁን በማራቅ የተለመደውን አብሮነታችሁንና ትብብራችሁን እንፈልጋለን። መንግስትም በአሁኑ ስአት ሙሉ ሀይሉን በማሰማራት ከየአካባቢው የፀጥታ ሀይሎች ጋር በመሆን ታጋቾቹን ኢንስፔክተር ሸዋንግዛውን ሁለት ልጆቹን እንዲሁም የወንድሙ ልጅ የሆነችውን ሲሐምንና ባለቤቷን ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ሲሆን ለዚህም የእናንተን የህዝባችንን እርዳታ እንጠይቃለን!" በማለት ለሁሉም የሀገሪቱ ሚዲያዎች መግለጫ ሰጡ። መግለጫውም በሬዲዮዎችና በቴሌቭዥኖች ተስተጋባ።

@amba88
@amba88
3.2K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-26 21:02:54 "ናፊባ"
ክፍል ~ ሠማንያ ዘጠኝ
በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888
"እኔ ምን አውቃለሁ ወንድሜ እኔ ራሱ ግራ ገብቶኝ የምናገረው ነገር ጠፍቶብኛል"አለ ሸዋንግዛው እጁን አፉ ላይ ጭኖ። "ይሄ ቦታ ግን ይስማዕከ ዴርቶጋዳ ላይ ያስቀመጠው ና የገለፀው የምድር ከተማ ጋር ይመሳሰላል።የምር እዛ ድርሰት ውስጥ በምናብ የገባሁ ያህል ነው የተሰማኝ"አለ ተሕሚድ ዴርቶጋዳ ላይ የተገለፀውን የዳጋ ቅዱስ እስጢፋኖስ ገዳም ምድራዊ ከተማ በምናቡ እያስታወሰ። "በጣም ነው የሚገርመው"ብሎ ንግግሩን ሳይጨርስ ከፊታቸው ሆኖ ሲመራቸው የነበረው ሰው "ደርሰናል" ብሎ ቦታ ሲለቅላቸው በሩ ለሁለት ተከፈተ። "አባዬ " ብሩክታዊትና ኤሌዘር እየተንደረደሩ እላዩ ላይ ተከመሩበት።ሸዋንግዛው ስሜቱን መቆጣጠር ተስኖት እያለቀሰ ሁለቱንም በየተራ አቅፎ ሳማቸው።ሲሐምም ተሕሚድ ላይ ተሳፍራ የደስታ እንባ ታለቅስ ያዘች። ሁላቸውም ጋር ዝብርቅርቅ ስሜት ውስጥ ሆነው ለረጅም ስአት ከተቃቀፉ በኋላ ተቀመጡ። ሸዋንግዛው ዙሪያ ገባውን ሲያማትር ይህ ቀረው የማይባል ቦታ ነው ያለው።ሁሉም የተሟላለት ክፍል ነው።ልጆቹን እያቀያየረ ከሳመ በኋላ እቅፍ አድርጓቸው ወደ ኋላ ተለጥጦ ተኛ። በልጆቹ እስትንፋስ የአለምን ሁለንተና ግርግር ለመርሳት አሸለበ። የሰላም አየር ወደ ውስጡ እያስገባ እንቅልፍ ወሰደው። ተሕሚድ የሸዋንግዛውን በቅፅበት እንቅልፍ መወሰድ እየተመለከተ በሀዘኔታ "ኡፍ ምን አለ ሁሉም ሰው እንደ አንተ በሀቀኝነት ለገባበት ስራ ቢፋለም!" አለና ወደ ሲሐም በመዞር "እንዴት ወደዚህ አመጧችሁ?"አለ ተሕሚድ "ተወው እሱን በጣም ነበር የፈራሁት።ነገር ግን ልጆቹ ፍፁም እኛ ሰላማዊ ሰዎች ነን።ለእናንተ ደህንነት ስንል ነው። ኢንስፔክተር ና ፍቅረኛሽም ይመጣሉ ብለው።እነ ኤሌዝን ደግሞ መጣወቻ ገዝተው ምናምን ነው ያመጡን። እኔማ እኔን አግተውኝ የነበሩት ሰዎች መልሰው የያዙኝ መስሎኝ ቀጣም ፈርቼ ነበር።ግን ከመጣን በኋላ በቃ ፍፁም ሰላማዊ ነበሩ።እንደመጣን ሌላ ክፍል አሳረፉን። ከዛ የተወሰነ እንቆዬን ወደዚህ አመጡን እና ምንም ሳንፈራ የምንፈልገውን እንድንጠይቅ ነገሩን" አለች። ተሕሚድም በረጅሙ እፎይ ብሎ ተነፈሰ።የነፃነት ትርጉሟ ብዙ ነው ለነፃነት የሚከፈል ዋጋ ትልቅ ቢሆንም ውጤቱ ግን እጅግ ከማርና ከወይን የጣፈጠ ነው። እንደወይን የጣፈጠ የነፃነት አለም ለመፍጠር ብዙዎች መከራ ደርሶባቸዋል ታስረዋል ተገርፈዋል።በመጨረሻ ግን በእነሱ ግርፋት ና ስቃይ ብዙዎች ያለ ሀሳብ እንዲተነፍሱና እንዲኖሩ ምክንያት ሆነዋል።
********
ብዛት ያለው ሀይል ወደ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው መኖሪያ ቤት ቢገባም በቤት ውስጥ ባለመገኘቱ ታላቅ ብስጭት በባለስልጣናት ላይ ታዬ። ንዴታቸውን ማስታገሻ ይሆናቸው ዘንድም የፖሊስ ኮሚሽነሩን ሀላፊን ጨምሮ ኮማንደር በርናባስ ይገዙን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራቸውን አሐዱ አሉ። ጉዳዩ እስከ ጠቅላይ ምኒስቴሩ ጋር በመሄዱ አንዳች ቁጣንና መከፋፈልን በመካከላቸው አስርፆል።ያሳሰባቸው ምን አይነት ሀይልና ቡድን ነው ኢንስፔክተር ሸዋንግዛውን በዛች ቅፅበት ያስመለጡት? እነማን ናቸው? የሚለው ከፍተኛ ጥያቄ ሆኗል። ለዚህም እልባት ለማግኘት አስቸኳይ ስብሰባ በየ ኃላፊነት መስክ ላይ የተቀመጡትን ትላልቅ ባለስልጣና ወደ ቤተመንግስት በስአታት ውስጥ አስቸኳይ ስብሰባ በመጥራት ጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጥበት በጠቅላይ ምኒስቴር ፅህፈት ቤት ተጠራ። የዋና ሳጅን አክሊሉ የሺህዋስ ሞት ርዕስ በነበረባት ከተማ ሌላ ትርምስ ስለመፈጠሩ የሚያሳይ ችግር እንደተስተዋለ በህዝቡ ላይም ለመረዳት ጊዜ አልፈጀባቸውም።ስለዚህ የህዝቡን ቀልብ ለመሳብ ወይም ሀሳቡን እንዳይሰበስብ ግራ የማጋባት ስራ መስራት እንዳለባቸው የውሸትና የማስተባበያ ሀሳብ መፍጠር እንዳለባቸው አምነዋል።
"አሁን የሚያሳስበው የባለፈው የሶሻል ሚዲያ አቢዮት እንዳይከፈት ነው። ኢንስፔክተር የሆነ ነገር ሆኗል ቢባል ማንም ዝም አይልም።የመንግስታችን ተስፋ ሰጪነት የታየው በእሱ ጠንካራ ስራ ነው። በሸዋንግዛው ትልቅ እምነት አላቸው።ስለዚህ ይሄ ነገር ህዝቡ ጋር ከመዳረሱ በፊት እኛ ቀድመን ሸዋንግዛው እንደታፈነና ህብረተሰቡ አስፈላጊውን እርዳታ እንዲያደርግ መጠየቅ እንዳለባቸው ሀሳብ ያነሳሉ። ሀሳቡ የሚደገፍ በመሆኑ አስቸኳይ ተሰብሳቢ ምኒስቴሮች ሀሳቡን አፅድቀው በፍጥነት ለሚዲያ አካላት መግለጫ መስጠት እንዳለባቸው ከተስማሙ በኋላ ቀጣዩ ደግሞ የሸዋንግዛው አጋቾችን ማወቅና መመርመር። ምክንያቱም እርሱን የፈለጉበት ስለ ፓርቲያችን በርካታ ምስጢሮችን ስለሚያውቅ እኛን ለማጥቃት በቀላሉ እንዲመቻቸው ነው።ስለዚህ ይህ ጉዳይም ጊዜ የሚያስፈልገው ባለመሆኑ ይህንንም በሚገባ ማጣራት ይኖርብናል"በሚል አቅጣጫ በሁለቱ ነጥቦች ላይ ድምፅ ሰጥተው ስብሰባው ተበተነ።
*******
"አሁን ሙሉለሙሉ በሚባል ደረጃ በሁሉም የከተማችን ቦታዎች ማለትም ሰዎች ይሰበሰቡበታል በሚባሉ ሁሉ ፍላየሮችን በትነናል። የአዲስ አበባ መንገዶች በእነዚህ ውብ እና ድንቅ ቢራቢሮ በመሰሉ ወረቀቶች ጎዳናዎቿ ሳይቀሩ አጊጠዋል።"አለ በፈገግታ "በጣም ጥሩ። አሁን ደግሞ የሚቀረው በሶሻል ሚዲያ የኢኔስፔክተር ሸዋንግዛውን መታገት የሚገልፅ መረጃ መውጣት አለበት። የመንግስትን ስራ ከስር ከስሩ የሚነቅፉትን አክቲቢስቶች ታግ አድርጋቸው መረጃውንም ቀድመህ ስጣቸው"አለ ወረቀቱን እየሰጠው "ሁሉንም ነገር እዚህ ላይ ፅፌዋለሁ። ይሄ ተለቆ በከተማዋ ላይ የተበተነው ፍላዬር ጋር ሲዳመር የምንፈልገውን ግብ ይመታልናል። "መንግስት የንፁሀንን ደም ባፈረሱ ሰዎች ላይ ፍትህ ያሰፍናል ወንጀለኞቹንም ለፍርድ ያቀርባል ብለን ስንጠብቅ ነገር ግን በደንታቢስነት ከነገ ዛሬ እያለ እዚህ ደረሰ። ሞቱ ከንፁሀን ዜጎች ባለፈ በታማኝ የህዝብ ልጆች በሆኑ ቅን መርማሪ ፖሊሶች ላይም የደረሰ ሲሆን ለዚህም ከኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ጎን በመሆን ገዳዮችን ለፍርድ ለማቅረብ በከፍተኛ ሀቀኝነት እየሰራ የነበረው ዋና ሳጅን አክሊሉ የሺህዋስም በግፍ መገደሉ የአገዛዙ አቅመቢስነትን የሚገልፅ ሲሆን ይህ አልበቃው ብሎ ደግሞ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ለምን የመንግስትን አካሄድ ትቃወማለህ በሚል አፈና ተፈፅሞበታል። ለዚህም በቤቱ ስራውን እየሰራ በነበረበት በርካታ ቁጥር ያለው የመንግስት ሀይል በመሄድ ከቤቱ አውነው ይዘውት እንደሄዱና እስካሁን የት እንዳደረጉት አይታወቅም። የህዝብን እምባ በማበስ ፋንታ የህዝብን አለኝታ የሆኑ ታማኝ ሰዎችን ማፈን ራሱ ለህዝቡ ያለውን ግዴለሽነት ያሳያልና ህዝቡ ይሄን አፀያፊ የመንግስትን ድርጊት በነቂስ ወጥቶ ሊያወግዝ ይገባል።"የሚል ፅሁፍ ነበር በወረቀት የሰጠው። ይሄን ሀሳብ የያዘ ፅሁፍን ነው ወደ ሶሻልሚዲያ በመለጠፍ የአቢዮት ሀሽታግ የሚጀመረው።ወረቀቷን ወስዶ በሚገባ በወርድ ከፃፈ በኋላ ወደ ስለሰኩ በመላክ ይታወቃሉ ወደሚባሉ የማህበረሰብ አንቂዎች በውስጥ መስመር ተላከላቸው።ከአንድ ፍላዬር ጋር በማድረግ ለሁሉም እንዲዳረስ አደረገ።

@amba88
@amba88
3.1K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 18:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-26 18:49:30 ተከታይዋ የቻናል ሊንክ የ"ምትኬ" አድራሻ ናት። ምትኬን በዚች ቻናል ታገኟታላችሁ። ዮቶራዊያን የምትኬ አፍቃሪዎች የማንንም ደጅ ሳትጠኑ በዚች አድራሻ ብቻ መጠበቅ ትችላላችሁ።
ምትክ አልባዋ ምትኬ!!!
@mastaweshaye
@mastaweshaye
@mastaweshaye
2.5K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 15:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-25 22:09:31 keep trying (ሙከራህን ቀጥል)

ምን እየሰራህ ነው? ምን እያደረክ ነው ቀንህን በምንድነው የምታሳልፈው? ለምትሰራው ስራስ ፍቅርና እምነት አለህ?
ካለ መስራትህን ቀጥል የሰዎችን ይሁንታ ለማግኘት ስትል ስራህን ከምትተው የሰዎችን አድናቆት ለማግኘት ስትል ስራ! ያኔ እነዛ ሰዎች ምልከታቸውና ተግሳፃቸው ልክ እንዳልነበር በማስተማር ወደ ሕይወት መንገዳቸው እኖዲራመዱ ምስንያት ትሆናለህና።
ስለዚህ በሙከራህ መክሸፍ ተበሳጭተህ ሙከራህን አታቋርጥ ዝም ብለህ ሙከራህን ቀጥል። ትሉ አንድ ጊዜ ብቻ ሞክሮ እንደወደቀ መሞከሩን ቢያቆም ኖሮ በስምንተኛው ሙከራ ዛፉን አይወጣም ነበር።

መልካም አዳር!!! @Adwa1888

@amba88
2.5K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 19:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-25 21:06:46 "ናፊባ"
ክፍል ~ ሠማንያ ሥምንት
በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888
"እነዚህን ሰነዶች በጥንቃቄ እንያዝና ለማምለጥ የተቻለንን እናድርግ!"አለ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው "አይ ኢንስፔክተር በዚህ ስዐትም ስለዚህ መረጃ ታስባለህ? መጀመሪያ የእኛ መኖርና አለመኖር በምን ተረጋገጠና"አለ ተሕሚድ በሸዋንግዛው ንግግር እንደመሳቅ እያለ " እዚህ ላይ አንድ ነገር ዘንገት ብለሀል። የሰው ልጅ የሚሞተው ተስፋ ማድረግ ሲያቆም ነው። ተስፋ ብቸኛ የሕይወታችን ማስቀጠያ መንገዳችን ነው። እኔ በዚህ ሁኔታ እንኳ ሆኜ የማስበው ስለቀጣይ እጣፈንታችን ነው። በሕይወት እስካለሁ ድረስ ፕላን ማድረጌን እቀጥላለሁ። ማድረግ ያለብኝን ነገር ሁሉ እያደረኩ እቀጥላለሁ። አንድ አባት አትክልት እየኮተኮቱ ድንገት የሞት መላዕክት ይመጡና "ለመሞት ሶስት ስአት ነው የቀረዎት ቢባሉ ምን ያደርጋሉ?" ብሎ ሲጠይቃቸው እሳቸውም ፈገግ ብለው "ኩትኮታዬን እቀጥላለሁ"አሉ ይባላል።እስከመጨረሻዋ የእንባ ጠብታ መዋደቅ ያስፈልጋል። በሕይወት እስካለሁ።የነዛን ምስኪን ዜጎች ገዳይ ለፍርድ ማቅረብና የወዳጅ ዘመዶቻቸውን እንባ ማበስ ቀዳሚው ስራዬ ሆኖ ይቀጥላል! ስለዚህ አንተም እንደዛ ሆነህ የተነሳህበትን አላማ ለማሳካት መጣር አለብህ። ለአላማህ አንተ እንጅ የምትሞተው አላማህ ለአንተ አይሞትም" አለና የሚያስፈልጉትን መረጃዎች መሰብሰቡን ቀጠለ። ተሕሚድ ሸዋንግዛው የተናገረው ሜታፎርና ታሪክ ውስጡ ላይ እንደ አለት ድንጋይ የተቀመጠ ይመስላል።አንዳንዶቻችን የሆነ ነገር ሲጋረጥብን ቢቀርስ ሌላ ነገር ብንፈጥርስ ብለን የምናቆመው ነገር አለ። የምንሰራው ስራና ራዕያችን ከተዛመደ እንቅፋቶች ይበዙብናል።ብዙ ጊዜ ሞቲቬሽናል ስፒከሮች ስለ ስኬት ሲያነሱ ቀዳሚ ምሳሌያቸው የሚሆነው ቶማስ ኤዲሰን ነው። ይህ ሰው እንግዲህ የአለማችንን ገፅታ በብርሃን አጎናፅፎ የራሱን ታሪክ የቀለበሰ ነው። ስለዚህ ሰው ስኬት ማውራቱ አይጠቅምም የሚጠቅመው ስኬት ላይ የደረሰበትን ስቃይ መከራና መገለልን በመማር የራስን ስኬት መስራት በመቻል ነው። ስልክ ያለቻርጅ አይሰራም ቻርጅ የሚደረገው ደግሞ ከመብራት በሚሰበሰብ ሀይል ነው። አጠቃላይ ግዙፍ የሚባሉ ፋብሪካዎች ምኖች በመብራት ላይ ጥገኞች ናቸው ማለት ነው። ቶማስ ኤዲሰን ሁሉም ደደብ ተማሪ ብለው አንቅረው የተፉት ነገር ግን እናቱ ያን አስተያየታቸውን ለልጇ በበጎ ነገር በመቀየር ለአሁኗ አለም ነፀብራቅን አብቅተዋል። አሁን ሀሳቤ የቶማስን የሕይወት ታሪክ መተንተን አይደለም።መብራትን ለመፍጠር አንድ ሺህ ጊዜ ተሳስቷል።ብዙዎችም ለምን አርፈህ አትቀመጥም።አይሆንም አይሳካም ይህ በአንተ አቅም የሚሆን አይደለም ብለውታል።ነገር ግን ቶማስ ሙከራውን አላቆመም።ሙከራህን ቀጠለ ምንም አይነት ተስፋ በማያሰጥበት ሁኔታ ላይ ብትሆንም የየዝከውን ነገር አትልቀቅ። ቃልኪዳን ትልቅ ማሰሪያ ገመድ ነው። ቶማስ ከአንድ ሺህ ሙከራዎቹ የተማረው ነገር ቢኖር መብራት የማይሰሩበትን መንገድ ነው። ስለዚህ በማንኛውም ቦታና ሁኔታ ሆነህ አላማህን ለማሳካት ጣር።
ከፍተኛ የሆነ የተኩስ ድምፅ ይሰማ ጀመር። "በቃ ተጀመረ ማለት ነው።"አለ ተሕሚድ "ግን ከማን ጋር ነው የሚታኮሱት? ከተማ ላይስ ተኩስ መክፈት አግባብ ነዎይ?ይሄ እኮ ትልቅ የጦር ወንጀል ነው! ሌሎች እኔን የሚፈልጉኝ ሰዎችም አሉ ማለት ነው?"በርካታ ጥያቄዎችን ለተሕሚድ እየጠየቀ ግራ መጋባቱን ቀጠለ። "ምንአልባት ኮማንደር በርናባስ ይሆን እንዴ? ለማለፍ ሞክሮ እምቢ ሲሉት ይሆን?"አለ ተሕሚድ"ምን አልባት ልክ ልትሆን ትችላለህ ግምትህ ልክ መሆንና አለመሆኑን ልደውልለትና ቸክ እናድርግ" ብሎ ወደ በርናባስ ስልክ ደወለ።
በርናባስ ምንም አይነት ሀይል ይዞ እንዳልመጣና እሱን ለማድረግ ታማኝ ሰዎችን እያፈላለኩ ነው በማለት መፅናኛ ቃላት ሰጥቶት ወሪያቸውን ጨረሱ። ተሕሚድ የገመተው ግምት ልክ ባለመሆኑ እንደማፈር እያለ "ታዲያ ማን ሊሆን ይችላል?" ይሄኔ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው አንድ ሀሳብ ወደ ምናቡ መጣለት። እንደተከበበ ለነገረው ሰው መደወል። "እየውልህ ማንነትህን አላውቅም።ከእኔ ምን እንደምትፈልግ አላውቅም።ለምን ያን ሁሉ ምስጢርም ስታስቀምጥልኝ እንደነበር አላውቅም። አሁንም ለምን እንደምትረዳኝ አላውቅም። ኢላማህ እኔ ልሁን አልሁንም አላውቅም።ግን አሁን ቢያንስ ልትጎዳኝ እንደማትፈልግ ተረድቻለሁ።ስለዚህ አንድ ነገር ብቻ ላስቸግርህ እኔ አንድ ነገር ብሆን ልጆቼን ለሚስቴ አደራ አስረክብልኝ። ይሄን ብቻ እንድትተባበረኝ ነው የምፈልገው!" አለ ሸዋንግዛው የመጨረሻ ንዝ በሚመስል አነጋገር "ኢንስፔክተር ምንም ችግር አይፈጠርም ተኩሱን የከፈቱት የእኔ ሰዎች ናቸው። ዋናው አላማችን አንተን ከመንግስት አፋኝነት ነፃ ማውጣት ነው። ስለዚህ አሁን እንደደረሰኝ መረጃ የበርህን አካባቢ የእኛ ሰዎች ተቆጣጥረውታል ስለዚህ ሌላ ሀይል ሳይመጣ በፍጥነት ከዛ አካባቢ እንድትወጡ ተዘጋጁ"አለ ሸዋንግዛውን ለረጅም ደቂቃ ካዳመጠው በኋላ። ኢንስፔክተር ሸዋንግዛውጰበሰውዬው አነጋገርና ፍፁም የሆነ እርጋታ እየተገረመ የሚለውን ከመተግበር ውጪ ሌላ አማራጭ እንደሌለው ተረድቷል።
*****
" ልጆች ናቸው። እንዳይፈሩ ጥንቃቄ አድርጉ። ሲሀምንም ያለውን እውነት በመናገር እሷንም ከስጋት ነፃ እንድታደርጓት እፈልጋለሁ።የተወሰኑ አባላቶቻችንን ወደ ስፍራው በመላክም በአፋጣኝ እነ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛውን ወደዚህ የማምጣት ስራ መሠራት አለበት ሌላውን ስራ በሙሉ ተውትና አሁን ትኩረታችን ወደዚህ ነው መሆን ያለበት።የሸዋንግዛው መኖር ለእኛ በጣም አስፈላጊ ነው ጠቃሚ ነው። አብዝሀኛውን ስራችንን የሚሰራልን እሱ መሆኑን እንዳትረሱ"በማለት ኮስተር ብሎ አዘዘ። ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ለተሕሚድ ሙሉ ሽፋን በመስጠት የተወሰኑ ለምርመራ ይጠቅሙኛል ያላቸውን መረጃዎችና ላፕቶፕ ይዞ በመውጣት በተነገረው መሠረት በሩን ሲከፍት በርካታ ሲቢል ሰዎች ቆመዋል። ከዛ በቅርብ እርቀት ደግሞ የተኩስ ድምፅ ይሰማል።አካባቢው ሰላሙ ተረብሿል።በፍጥነት መሀል ላይ አስቀምጠዋቸው ይዘዋቸው ከአካባቢው ተሰወሩ። ሸዋንግዘው ወደየት እንደሚሄድም ማን እንደሚወስደውም ሳያውቅ ያለምንም ተቃርኖ ታግቶ ይሄድ ጀመር። በመጨረሻ በአንድ ቅንጡ ቪላ ቤት ውስጥ ገብተው የቤቱ ወለል ላይ የተነጠፈውን አረኔጓዴ ስጋጃ በመክፈት ጥቂት ቁጥሮችን በመጫን በሩ ተንሸራተተ። ጥቁር ሲሊንደር የሚመስል የሚያብረቀርቅ ነገር ላይ ሶስታቸው ከቆሙ በኋላ እነሱ ጋር ያልቆመው ልጅ ከቆሙባት አጠገብ የሆነች የአረንጓዴ በትን ሲጫን በእርጋት ይዟቸው ወደታች ይሰምጥ ጀመር።ኢንስፔክተር ሸዋንግዛውና ተሕሚድ እርሰበእርስ ተያዩ። ወደታች በወረዱ ቁጥር በጨለማ የተዋጠው ክፍላቸው በብርሃን እየተተካ በግምት ወደሶስት ደቂቃ የሚሆን ጉዞ ከጨረሱ በኋላ የቆሙበት ሊፍት ደወል ሲያሰማ በፍጥነት እግራቸውን እንዲያወርዱ ካሳወቃቸው በኋላ ቀጥታ ተከተሉኝ በማለት ወደ አንድ ክፍል ይዟቸው ይሄድ ጀመር። ግራ ቀኝ ያሉት መብራቶች የምድሩን አለም የሰማይ ከዋክብት አስመስለው በብርሃን አንቆጥቁጠውታል። "ምንድን ነው የማየው? አለ ተሕሚድ።

@amba88
@amba88
2.5K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-24 20:54:50 "ናፊባ"
ክፍል ~ ሠማንያ ሠባት
በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888
"መኖር የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ድርሻው ብቻም ሳይሆን
ኃሴት እንዲያገኝ የሚያደርገው እጣ ፈንታው ነው።
ረሀብና በሽታ ብቻ ሰውን አይገለውም።
ቤት የሌላቸው በርካታ ሰዎች ቢኖሩም አንተ ግን....."
የምትል ቆፍጣና ሀሳብ ከያዘች የአራት መስመር ሀሳብ ጋር ተሰናኝቶ ልቡን በአንዳች ስሜት እየነጠቀ ይረብሸው ጀመር።ደጋግሞ አነበበው ነገር ግን ወደውስጡ ሊነግረው የሚችል ተዛማጅ ትርጉም አጣ። የሚተነተኑ ሳይሆን የሚያጠራጥሩም ሳይሆን የሚታመኑ፣ የሚያሻሙ ሳይሆን ግልፅ የሆኑ ሀሳቦች የተቀመጡበት ነው።" መኖር የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ድርሻው ብቻም ሳይሆን ኃሴት እንዲያገኝ የሚያደርገው እጣፈንታው ነው።ይሄ ምን ማለት ነው? ምን አይነት ሀሳብ ነው። ትንሽ እንኳ የሚያሻማ ቢሆን ችግር የለውም ነበር ነገር ግን ምን የሚሉት አገላለፅ ነው? አለ ሸዋንግዛው ምሬት ና ስልቹነት ፊቱ ላይ በሚገባ እየተቀየረ።ተሕሚድ የሸዋንግዛውን ሁኔታ በትዕግሥት እየተመለከተ "ይቅርታና በድጋሚ አሁንም ጥሩ ስሜት ላይ ስላልሆንክ ምንም ልትረዳው አትችልም በቅድሚያ አእምሮህን ነፃ ማድረግ ይጠበቅብሀል!"የሚል ምክረ ሀሳብ ለመጨረሻ ጊዜ አቀረበለት።
**********
"የሸዋንግዛው መኖሪያ ቤት ብረት በለበሱ ሰዎች ተከቧል።አሁን ላይ ባለን መረጃ እርሱና ተሕሚድ በመኖሪያ ቤት ውስጥ እንዳሉ ናቸው። የእኛ ሀይሎች ከመንግስት ሀይል ጋር ሲነፃፀር ምንም ነው። ስለዚህ ሌላ መንገድ ስለሌለ አባላቶቻችንን እንዲመለሱ አዘዝኳቸው" አለ በሀፍረት አንገቱን እያቀረቀረ። "እና እንደ ጀብድ አድርገህ ታወራኛለህ።ብቻውን እንዲጋፈጥ አድርገነዋል ማለት እኮ ነው።የሆነ ነገር እንዲያደርጉ እንኳ ማዘዝ ነበረብህ!" "ለምሳሌ ምን ማድረግ ነበረብኝ? እኔ እኮ አንተን ሳላማክርህ ብዬ ነው።ያው ባለማወቅ ስህተት እንዳልፈፅም ብዬ ነው እንጅ። እዛው አካባቢ ሆነው ኢንስፔክተርን የከበቡትን የመንግስት ቅልብ ምልምሎች ላይ ከእርቀት የተኩስ ድምፅ በማሰማት አካባቢው ላይ አንዳች ነገር እንደተፈጠረ ማመላከትና ለማንቃት አስቤ ነበር። ግን በዚህ ጊዜ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ያለምንም ማስጠንቀቂያ ወይ መሳሪያ ይዞ ሊወጣ ይችላል። ወይም ደግሞ ለፖሊስ መኮንኖቹ ደውሎ በገዛ ፈቃዱ ቀለበት ውስጥ ሊገባ ይችላል ብዬ ስላሰብኩ ነው!" በማለት ጥርጣሬዎቹን በሙሉ አንድ በአንድ ዝርግፍ አድርጎ ተናገረ።"በርግጥ ቸኩለህ ውሳኔ አለመወሰንህ ጥሩ ነው። በል ለማንኛውም ለልጆቹ ደውልና በቅርብ እርቀት ሆነው ምን ያህል ፖሊስ እንደከበበው በቁጥር ደረጃ እንዲያጣሩ አድርግ። እኔ ደግሞ ለኢንስፔክተር ሸዋንግዛው በመደወል ያለውን ነገር አሳውቄው ቅድሚያ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ላድርገው።
"ሀሎ ጤና ይስጥልኝ" "አብሮ ይስጥልኝ ማን ልበል?" አለ ሸዋንግዛው "ይቅርታ ማንነቴን እንኳ አታውቀውም ግን አንድ መረጃ ልነግርህ ነው። ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው በአሁኑ ስአት ቤትህ ከመንግስት በተሰጣቸው አንተን የማፈን ልዩ ኦፕሬሽን ከበባ ውስጥ ነህ! ምን አልባት ይሄን ስልህ ልትገረም ትችላለህ። ወይም ደግሞ እኔን ላታምነኝ ትችላለህ። ግን በእርጋታ ቀስ ብለህ በመውጣት መመልከት ትችላለህ! ለጊዜው እኛ እንረዳሀለን። ነገር ግን በተዘዋዋሪ እንጅ በቀጥታ አይደለም። ልጆችህንና የወንድምህን ልጅ በአስተማማኝ ቦታ እናስቀምጣቸዋለን።ይሄን የምናደርገው እንደነገርኩህ አንተን ለመርዳት እንጅ ለማስፈራራት አይደለም።እርግጠኛ እንድትሆን ያህል ራሴን ደብቄ የምስጢር ጥቅሎችን የማስቀምጥልህ ሰው ነኝ። ካንተ ጎን የምሆንበት ምክንያት እንጅ ከአንተ ተቃራኒ የምሆንበት ምክንያት እንደሌለኝ በመረዳት ሙሉ ትኩረትህን ከዚህ ከበባ ራስህንና ተሕሚድን የምታወጣበትን ሀሳብ አፍልቅ" ብሎት ስልኩን ጆሮው ላይ ዘጋው። ኢንስፔክተር ሸዋግግዛውጰየሰው ልጅ የመጨረሻ ደረጃ የሚባለውን ግራ መጋባትን በቅፅበት አስተናገደ። ሁሉም የሰማው ነገር እንግዳ ሆነበተ። ለአመታት በታማኝነት ሲያገለግለበት የነበረው ስራው ተጠያቂ እንዳደረገው ለማመን ተቸገረ። ለብዙ ጊዜ ወደስልጣኑ እንዲመለስ ግፊት ሲያደርግለት የነበረው መንግስት አሁን የሱ ጠላት መሆኑን ከማያውቀው ሰው እየሰማ ነው። "ምንድነው ያለህ ኢንስፔክተር"ተሕሚድ የተለመደውን ጥያቄ ሰነዘረ። ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ዝም።ምንም አይነት መልስ ሳይመልስለት ዝም ካለ በኋላ ብድግ አለና ቀስ አድርጎ በሩን ከፍቶ ወደ ግቢው በር አጮልቆ ያማትር ጀመር። ጊቢው ፀጥረጭ ብሏል። በእርጋታ ወደ ዋናው በር ጠጋ ብሎ በቀዳዳ ሲመለከት በርካታ ልዩ ፖሊሶች መሳሪያቸውን በተጠንቀቅ ይዘው ፊታቸውን ወደ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ቤት መግቢያ በር ተኮልኩለዋል። ይሄኔ ነበር የሰማው ነገር እውን መሆኑን ያረጋገጠው።በፍጥነት ወደ ቤቱ ተመልሶ ገባና አንዳች መውጫ ዘዴ ያስብ ጀመር። ለረጅም ደቂቃ ካሰበ በኋላ ለስራ ባልደረባው ለሆነ አንደ የወንጀል ምርመራ ቡድን አባል ለሆነው ወዳጁ ለኮማንደር በርናባስ ይገዙ ደወለለት። በእርጋታና በዝግታ እያንሾካሾከ " እየውልህ በርና ቀስ ብለህ አናግረኝ።እኔ መሆኔን ለማንም እንዳትናገር ዝም ብለህ የምልህን አድምጠኝ በዚህ ስአት ከአንተ ውጪ ማንንም ላምን አልችልም። ተከብቢያለሁ። የቻልከውን ነገር አድርግ ግን ለማንም ሰው እንዳትናገር። ከቻልክ የተወሰኑ የእኛን ሀይሎች ይዘህ መጥተህ የሆነ አቅጣጫ ለማስቀየር እና ሀሳባቸውን ለመስረቅ ሞክር።"የሚል ሀሳብም ተማፅዕኖም የበዛበት የቃላት ድርድር እንደ በረዶ አወረደበት።
"ኧረ እባክህ ኢንስፔክተር የተፈጠረውን ነገር ንገረኝ በጭንቀት ገደልከኝኮ"አለ ተሕሚድ የሚጠይቀው ጥያቄ ምላሽ ሲያጣና ጭንቀቱ እየበረታ ሲሄድ "አሁን ምንም ልልህ አልችልም።ተከበናል።" "ምን?" አለ ተሕሚድ ሳያስበው ጮክ ብሎ "በቃ በጠዋቱ ድርጊቴ የተቆጡት ባለስልጣናት እኔ እንድታፈን ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።" "እና አሁን ምንድነው የምናደርገው?" ተሕሚድ ራሱን በሁለት እጁ እንደያዘ ጥያቄውን ሰነዘረ። "ምን እናደርጋለን ብለህ ነው። ነፃ የሚያወጣንን ፈጣሪ መለማመን ነዋ! ውጪ ላይ በተጠንቀቅ ቆመዋል። እስኪ ከሴራው ላይ ካልተካፈለ ጓደኛዬን ማለቴ የስራ ባሌደረባዬን የሆነች ትንሽ የማርያም መንገድ እንዲከፍትልን ጠይቄዋለሁ። ግን አማራጭ ስለሌለኝ ነው እንጅ ትክክለኛ ሰው አይደለም የጠየኩት"አለ ሸዋንግዛው በኮማንደር በርናባስ ይገዙ እምነት እንደሌለው ለተሕሚድም በሚገባ እያስረገጠለት።ተሕሚድ ምን ማድረግ እንዳለበት ይቅርና ምን ማሰብ እኖዳለበት ሁሉ ጠፋው። አንዳች ምስጢር ለማግኘት ከማነፍነፍ በመውጣት የራሳቸውን ነፍስ ስለማትረፍ ይጨነቁ ጀመር። ሕይወት ልክ እንደዚህ ገጠመኝ ነች። ብዙዎች በብዙ ነገር ይመስሏታል። ግን ከምንም በላይ በተላያዩ ድራማቲክ በሆኑ ገፅታዎች የተላበሰት ሰርክ አዲስ ትዕይንት ነች።

@amba88
@amba88
2.6K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 19:44:46 "ናፊባ"
ክፍል ~ ሠማንያ ስድስት
በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888
ይቅርታ እኔ በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኜ ስብሰባውን መቀጠል አልችልም!" ብሎ ከመቀመጫው ተነስቶ ወጣ። ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ከመጠን በላይ እንደተናደደ ፊቱ ላይ በሚገባ ይታያል።በቃላት አልባ ጉርምርምታ ድርጊቱን የደገፉ የስብሰባው ተሳታፊዎች ቢኖሩም ከተለመደው የውስጥ ተቃውሞ ውጪ ማናቸውም ደፍረው ኢንስፔክተሩን ተከትለው የወጡ አልነበሩም። ከራሳቸው ጋር እየተሟገቱ ከራሳቸው ጋር እየተጣሉ የተቀመጡ በርካታ የስራ መኮንኖች ተቀምጠዋል። በባልስልጣናቱ ዐይን ላይ የሚያንዣብበው የቁጣ ደመና ከንሀሴ ሰማይ ይልቃል። ከብዙ የእርስ በእርስ መተያየት በኋላ "ይህን ስብሰባ መታደም የማትፈልጉ ካላችሁ የእኛን ይሁንታ ሳትጠብቁ መውጣት ትችላላችሁ!" አለ አንድ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን ሚኒስቴር በዚህን ጊዜ አንዱ እጁን አወጣና የመናገር እድል ከተሰጠው በኋላ " ስብሰባው አንዳች አቅጣጫ አያስቀምጥም። ለውጥም አምጥቶ አያውቅም። እኔ እስከማውቀው ድረስ ምንም አይነት እርምጃ አልወሰድንም።ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ያለው ልክ ነው። በዚህ ጉዳይ ህዝቡ በመንግስት ላይ ያለው አመኔታ ወርዷል። በመንግሥት ምንም አይነት እምነት የለውም። ቀን በቀን የሞት ዜና እየሰማ ተላምዶት ተስፋ ቆርጧል።ከምንም በላይ ደግሞ የሞት ሞት የሚሆነው ህዝብ በመንግስት ላይ እምነት ሲያጣ ነው።ስለዚህ እኔም ከይቅርታ ጋር ብወጣ ደስ ይለኛል!"አለና ወጣ። በቀሪው ተሰብሳቢ ላይ ድንጋጤንም ጥርጣሬም እየጫረ እየሄደ መሆኑን ሲያውቁ ሰብሳቢዎቹ ጎን ለጎን ተነጋገሩና ስብሰባውን ያለ አስተያየት ጀመሩ።
*************
"አሁን ጊዜው ደርሷል።ይቺን ወቅት ከመቼውም ጊዜ በላይ ነበር የምጠብቃት። አንዳንድ ነገሮች እንደገበሬው ወቅት እየተጠበቀ የሚሰሩ ስራዎች አሉ።ያለወቅት የሚዘራ እህልና ያለወቅቱ የሚፈነዳ አብዮት ግቡን አይመታም። ሁሉም ነገር በጊዜው ሲሆን መልካም ነውና አሁን የኛ ጊዜ ነው። ሜዳው ላይ እንዳሻችን የምንጫወትበት ጎል የምናስቆጥርበት ስአት። ሁሉም ሰው የእኛ ደጋፊ ይሆናል። የመንግስትን ስራዎች በሙሉ እናጋልጣለን። እጃችን ላይ ያሉ መረጃዎችን ለህዝብ እናደርሳለን።ስለዚህ ሁላችሁም ከዛሬ ጀምሮ የበረራ ወረቀት በማዘጋጀት በመላው አዲስአበባ ይበተን!!"የሚል መልዕክት አስተላለፈ። በጭብጨባ መልዕክቱን ተቀበሉ።ሁላቸውም ፊት ላይ የቁርጠኝነት መንፈስ ተሞልቷል። መተሳሰብ መደማመጥ መከባበር የተሞላበት ስነ ምግባራቸው ። እያንዳንዳቸው ስለተነገራቸው እና ለተሰጣቸው ዓላማ በቁርጠኝነት እስከመጨረሻው ለመዋደቅ ፅኑ የሆነ ፍላጎት ማሳየታቸው የሚገርም ነው። አብዝሀኛው ሰው አለማው የማይሳካው ወይ ለአላማው ቁርጠኛ አይደለም ወይም አላማው እንደሚሳካ የማያምን ነው። የብዙዎችን ሰዎች የሕይወት ዘመን ግብ ብንመለከት በተለይ ያሳኳቸውን የስኬት ማማዎች ብንመለከት።ለነዛ ስኬቶች ብዙ ዋጋ ከፍለዋል። ብዙዎች ደግሞ ግብ ላይ ስኬት ላይ መድረስን ይመኛሉ። ነገር ግን ለዛ ስኬት የሚያስፈልጉ መስዕዋዕቶችን መክፈል ደግሞ ተራራን የመግፋት ያህል ይቆጥሩታል።
በሀሳብ የኋሊት በትዝታ ሀዲድ ከነፈ።አመታትን ሲያስታውሳቸው ጊዚያቶቹ ሁሉ እንደ ድሮ ዘፈን black &white ሆኖ ተመለከተው። ሰከንዶች በከለር ተቀይረው የድሮውን ትቶ አሁን ያለበትን ዘመን ደግሞ በሙሉ መነፀር አሳየው። ጉዳዩ የዘመን መሸጋገር ብቻ አይደለም። አንዳች ትርጉም እና አንድምታ ይዟል። ጊዜ ታማኝ ነው።እንደ ጥበብ ሸማ ተሸምኖ በስአቱ ይደርሳል ወቅቶች ለዘመናቸው ታማኞች ናቸው።እየተቀባበሉ የሰውን ልጅ ህይወትም በፅሞና ይዘውራሉ። እያንዳንዷ ቀን ትርጉም አላት።ምንም ሳትሰራባት ካለፈች ትነጉዳለች። ጊዜ እነደ ወራጅ ውሃ ነው።ዝም ብሎ ይሄዳል። ነገር ግን እየሄደም አንተ ከሰራህበትና ለሕይወትህ ወሳኝ ግቦችን ለማሳካት የምትጥርበት ከሆነ የባከነ ጊዜ አይኖርህም።"የሚል ፍልስምናውን ከራሱ ለራሱ እያጣቀሰ ከቢሮው ወጥቶ ወደ አውቶብስ ተራ ወደ ሚገኘው ቅርንጫፍ ቢሮ ለመሄድ ወደ መኪናው ሲገባ ስልኩ ላይ ተደወለ። በፍጥነት አነሳው "አለቃ ዛሬ ጠዋት ላይ ምኒስቴሮችና ከፍተኛ ባለስልጣናት በሞተው ዋና ሳጅን አክሊሉ የሺህዋስ ላይ ስብሰባ አድርገው ነበር። እናም ስብሰባውን እርባናቢስ የማይጠቅም ብሎ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ረግጦት ወጥቷል። እናም ከጠቅላይ ምኒስቴሩ በተሰጠ ትዕዛዝ ኢንስፔክተር እንዲታፈን ውሳኔ ተላልፎበታል። ይህ መረጃ የጠላት ቡድናችንም ጋር ሳይደርስ አይቀርም!" አለ። ቶሎ ከመኪናው በፍጥነት ወረደና ተመልሶ ወደቢሮው በመግባት ሁሉንም ነገር በጥሞና ከሰማ በኋላ "በጣም ጥሩ አሁኑኑ ቡድን እስክልክልህ ድረስ ቀጥታ ወደ ኢንስፔክተር ቤት ሄደህ ተከታተል። በዚህ ፍጥነትና በዚህ ስአት ለማፈን አይሞክሩም" የሚል ምክረሀሳብ አቅርቦለት ቀጥታ ወደሌሎች ስልኮች ደወለ
*******
አንዳችም ሰው እንዳይረብሸው ስልኩን አጥፍቶ ለበርካታ ጊዜ የጠረጠራቸውን ሀሳቦች እየነቀሰ በሚገባ በወረቀት እየደረደረ እያስቀመጠ ባለበት ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ደረሰ። "እስካሁን ምንም ነገር አላገኘኽም? "አለ ችኮላና ንዴት በተቀላቀለበት አነጋገር። "እስካሁን ይሄን ነገር አውጥቻለሁ ከዛ ውጪ የማውቀውጰነገር የለም።እስኪ ደግሞ አንተ ተመልከትና አመሳጥር"ብሎ ተሕሚድ ቦታ ለቀቀለት። "ምን አይነት ኤሊቶች እንደተሰበሰቡ አላውቅም። ሁሌም በንፁሀን ደም ላይ ቆመው በሆደሰፊነት ማውራት የማይሰለቻቸው" ብሎ በንዴት ተቀምጦ ላፕቶፑን ጠጋ አደረጎ ማስታወሻውን ገልበጥ ገልበጥ አድርጎ ይመለከት ጀመር። "ኢንስፔክተር ጥሩ ስሜት ላይ ካልሆንክ አረፍ በል"አለ ተሕሚድ ጥሩ ስሜት ላይ እንዳልሆነ በሚገባ በንግግሩና በሁኔታው በመረዳት። ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ለትሕሚድ የሐዘኔታ ጥያቄ ምላሽ ሳይሰጥ ዝም ብሎ ተሕሚድ የፃፋቸውን ፊደሎች በአፀንኦት ይመለከታቸዋል።የተፃፉትን ፊደላት ከናፊባ መፅሐፍ ጋር በስሱ ያመሳስል ጀመር። አንዳቹም ሀረግ ከተደረደሩት ፊደሎች የመነጨ ሀሳባዊ አልነበረም።የሁለቱም የሀሳብ ቅኔ ለየቅል ነው።ወደ ጎን ደርድሮ አንዳች ፍች ይሰጣሉ ብሎ ቢያነባቸውም ከተራ አልፋቤት ድምፀት በቀር ወደ አንድ ተስፋ ወደሚያጭር ትርጉም አልተቀየሩለትም። በውስጡ የባለስልጣናቱ ደንዳናነትን እያሰበ በጎን በኩል ደግሞ የብዙ ንፁኅንን ሰዎች ሕይወት የቀጠፈውን ወይም የቀጠፈችውን ለማግኘት ከልቡ ሽቶ ነፍሱ እስክትወጣ በመፈለግ ላይ ነው። ልክ እንደ ፓይታጎረስና ሲግመንድ ሁሉ የብዙሀኑ የፍልስምና ሊቆች ሙከራህን ቀጥል (keep trying) እንደሚሉት የማግኘት ሙከራውን በየቀኑ እየሞከረ ነው።ቢሆንም ከሚደራረቡበት ችግሮች አንፃር እየደከመው በቶሎ እንዲያበቃለት እንደተማፅእኖም ፈጣሪን ይለማመናል።

@amba88
2.6K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 16:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 16:46:53 ዓሳ ሆኜ ሳለ
ከወፍ ያዘኝ ፍቅር
አለመብረሬ ነው የሚለኝ ቅርቅር።

አምባዬ ጌታነህ (የዮቶር ልጅ) @Adwa1888
2.5K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 13:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 16:32:20 በጠራው ጨረቃ በጠራው ለሊት፣
ምን ያላልኩት አለ ~ ያልተናገርሁት።

አምባዬ ጌታነህ (የዮቶር ልጅ) @Adwa1888
2.4K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 13:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 19:36:49 "ናፊባ"
ክፍል ~ ሠማንያ አምስት
በአምባዬ ጌታነህ @Adwa_1888
"ሙሉ አዳር አልወጣም። ሲመስለኝ መርዶው አልተነገረውም። የዋና ሳጅኑን መሞት ቢሰማ ኖሮ አስችሎት አይቆይም!" አለ የራሱን ፀጉር በጣቶቹ እየመነሸረ። ከእንቅልፍ መባነኑ እንዳይታወቅበት በተቻለው መጠን ሳይተኛ እንዳደረ ለማሳወቅ እየጣረ።" ተኝተህ በነበረበት ስአት ሄዶ ከሆነ ግን እኔ የለሁበትም!!" ንዴት የተቀላቀለበት ዱብዳ አነጋገር "ኧረ በጭራሽ ለሰከንድ ያህል እንኳን ልተኛ አላንቀላፋሁም።አይኔንም ከበራቸው አልነቀልኩም"አለ "እሺ ብቻ ለቅሶው ጋር ቀድሞህ ከተገኘ የሚያሳውቀኝ ሌላ አባል አለ" ብላ አስፈራራችውና ስልኩን ዘግታ አዲስ ነገር እንዳለ ለማወቅ ስልኳን ወደሌላኛው አሻንጉሊቷ ደወለች። የስልክ ተቀባይዋም ስልኩን አንስቶ ምንም ነገር እንደሌለና እስካሁን እንዳልመጣ ሲነግራት ከጥርጣሬዋ በመላቀቅ እፎይ አለች። ጥርጥሬ እንደምግብ የምታመሰኳው ነገር ነው። ለእሷ እያንዳንዱ ድርጊት ትልቅ ትርጉምና ዋጋ አለው። ይህን ምስጢራዊ ቡድን በሀላፊነት ስትመራ እያንዳንዱ ሰራተኛዋን በጥርጣሬ ነው የምትመለከተው። አንዳቸውንም የውሸት እንጅ የእውነቷን አታምናቸውም። ሁሉም የግቧ መውጫ መሰላላቸው እንጅ ሌላ አንዳች ጥቅም የላቸውም። ለዚህም በእነሱ ፊት ኮስታራ ፊቷን ነው ሰርክ የምታሳያቸው። አሁን ላይ ግን በርካታ ሰራተኞቿን በሞትና በክህደት ካጣች በኋላ ውስጧን ፍርሃት ቢገባውም ፍርሀቷን ግን በእነሱ ፊት አታሳይም።ቀን በቀን በወንድሟ እየተሳደደችም ፅንፍ ህልሟን ለማሳካት ማንኛውንም ነገር ማድረግ እንዳለባት አውቃለች። በጥንቃቄና በብልሀት የተወጠሩት የሚሽን ክሯቿ ለመበጠስ እየመነመኑ ቢመስሉም ነገር ግን እሷ በፍፁም ተስፋ አልቆረጠችም። ነገር ግን ግማሽ ነፍሷ የተሸነፈች እንደሆነ ይነግራታል። ቢሆንም እስከመጨረሻው ድረስ እታገላለሁ በሚል ፅኑ ፍላጎት መንገዷን ቀጥላለች።
*****
ንጋት ከጨለማ ወስዶ መልዕይተ ቀኑን ለፀሐይ ካስረከበ በኋላ ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው በማለዳ ቢነቃም ሀዘን እንዳጠላበት ነው። እስካሁን ፊቱ በጭራሽ የነቃ አይመስልም። የክብር ልብሱን አንድ በአንድ ከለበሰ በኋላ "በል ተሕሚድ ውሎዬ ለቅሶ ላይ ነው የሚሆነው።አንተ እንግዲህ የተለዬ ነገር ለማንኘት ሞክር የቻልከውን ያህል ጣር። ይሄ ሊሆን ይችላል ብለህ የጠረጠርከውን በሙሉ በማስታወሻህ ይዘህ ጠብቀኝ።የሕይወቴ ፈታኙና እጅግ ልዩ ትርጉም ያለው ምርመራዬን ነው የተጋራኸኝ። ከአንተ የሚጠበቀው ጥርጣሬዎችህነ ባገኘኽበትና ባሰብክበት ልክ ማስፈር ነው የሚጠበቅብህ ሌላ ከአንተ ምንም አይጠበቅም።ብሎ ትከሻውን መታመታ አድርጎት ትቶት ወጣ ።
ሸዋንግዛው በሀሳብ ውስጥ ትክዝ እንዳለ ነው። በአንዳች ነገር ክንፉ ተሰብሮ ዋጋ ቢስ የማይረባ ንስር ስነልቦናን ሀያ አራት ስአት ባልሞላ ጊዜ ተላብሷል። አቅሙ እስከዬት እንደሆነ የነገሩት መሰለው። የነዚህ ምስጢራዊ ሰዎች ማንነትና ምንነት የውሃ ሽታ ሆነበት። ሁኔታው ከአቅሙ በላይ እንደሆነ እንዲያውቅ አውቆም እንዲያምን ያደረጉት መሠለው።በዚህ ሁሉ የራስ ጥያቄና መልስ ተወጥሮ ባለበት ዝም ብሎ የመሀሉን ስፖኪዮ ሲመለከት ከኋላው ባለ አንድ ቅያስ ላይ መኪና ቆሞ ተመለከተ። ሽጉጡን ከመሳቢው አቀባብሎ በማውጣት ቀስ አድርጎ ማርሹ ጋር ያለበት ክፍት ቦታ ቀስ አድርጎ አስቀመጠው። ሰረቅ አድርጎ ወደ ኋላ እየተመለከተ "እነዚህ ውሾች እኔንም እየተከታተላችሁኝ ነበር? የማትረቡ ብሎ ሊዞር ሲል አይኑ ላይ አንድ ነገር ተመለከተ። የሚከታተለው መኪና ላይ "ዓደይ ሞል" የምትል በራሪ ወረቀት ነገር የመኪናው መስታውት ላይ ተመለከተ። የምፀት ፈገግታ ፈገግ አለና "መች አጣኋችሁ የዚህን ሰው ማንነትና ምንነት ያወኩ ጊዜ ያኔ እኔ ኢንስፔክተር ሸዋንግዘው አይደለሁም ልጆቼን ይንሳኝ!" አለ ከንፈሩን ንክስ እያደረገ።
********
ሲሐም ኤሌዝንና ብሩክታዊትን ትምህርት ቤት አድርሳ ከመጠች በኋላ ተሕሚድን ትተሻሸዋለች።"ኧረ ተይ የኔ ፍቅር ኢንስፔክተር በጣም ትልቅ ሀላፊነት ነው ሰጥቶኝ የሄደው"አለ የሚሰራውን ስራ አቁሞ አይኖቿን በስስት እየተመለከተ። " ትንሽ ጊዜ ብቻ ነው እኮ።ከዛ ስራዬን ስጨርስ ምንም ችግር የለውም።የፈለግነውን ጊዜ አብረን እናሳልፋለን"ብሎ ወደስራው ሊዞር ሲል ሲሐም መላፋቷን ስትቀጥል ትሕሚድ ቦግ አለበትና "እየነገርኩሽ አይደል ሲሓ! ምንድን ነው እንደ ህፃን ልጅ የምታዳግሚኝ"ብሎ ኮስተር አለባት። "እና ልትቆጣኝ ነው?" አለች እሷም ከመቅፅበት ኩስትር አለች። "የምገላው ባህሪሽ ይሄን ነው።በተደጋጋሚ ነግሬሻለሁ።ከዚህ በኋላ ግን ደግሜ አልነግርሽም እንዳታስቢው እሺ"አለና ዝም ብሎ ወደ ላፕቶፑ አይኖቹን ላከ። ሲሐም ጥፋቷ ታውቋት ይሁን በተሕሚድ ተናዳ በውል ባታስታውቅም እየተመናቀረች ክፍሉን ለቃለት ወጣች። የእሷን መውጣት ተከትሎ ትንሽ ጊዜ ከቆዬ በኋላ በሩን ከውስጥ ቆለፈው። መዘጋቱን የተመለከተችው ሲሐም ይበልጥ በመናደድ "ቆይ አሁን በሩን መዝጋት ምን ይሉታል?" ብላ አጉተመተመች።
********
በርካታ የፖሊስ መኮንኖች፣ የፖሊስ አባላት፣ የፌደራል ፖሊሶች፣የደህንነት ተወካዮች ሰቪሎች እና ሲቪሎች እንዲሁም ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት ከሆስፒታል የአስከሬን የማውጣት ስነስርአትና በክብር እየተደረገለት ይገኛል። ሁሉም ፊት ላይ አንዳች ሀዘን ይነበባል። በተለመደው ዝግጅት በስነስርአት አስከሬኑ ወደ መኖሪያ ቤቱ ተሸኝቶ ዘመድ አዝማድ የስራ ባልደረባዎችና ጓደኞች በተገኙበት የማስተላለፍ ስራ ከተሰራ በኋላ የሁሉም የፖሊስ የደህንነትና የወንጀል ምርመራ ክፍል እንዲሁም የፌደራል ፖሊስ ለስብሰባ እንዲገቡ የፍትሕ ምኒስቴሩና የደሕንነት ኃላፊው ለሁሉም መረጃውን አደረሰ።
ጥሪ የተደረገላቸው የስራ ሀላፊዎች ሁሉም ተገኝተው ስብሰባው መካሄድ ሲጀምር ሁሉም በየተራ ሀሳብና አስተያየት መስጠት ጀመረ። ሰብሳቢዎቹም ፍፁም በሆነ መረጋጋት የተፈጠረው ነገር ምንም ሳይመስላቸው ፊታቸውን አለስልሰው ልባቸውን አደንድነው ስበሳባቸውን ማካሄድ ቀጠሉ። ኢንስፔክተር ሸዋንግዛው ለአንድ ሀያ ደቂቃ ስብሰባው አብ የሚል ነገር ያለው እስኪመስለው ድረስ ቢቆይም ነገር ግን። ዝም ብሎ ሁኔታውንና ድርጊቱን ውሃ ለመቸለስ ለማቀዝቀዝ እንደሆነ ሲረዳ የደህንነት ምኒስቴሩ ለአስተያየት ሰጪዎች እድል በሚሰጥበት ጊዜ እጁን አውጥቶ እድል ከተቀበለ በኋላ የደህንነት ምኒስቴሩን ይሁንታ ሳያገኝ መናገር ጀመረ። ሁሉም በድንጋጤ ዞረው ተመለከቱት "እስካሁኑ ደቂቃ ዴረስ በትዕግሥት ስጠባበቅ ነበር። ምን አልባት ሄደን ከምንሰራው ስራ በላይ የበለጠ ቁምነገር ካለ ብዬ ነበር የተቀመጥኩት። እንጅ የፖለቲካ ሽኩቻውንና አንድ ነገር በተፈጠረ ቁጥር ስብሰባ የምትሉት ነገር በጣም ይሰለቻል። ትላንት ንፁሀኖች ሲሞቱ ነበር።ዛሬ ደግሞ ይሄው ቢሯችን ላይ ገብቷል።ዋና ሳጅን አክሊሉ የሺህዋስ ከወራት በፊት ልክ እንደኛ የንፁሀን ደም ደመክልብ ሆኖ እንዳይቀር ለዘመዶቻቸው ደግሞ ፍትህን ለማስገኘት ሌት ተቀን ሲሰራ የነበር ጓዳችን ነበር። ነገር ግን በዚህ ስአት እሱም የነዛ ምስኪን ዜጎች እጣ ፈንታ ደርሶት እሱም አርፏል። እኛ ደግሞ አሁንም በቸልተኝነት ስብሰባ ላይ ተቀምጠን የማይሆነውንም የሚሆነውንም እያወራን ነው። ይቅርታ እኔ በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኜ ስብሰቤውን መቀጠል አልችልም!" ብሎ .......

@amba88
3.7K viewsአምባዬ ጌታነህ❶ , 16:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ