Get Mystery Box with random crypto!

Alex Abreham በነገራችን - ላይ

የቴሌግራም ቻናል አርማ alexabreham — Alex Abreham በነገራችን - ላይ A
የቴሌግራም ቻናል አርማ alexabreham — Alex Abreham በነገራችን - ላይ
የሰርጥ አድራሻ: @alexabreham
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.24K
የሰርጥ መግለጫ

በገበያ ላይ የሚገኙ የአሌክስ አብረሃም መፅሐፍት ዝርዝር
1- ከዕለታት ግማሽ ቀን
2- ዙቤይዳ
3 - ዶክተር አሸብር
4 - እናት ሀገር ፍቅር
5 - አንፈርስም አንታደስም
💚💛❤️
አሌክስ ማለት በቃ አሌክስ ነው::
Not Official
@con_me_here

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-09 09:44:56 መንገድ
ክፍል 1
(በእውቀቱ ስዩም)

በደናው ቀን ብርቱ ነበርሁ፤ ባንድ እጄ ፑሽአፕ እየሰራሁ በሌላው እጄ ጢሜን እላጭ ነበር፤ አሁን አንድ ኪሎ ሜትር ከተራመድሁ ይደክመኛል፤ ትናንት ከቤት ወጥቸ የቀበናን መንገድ ትንሽ ወረድኩና እንግሊዝ ኢምባሲ የተከለውን የስልክ እንጨት ተደግፌ እፍወይይይይ ብየ ተነፈስሁ፤ እፎይይ ስል ከሆዴ መለስተኛ አውሎ ነፋስ ወጣ! መንገድ ዳር በቆሎ ጠብሰው የሚሸጡ ሴቶች ባተነፋፈሴ ተደንቀው ዞር ዞር ያሉ አዩኝ “ አሁን የተነፈስከውን ባግባቡ ብትጠቀምበት አምስት ምድጃ ያቀጣጥላል” የሚሉኝ መሰለኝ ፤
የቀረውን መንገድ በመኪና ለመመለስ ፈለግሁ፤ ግድ ካልሆነ በቀር ራይድ አልጠራም፤ ቀን ጥሏቸው መንገድ ዳር የቆሙ ላዳዎችን እጠቀማለሁ፤ ይቺ ላዳ አሮጌ ናት፤ ፍሬቻዋ ስለተሰረቀ ፋኖስ ተገጥሞላታል፤ የላዳውን በር ልከፍተው ሞከርኩ፤ እምቢ አለኝ ፤ ሰውየው ከውስጥ ሆኖ ሊያግዘኝ ተፍጨረጨረ ፤ በመጨረሻ ወጣና ለሁለት መታገል ጀመርን፤ ከእልህና እህል አስጨራሽ ትግል በሁዋላ የላዳው ጋቢና በር እንደ ድስት ግጣም ተነሳ! ገባሁና ከሁዋላ ተቀመጥሁ፤ ሾፌሩ የሳይክል እግር የሚያክለውን መሪ እንደ በረኛ ተጠምጥሞበት ጉዙ ጀመርን፤
ከጎኔ ያለውን ሳተራምስ ከቆየሁ በሁዋላ “ ቀበቶ የለም እንዴ?” ስል ጠየኩት
“ ቀበቶ ተበላሽቷል! ሰንሰለቱን ብትጠቀም ይደብርሀል?”
እንደ ባህታዊ ሰንለቱን ታጥቄ ጉዞ ጀመርን፤
“ የማንን ሙዚቃ ላድርግልህ? “
“ የሙሉቀን መለሰ ይኖራል?”
“ አይጠፋም “ አለና ፤ ከእግሩ ስር ዳንቴል ለብሶ የተጋደመውን ቴፕ ቆስቁሶ ጥላሁን ገሰሰን ከፈተልኝ ፤
“የዘንባባ ማር ነው ፍቅርሽ
ቄጤማ ይመስላል ጸጉርሽ”
“ የዘንባባ ማር የሚባል ነገር ግን አለ?” የሚል ጥያቄ አነሳሁ፤
“ ፍቅር አይያዝህ ወንድሜ” አለ ሾፌሩ” ፍቅር ከያዘህ አይደለም የዘንባባ ማር ፤ የግራዋ ወተት ሊታይህ ይችላል” አለኝ ሾፌሩ
እንዲህ እያወጋን ስንሄድ የትራፊክ ፖሊስ ነፍቶ አስቆመን፤
“ ጥፋቴ ምንድነው?”
“ ወድያ ያለውን መብራት ጥሰህ መጥተኻል”
ሰውየው በናቱ በአባቱ በመላእክቱ እና በህብረተሰቡ ምሎ ሸመጠጠ፤
ለሀያ ደቂቃ ከተከራከሩ በሁዋላ ሾፌሩ “ የዛሬን አስተምረህ ልቀቀኝ “ ሲል ሰማሁት፤
“ አስተምሬ ብቀጣህ እመርጣለሁ” አለ ፖሊሱ ቅጣቱን ፈርሞ አቀበለው ፤ ከዚያ ሌላ ህግ የሚጥስ መኪና ፍለጋ በጉጉት ማማተር ጀመረ፤
ሾፌሩ የተሰጠውን ደረሰኝ ዳጎስ ባለ የቅጣት መዝገቡ ውስጥ ከወሸቀ በሁዋላ ፖሊሱ ወደ ቆመበት አቅጣጫ እየተመለከተ
በሚጢጢ ድምጽ “ እስቱቢድ” ብሎ ተሳደበ፤ በሆዱ ቢሳደብ ራሱ ከዚህ የተሻለ ሳይሰማ አይቀርም፤
2.2K views06:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 04:51:18 #ሰው_ባለው_ነው....."
Mengistu M Tsion


ሰንበት ማለዳ ላይ ረፈድ አድርጌ ብነሳም በእንግድነት መጥቶ ከኔ ቤት ሶፋ ወንበር ላይ የተኛው ባልንጀራዬ ግን አሁንም አልነቃም ነበር። ማታ የጠጣቸው ባዶ የቢራ ቆርቆሮዎች ጠረጴዛውን ሞልተውታል። የአሜሪከን ባንዲራ ቀለም ያለበት ትልቅ ላይተርና American Spirit የሚባል ቢጫ ቀለም ያለው የትንባሆ ፓኬት ደግሞ ከጠረጴዛው ስር ወድቋል። መጋረጃውን ወደ አንድ ጎን ሰብስቤ የሳሎኑን መስኮት ከፈትኩት። ብሩህ ሞቃት ማለዳ! ገና ከጠዋቱ አራት ሰዓት እንኳ ሳይሆን ሙቀቱ ፊት ይጋረፋል! ተዘግቶ ያደረው ክፍል ይንፈስበት ብዬ እንጂ የቤቱን ውስጥ ቅዝቃዜ ለመጠበቅ መስኮትም ሆነ በር የግድ መዘጋት ነበረበት።

የተጋደመውን ወዳጄን ገልመጥ አድርጌው
"አንተ አትነሳም እንዴ?" እያልኩ ወደጄን በድምፄ ትልቁን ቲቪ ደሞ በርቀት መቆጣጠሪያው ከእንቅልፋቸው አባነንኳቸው። ባልንጀራዬ አፋሽኮ ተገላብጦ ተመልሶ ቢተኛም የቀሰቀስኩት ቲቪ ግን ብቻውን ያወራ ጀመር። ስለሃገሬ "ተስፋ ቢስ" ወሬ የምቃርመው አልያም ፈገግ የሚያሰኙኝን የቪዲዮ ክሊፖች መልከት የማደርገው ሰንበት ማለዳ ላይ ነው። ታዲያ ዛሬም አንዲት የfb ወዳጄ "ተመልከታቸው!" ስትል ከላከችልኝ ሁለት ሊንኮች አንዱን ተጭኜ ከፈትኩት። ይህች የfb ወደጄ በጣም ካላስገረማት፣ ወይ ካላሳቃት፣ ወይ ካላስደነቃት በቀር መልዕክቶቿን ወደ እኔ ስለማትልካቸው ብዙ ግዜ የምትልካቸውን ተመልክቼያቸዋለሁ።

የቪዲዮ ምስሉ የሚያሳየው በቲቪ ተከታታይ ድራማ ላይ የሚታወቀውን ንብረት ገላውን (እከ) ቃለ ምልልስ ነበር። እከ ልክ ድራማው ላይ እንዳለው የዋህ ነው ለካ! አወራሩ ምስኪን ባላገር ፣ አቀራረቡ ቀጥተኛ፣ ካንደበቱ በሚወጡት ገራገር ቃላት የተነሳ ደግሞ የነብሱን ቅንነት ማየት ይቻላል። "ካፍ የሚወጣ ከልብ ይወጣል" አይደለ የሚል መፅሀፉ! ድንግጥ ብዬ ፍንድት እስክል የሳቅኩት "ባንድ አረፍተ ነገር ለምን አልገላገለውም" ሲል አስቦ ይመስለኛል "ዘማዊ አርቲስት ነበርኩ በቃ" ሲል ነው። ያኔ ነበር በረጅም ሳቄ የተነሳ ከእንቅልፉ የተነሳው ባልንጀራዬ ክንብንቡን ገልጦ አይኖቹን እያሻሸ
"ምን እያየህ ነው ?" ያለኝ
"ታሪክህን" አልኩት ይህው በእንስት ጉዳይ የማይታማውን ወዳጄን። መልስ አልሰጠኝም። ቆይቶ
"ስንት ሰዓት ነው አለኝ?" እከ ላይ ተመስጬ ስለነበር አልመለስኩለትም። ተከናነበና ተመልሶ ተኛ!

እከ የዋህ ልበለው ጂል ግራ እንደገባኝ ቃለ ምልልሱ ሳይሆን "የንሰሀ" ፕሮግራሙ አለቀ። በዚህ ክፉ ግዜና የተበላና የተጠጣው ሳይቀር በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በሚከርምበት ዘመን ራስን እንዲህ አጋልጦ ፣ ድካምና ገመናን አደባባይ ማስጣት ለምን እንደፈለገው አልገባኝም። የርሱስ ዘመዶች፣ የሚስትስ ቤተሰቦችና ባልንጀሮች ላይ የሚያደርሰው አሉታዊ ተፅእኖው የከፋ አይሆንም ወይ?? በርግጥ ሁላችንም ትንሽ ትንሽ "እከ" ነን። ሆኖም አንዳንድ ነገር ደሞ ከመገለጡ ይልቅ መሸፈኑ ነው ይበልጥ አስተማሪነቱ።
"ከኔ ተማሩ! ከትዳር በፊት አትቅበጡ" በሚል ያደባባይ ንሰሀውን ያጠናቀቀውን "እከ" ን ትቼ "ይህን የእርሱን ፕሮግራም ካየች በኋላ ቢሆን ኖሮ እስከ ጋብቻዋ በድንግልና ትፀና ነበር" እያልኩ እየቀለድኩ "ካለብኝ የወሲብ ሱስ የተነሳ ሃምሳ የሚበልጡ ወንዶችን በተከታታይ አውጥቻለሁ። ግን ቅምም አላለኝ። ምን ላድርግ? እርዳታ ፈልጋለሁ" ወደምትል ሃያዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደምትገኝ ሌላኛይቱ ተናዛዥ ታሪክ መመልከት ተሸጋገርኩ። ልጅቱ መልኳ ባይታይም የሚያማልል ድምፅ ያላት ወጣት ነበረች። ታሪኳ የውሸት ይሆን እንዴ ስል በጥርጣሬ የሰማኋት ቢሆንም ከታሪኩ consistency እንዲሁም ከምትናገርበት ጥልቅ ስሜት ድምፀት የተነሳ ጥርጣሬዬን ለማስወገድ ተገድጄ ነበር። ልጅቱ ልትተው በምትፈልገው ግን ባልቻለችው ክፉ የዝሙት ሱስ ሰንሰለት ተጠፍንጋ ስትሰቃይ ላደመጣት ታሳዝናለች።
"በነጠላ ጫማ ባንቺ አረማመድ
እንዴት አለቀልሽ ያሁሉ መንገድ" እንደሚለው ዘፈን ሁሉ ባንድ ሰሞን ብቻ ሃምሳ ኮርማ አስተናግዶ ቅም ያላለው የወሲብ ዛሯን ከልጅነቷ ጋር አነፃፅሬ
በውስጤ " ሰው ብርቱ......." ብየለሁ።

የዚህችን ወጣት ታሪክ ተገርሜ እያደመጥኩና እየተመለከትኩ በነበረበት ወቅት ተኝቷል ብዬ የነበረው ባልንጀራዬ ለካስ ነቅቶ ኖሮ ክንብንቡን ገለጥ አድርጎ አብሮኝ ሲከታተል ነበርና ፕሮግራሙ ሲያልቅ
"ስልኳን አላስቀመጠችም እንዴ?" አለኝ
ንቅት ብሎ ጥርት ባለ ድምፅ!
"ለምን ፈለከው?" አልኩት አትኩሬ እያየሁት።
"እርዱኝ! እርዳታ ፈልጋለሁ ስትል አልሰማሃትም እንዴ? ዛሬ አይደል እንዴ ሃገር ቤት የምበረው?" አለኝና በረዥሙ አፋሸከ።
"እሺ ኮርማው! በምን ልትረዳት ነው?" አልኩት የግርምት ሳቅ እየሳቅኩ
"ያው ሰው ባለው አይደል የሚሰለፈው!? በምችለው አቅም ልረዳት ነው። እህታችን እኮ ነች" አለኝና ወደ መታጠቢያ ቤት ለመሄድ ከሶፋው ላይ ተነሳ!
ከ...................ት ብዬ እየሳቅኩ ቁርስ ላዘጋጅ ተነሳሁ!

ብያለሁ እኮ ትንሽ ትንሽ ሁላችንም "እከ" ነን።

Mengistu M Tsion
2.9K viewsedited  01:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 04:50:53
Mengistu M Tsion

2.2K views01:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 08:30:17 አንዳንድ ነገሮች
(በእውቀቱ ስዩም)
ፓስተር ዮናታን “ መልካም ወጣት “ የሚል ስልጠና በመስጠቱ የምትናደዱ ሰዎች ፥ ለምን እናንተ “ መልካም ሽማግሌ” የሚል ስልጠና ጀምራችሁ አትሸቅሉም? እኔና ዮናታን የመጀመርያዎቹ ተመዝጋቢዎች እንደምንሆን ተወዲሁ ላረጋግጥላችሁ እፈልጋለሁ፡ ፡
ዘግይቼም ቢሆን ለኢትዮጵያ ህዝብ እንኩዋን ደስ ያለህ ማለት እፈልጋለሁ፤ አንዳንዴ በደስታ ስትሆኑ ብዙ ነገር አይታችሁ ባላየ ታሳልፋላችሁ፤ አትሌቶቻችን ድል ያደረጉ ቀን እጅግ ከመደሰታችን የተነሳ “ እኛም ኮራን “ እሚለውን ዝማሬ እስከመጨረሻው ታግሰን እንሰማዋለን፤
በቀደም እዚህ በረንዳ ላይ ቁጭ ብለን እንቀመቅማለን፤ ከመካከላችን አንዱ፥
“ ትግሬዎች በስልጣን ላይ በነበሩበት ጊዜ ያላገኙትን የሩጫ ድል እንዴት ሊያስታቅፉን ቻሉ” የሚል ጥያቄ ጠየቀ፤
የምታስተናግደን ሴት፤ የሰላም ተስፋየን ቅርጽ እና የፍርያት የማነን ፊት አስተባብራ የያዘች ቆንጅየ ልጅ ስለሆነች ፥እስዋን ኢምፕረስ ለማድረግ እየተጭዋጩዋህን እየተሻማን ምላሻችንን አቀረብን፤
አንድ “ መልካም ሽማግሌ” ያቀረቡትን ምላሽ ከታች አስቀምጨዋለሁ::
“ የትግራይ ሰው አትሌቲክስ ከጥንት ጀምሮ መክሊቱ ነው ፤ ደብረዳሞን የመሳሰሉ ተራሮች በሌጣ እግሩ ሲወጣ ሲወርድ ስለኖረ እግሩ ብርቱ ፥ ትንፋሹ የትየለሌ ነው ፤ ግን መንግስትነት ያዘናጋል፤ መንግስት ስትሆን ታሯሩጣለህ እንጂ አትሮጥም፤ ስላዳመጣችሁኝ አመሰግናለሁ”
በነገራችን ላይ ስለምስጋና ያለኝ ፍልስፍና አጭር ነው ፤ የተደረገለት ያመስግን ! የተደረገበት ያማርር!
ለነገሬ ማድመቂያ የሻለቃ ገብረሀናን ተረብ ልንገራችሁ፤( የገብረሀና ማእረግ ዘመኑን እንዲመጥን ሆኖ ተቀይሯል)
ሻለቃ ገብረሀና ደቀመዝሙር አላቸው ፤ ደቀመዝሙሩ ቀኑን ሙሉ ሲዞር ውሎ ከየቤቱ ቁራሽ እና ጥሬ ለምኖ ያቀርብላቸዋል፤ አንድ ምሽት ደቀመዝሙሩ ቀኑን ሙሉ ሲንከራተት ውሎ አልቀናውም፤ ራት ሰአት ላይ ከግብዳ አኮፋዳ ውስጥ ፥ የትራምፕን መዳፍ እምታክል ጢንጥየ ቁራሽ አውጥቶ አቀረበላቸው ፤ ሻለቃ ገብረሀና እያጉረመረሙ መዳፋቸውን ወደ ቁራሺቱ ሰደድ ሲያደርጉ፥ ደቀ መዝሙር እጃቸውን አፈፍ አድርጎ ያዛቸውና፥
“ሻለቃ ከመብላታችን በፊት እናመስግን " አላቸው፤

እሳቸው ፈገግ ብለው፤
“ ተው ልጅየ! አሾፋችሁብኝ ብሎ መብረቅ ይጥልብናል”
3.5K views05:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-24 07:55:20
ጃንሆይ

በአንድ ወቅት የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጠኛ ንጉሱን እንዲህ ሲል ይጠይቃቸዋል....

“ለመሆኑ ...ኢትዮጵያዊነት ምንድን ነው? ”
ጃንሆይም ቆፍጠን ባለ አነጋገር ለዛ...
“ኢትዮጵያዊነት ኩራትና ትህትና ነው” አሉት።
ጋዜጠኛውም ቢሆን የዋዛ አልነበረምና......
“ይቅርታ ያድርጉልኝና ጃንሆይ ይሄ ሃምብልነስ እና ፕራውድነስ የሚሉት ነገር እርስ በርሱ የሚጣረስ ማንነት አይመስልዎትም?” የሚል ጥያቄ ያስከትላል።

ንጉሱም እንዲህ አሉ .....“አየህ አንድ በጣም ተራ የምትለው ገበሬ ቤት በእንግድነት ብትሄድ ያለውን አብልቶ፤ እግርህን አጥቦ፤ ያጠበውን እግርህን ስሞ፤ አልጋውን ላንተ ለቆ እርሱ ግን መሬት ላይ ይተኛል። በዚያው ልክ በሚስቱ፣ በርስቱና በሃገሩ ላይ ብትመጣበት ደግሞ በግንባርህ ላይ ጥይት ይቆጥርልሃል፤ ስለዚህ አይጋጭም፤ ነገር ግን ይሄንን ነገር ለመረዳት አንተ ራስህ ኢትዮጵያዊ መሆን አለብህ” ነበር ያሉት።
3.9K views04:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 08:43:42
ስለተመቸኝ!!!

መልካም ቀን!
4.2K views05:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 05:52:02 #ፉዣዥ

ባለፈው እኮ ነው። ፉዣዥ የጠፋለት። ተቅበዝብዤ በሌላ ፕሮፋይል ስፅፍ ነበር። አንደኛው የፃፍኩት ከታች ያለው ነው።
*
“እግዚአብሄር ቬጂተሪያንን (ስጋ ጠሎችን) ይጠላል” አለኝ አንድ ወዳጄ። ስጋ ቤት ምሳ እየበላን።

“እረ ባክህ” አልኩት በመገረም።

“የገረመህ ይመስላል”

“እንዴታ። እንዴት አይገርመኝ። መዳፌን አፌ ላይ መጫን ብቻ እኮ ነው የቀረኝ። ባለሁበት ደርቄ እያየኸኝ። ምን ጥያቄ አለው? ገርሞኛል እንጂ”

“ለምን ገረመህ?”

“ያልጠበቅኩት ነገር ነዋ”

“ምኑን ነው ያልጠበቅከው?”

“እግዚአብሄር ስጋ ጠሎችን (ቬጂተሪያኖችን) እንደሚጠላ”

“ማንን የሚጠላ ነበር የሚመስልህ?”

“እኛን ነዋ። ስጋ አፍቃሪዎችን”

“እኛንማ ይወደናል”

“እንዴት ይወደናል? ህይወት እያጠፋን እንዴት ይወደናል?”

“የአቤል እና የቃየንን ታሪክ ታውቀዋለህ መቼም?”

“እንዳንተ ባይሆንም በጥቂቱ”

“ምን ታውቃለህ? እስኪ ንገረኝ”

“ቃየን ታላቅና አርሶ አደር እንደነበር። አቤል ታናሽና አርብቶአደር እንደነበር አውቃለሁ። በተጨማሪም ቃየን ታናሽ ወንድሙን አቤልን እንደገደለው”

“ለምን ገደለው?”

“በቅናት ተነሳስቶ”

“ምን አስቀናው?”

“እግዚአብሄር የአቤልን መስዋእት ወዶ የእርሱን ግን ስላልተመለከተለት”

“አቤል ምን መስዋእት አቅርቦ ነው?”

“ከመንጋዎቹ ውስጥ መጀመሪያ የተወለዱትንና የሰቡትን”

“ቃየንስ ምን አቀረበ?”

“ቃየንማ አርሶ አደር ስለነበር ገብስና በቆሎ ድንችና ዳጉሳ ይሆናላ”

“ታዲያ እግዚአብሄር ምን አለ”

“እግዚአብሄር የአቤልን ስጦታ ወደደው”

“የቃየንስ?”

“የቃየንንማ እንኳን ሊወደው አልተመለከተውም ነበር”

“ታዲያ ከዚህ በላይ ምን ትፈልጋለህ። እግዚአብሄር ስጋ ተመጋቢዎችን ይወዳል”

ጥርግ አድርገን በላን። እግዚአብሄር እንደሚወደን እያሰብን በደስታ ተመገብን። ቬጂተሪያኖች እንዳይነሱብን ብቻ። ከተነሱብንም እንደ ቃየን በምድረበዳ መቅበዝበዛቸው ነው።

አንድ ነገር ግን ከነከነኝ። አቤል ከብት አርቢ ነበር፥ ቃየን ግን አርሶ አደር። ይህ ማለት አቤል ስጋ ብቻ ተመጋቢ ነበር ማለት ነው?

ቃየን ስጋ አይበላም ነበር ማለት ነው?

አቤል እና ቃየን አይገበያዩም ነበር ማለት ነው?

ደወልኩ ወዳጄ ጋር። በስንት ጥረት አገኘሁት። የከነከነኝን ጥያቄ አነሳሁለት።

“አንተ ደግሞ ቀልድ አታውቅም” አለኝ።

“ምን አይነት ቀልድ ነው? ሲሪየስ በሆነ ጉዳይ ትቀልዳለህ እንዴ?”

“ምን ተጎዳህ። በደስታ ጥርግ አድርገህ በላህ አይደል”

“እርሱማ ልክ ነህ”

“አንተም እንዴት እንደ ቃየን ትሆናለህ”

“እንደ ቃየንማ አልሆንኩም፤ እንደ አቤል እንጂ”

“ምኑን እንደ አቤል ሆንክ? እንደ ቃየን እንጂ። የአቤልን መስዋእት እግዚአብሄር ወዶታል፥ የኔን አልወደደውም ብሎ ያመነው፥ የደመደመው እራሱ ቃየን ነው። እግዚአብሄር ይሄንን ይውደድ፥ ያንን ይጥላ፤ በምን አይቶ ነው ያመነውን ያመነው? እግዚአብሄርን የኔን አልተመለከተውም ብሎ ያመነው በምን አይቶ ነው? እግዚአብሄር የማይመለከተው ነገር አለ እንዴ? በእግዚአብሄር ዘንድ እኮ ክፉ እና መልካም የሚባል የለም። ሁሉም አንድ ነው። ክፉና መልካምን የፈጠሩት የቃየን እናትና አባት ናቸው። እንደ እግዚአብሄር ተፈጥረው እያለ "እንደ አንዱ" ብቻ የሆኑትና ይሄን መልካም ያንን ክፉ እያሉ መመደብ የጀመሩት፤ እናትና አባቱ ናቸው። ሁሉ ገንዘቡ የሆነው እግዚአብሄር፤ አንዱን ወዶ ሌላውን አይጠላም”

“የእነ አቤል እና ቃየን ታሪክ ጉዳይ ታዲያ ምንድር ነው?”

“ታሪኩማ ሁለት አካላት ለእግዚአብሄር ስላቀረቡት መስዋእት ነው”

“ምንድር ነው የምታወራው ሰውየ? ምን ታወናብደኛለህ?”

“እንግዲህ ከዚህ በላይ ምንም ማለት አልችልም። ሳምንት ቅዳሜ እስክንገናኝ ድረስ አዲዮስ”

ዘጋው። ስልኩን ዘጋብኝ።

“ጆሮዬ ላይ ስልኩን ዘጋብኝ” ብዬ ለጋራ ወዳጃችን አማረርኩ።

“ምን ያናድድሃል? ከሁለት አንደኛው ሌላኛው ጆሮ ላይ ስልኩን ሳይዘጋ የሚጠናቀቅ የስልክ ምልልስ አይቼ አላውቅም” አለኝ።

ያሁኑ ይባስ።

ድጋሚ ደወልኩለት።

“ጥያቄዬን አልመለስክልኝም” አልኩት።

“ምኑን?”

“አቤል ከጠቦቶቹ ጥቂት ለቃየን ሰጥቶ ከቃየን ድንችና ዳጉሳ እንዲሁም ጤፍ አይገበይም ነበር? ገበያ አይታወቅም ነበር?”

“አንተ ደግሞ ስለ ገበያ ታወራለህ። አቤልና ቃየን እኮ ምድር ከተፈጠረች በኋላ፥ የሰው ልጅ ከተፈጠረ በኋላ የተወለዱ ናቸው። የመጀመሪያዎቹ ተወላጆች እኮ ናቸው። አንተ ስለ ገበያ ታወራለህ። ገበያ የተፈጠረው ገና ትናንት አይደለም እንዴ። አዳም ስሚዝ አይደለም እንዴ ስለ ገበያ ጥቅም የፃፈውና የሰውን ልጅ ስለ ነፃ ገበያ ጥቅም ያስተማረው”

ከቅድሙ “ያሁኑ ይባስ” ይልቅ የዚህኛው “ያሁኑ ይባስ” ባሰ።

“እሺ ይሁንልህ። አቤል የአዳም ልጅ አይደለም የሚባለውስ እውነት ነው?”

“ማነው ያለው?”

“አንዳንድ አስተማሪዎች እንደዛ ይላሉ”

“በምን አወቁ?”

“አዳም ሚስቱን ሄዋንን አወቀ ፀነሰችም፥ ቃየንን ወለደች ይላል መፅሃፉ። አቤል ከተገደለ በኋላም አዳም ሚስቱን ሄዋንን አወቀ ፀነሰችም፥ ሴትን ወደለች ይላል መፅሃፉ። ስለ አቤል አወላለድ ሲያወራ ግን ሄዋን አቤልን ወለደች ይላል እንጂ አቤል ከመወለዱ በፊት አዳም ሚስቱን ሄዋንን እንዳወቀና እንደፀነሰች ምንም የሚለው ነገር የለም። ከዚህ ተነስተው አቤል የአዳም ልጅ አይደለም ይላሉ” አልኩት።

“የማወቀው ነገር የለም። ያንተ የልደት ሰርተፊኬት ላይ አባትህ እና እናትህ ተገለፁ እንጂ አባትህ እናትህን እንዳወቃት ተፅፏል?” አለኝ።

“አልተፃፈም”

“ይህ ማለት አንተ ያባትህ ልጅ አይደለህም ማለት ነው?”

“ነኝ እንጂ”

“ታዲያ ምን ታደርቀኛለህ? የአቤልም እንደዛው ነው”

“ታዲያ የቃየን እና የሴት ሰርተፊኬት ላይ አዳም ሄዋንን እንዳወቃት ለምን ተፃፈ?” አልኩት።

“ሰርተፊኬቱ እንደወጣበት ቀበሌ ይለያያላ። አንዳንዶች ይፅፉታል ሌሎቹ አይፅፉትም። በቃ እንደዛ ውሰደው። ለመሆኑ ግን ሄዋን አቤልን ከአዳም ካልወለደችው ከማን ትወልደዋለች ተብሎ ተፈርቶ ነው? ከአትክልተኛው?”

“ምን አውቃለሁ?”

“በል አሁን ቻው ስራ አለብኝ። እንዳንተ ፀጉር የምሰነጥቅበት ትርፍ ጊዜ የለኝም” ብሎ ጆሮዬ ላይ ዘጋብኝ።

#ፉዣዥ
4.0K views02:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-18 08:08:20 ጥላ ለ ሙት

መሪያችን የተናገሩትን ንግግር ሰምቼ ሙት አያቴ መቃብር ላይ ሄጄ ዛፍ ለመትከል አሰብኩ።
ከዛ እንዴት መትከል እንዳለብኝ፥ የሚያስፈልጉኝን መሳሪያዎች አዘጋጅቼ ሲነጋልኝ መጠዋት ለመትከል አስቤ ተኛሁ፤ኤጭ መተኛት አይባል ሙት አያቴ ጋር ጭቅጭቅ ልበለው ንዝንዝ ልበለው ክርክር ወይም ውይይት ይዘን ነበር።
ይመስለኛል ነግቶልኝ ዛፍ ልተክል ሂጄ ነው፤
ግራ ገብቶኝ ቆሚያለሁ መቃብሯን ልፈነቀለው ነው? እንደዛ ካላረኩማ እንዴት መትከል ይቻለኛል እያልኩ እራሴን እየጠየኩ ና ለራሴ መልስ እየሰጠሁ፡ ከዛ መቃብሯን ልፈነቅል አንዴ ድም ሳረገው
-ኧረ ልረፍበት...የሚል ከሩቅ.... ምን ከሩቅ ከመሬት ስር የወጣ ድምፅ ሰማሁ የአያቴ ነበር።
- እንዴ አያቴ..አልኩ እንባ እያቀረርኩ...እዚህ መቃብር መጥቼ ስንቴ ለምኜሽ ነበር ይቅር ብዬሻለሁ እንድትይኝ ለምኜሻለሁ አሁን ግን.... ብዬ ወሬዬን ከመቀጠሌ በፊት አያቴ አቋረጠችኝ
- ኤዲያ ዝም በይልኝ እባክሽ አሁን ልረፍበት ሰው ሞቶ እንኳን አያርፍም እንዴ እናንተ ሀገር.. ነው አዲሱ ስትራቴጂ ነው? መቃብር ብጥበጣውስ በዘር ነው? እ? በዘር ጭፍጨፋ ያልሞቱትን በመቃብ ብጥበጣ ረብሿቸው ብሏቹ ነው?
-ማ? አልኩ ጥያቄዋ ግራ አጋብቶኝ
-ማ? ህ መሪያቹህ አለችኝ ምሬት በተቀላቀለበት ድምፅ
-እንዴ አያቴ መቃብር ቦታ ላይም የእይታ መስኮት አለ እንዴ? ፖርላማ ይቀርባል?
- ሃሃሃሃሃሃ ስኖር እንዲህ ስቄ አቃለሁ ቤቦ? አለችኝ ሳቅ ባፈነው ድምፅ። እህ እህ ለመሆኑ ምን ልታደርጊው ነው መቃብሬን የምፈነቅይው አንቺ?
-ከሄድኩበት ሀሳብ እንደመባነን ብዬ ዛ ዛፍ ተክልልሽና ጥላ እንዲሆንሽ።
መቃብሩን የሚያናጋ ሳቅ ተከተለው ንግግሬን........በዚህ ሳቋ ምክንያት ሌላ መቃብርተኞችም ሳይበጠበጡ አልቀረም።
-አሁንስ አበዛሽው አያቴ ምነው? እንዴ ምን የሚያስቅ አገኘሽ? ከመቼ ጀምሮ ነው በሰው የምታሾፊው?
- መቃብር ላይ ዛፍ መተከል ከጀመረ ጀምሮ?
ቆይ ቆይ ማን ሲል ሰምተሽ ነው በሞቴ(ይች አባባል ዛሬ ትክክለኛ ሰው ላይ ገባች) ምላሼን ለመስማት በጓጓ ድምፅ
- እህ ቅድም የገባሽ መስሎኝ መሪያችን ነዋ!
-ያ ሳቋ ተደገመ፡ ይልቁን ዛፉን ትተሽ እንደዚህ ያለ አይረሴ ቀልድ እየቃረምሽ ብታመጭልኝ እ? ድሮም ዋዘኛ የገዛው እና ብልህ የገዛው እቃ አንዳይነትም ቢሆን አንድ አይነት ጥቅም አይኖረውም።
-የምን ዋዘኛ፣ ብልኸኛ ነው የምትይኝ አያቴ?
- ያኔ አሞኛል ስላቹ ህመሜን እንደቀላል፣ እንደዋዛ፣ እንደቀልድ ባታዩብኝ እዚህ እገኝ ነበር? አዎ ሁሉም ሁሌ ምድር ላይ አይኖርም ግን ልናተርፋቸው የሚቻሉ ሞቶችን ስንሞት አይታቹ አሁን ዛፍ ጥላ ትሉብናላቹ (እልህና ንዴት የተቀላቀለበት ንግግር) እርዳታ አስፈልጎኝ ስማፀናቹ ሳደርሱ አሁን ዛፍ ልተክሉልኝ (ማሰቢያቹ ተናግቷል ተመርመሩት አይነት ናት ይችስ) ነው ሀገሪቱ ሞላችባችሁ እ? የሙቶች መቃብር ላይ ዛፍ እየተከላቹ ቦታ ልታሲዙ ነው? አይዟቹህ ሰው እያለቀላቹ ስለሆነ ቦታ አይታጣም እኮ ። አሁን ሙት መቃብር ላ ዛፍ ተክለሽ ጥላ ነው ጫና የምትፈጥሪው እ? ኧረ ጉድ ነው በኔ አፅም ብስባሽ ዛፉ እንዲለመልም ነው ሃሃሃሃሃ
በይ የሞተ አካል ላይ ዛፍ እየተከልሽ ጥላ ይሁን ከምትይ እየኖሩ የዛፍ ሳይሆን የድጋፍ ጥላ ለሚያስፈልጋቸው ጥላ ሁኚ።አያሰማን የለ አዬ መሞት ደጉ.
-ኧረ መኖር ደጉ ነው ልላት ስል ከእንቅልፌ ባነንኩ እንዲህ ከሆነ መኖር እውነትም መሞት ደግ ነው እሱንም ቀንተን ዛፍ በመትከል ሰበብ ካልበጠበጥናቸው

ምን ማለት ፈልጌ ነው አታነካኩኝ ፖለቲካ አልወድም።

ቤተልሔም ሳሙኤል('ቴጌ ሐበሻዊት)
3.0K views05:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 13:09:44 እልል ያለ የፍቅር ታሪክ !

(በእውቀቱ ስዩም )
አማረችን እወዳታለሁ፤ እሷም ትወደኛለች
ፍቅራችን የታይታ ሳይሆን የታይታኒክ ነው ፤
የዛን ቀን የተቀጣጠርንበት ቦታ ስደርስ፥
“ በጣም አስጠበቅኸኝ” አለችኝ
“ ትራፊክ ፖሊስ ይዞኝ ነው “ ብየ መለስኩላት፤
“ መኪና ሳይኖርህ ትራፊክ እንዴት ሊይዝህ ይችላል? “
“ከተፈቀደው ፍጥነት በላይ ሮጠሀል ብሎ ያዘኝ “
ቢራ አዘዝኩ፤
አማረች ፥ አማሩላ አዘዘች፤
ከውስጥ የሂሩት በቀለ ተወዳጅ ዜማ ይንቆረቆራል፤
“ እንደ መሽኮርመም ይላል ምነው
አፋር አይሉት ሶማሌ ነው “

ቀዝቃዛ ነፋስ መንፈስ ጀመረ፤
ሰማዩ ብልጭ አለ፤
ፊቷ ላይ አማተብኩላት፥
ሰማዩ ማጉረምረምና ማካፋት ጀመረ፤
የመብረቅ መከላከያ የተገጠመለት ጃንጥላየን ዘረጋሁ፤

“ በረደሽ ? “ ስል ጠየኳት፥

ጭንቅላቷን ባዎንታ ነቀነቀች፥
ካቦርቴን ምሽልቅ አድርጌ አወለቅሁና ኮሌታውን አስተካክየ መልሸ ለበስኩት፤

ከፊትለፊታችን የተንጣለለው የአበባ እርሻ የፍቅር ስሜቴን ቀሰቀሰው፤ በአበባ እርሻው ውስጥ ልዩ ልዩ ቀለም እና መአዛ ያላቸው ፌስታሎች ተበትነዋል፤

ከአበባ ርሻው አጠገብ የሚገማሸረው የግንፍሌ ወንዝ አካባቢውን የበለጠ ግርማ ሞገስ ሰጥቶታል፤ ወንዙ ከአቃቂ ወንዝ የተረከበውን የውሻ አስከሬን በመሸኘት ላይ ነበር፤
“የልጅነት ትዝታየ ተቀሰቀሰብኝ “ አልኳት፤

“ አባብልህ አስተኛው “ አለችኝ፤

“ በልጅነቴ አሳ እያጠመድሁ ቤተሰቤን እደግፍ ነበር “ በማለት ቀጠልኩ፤
“ በመረብ ወይስ በመንጠቆ?”

“ በወንጭፍ”

“ እንዴት ተደርጎ?”

“ ከሰፈራችን ብዙ ሳይርቅ አንድ ግዙፍ ዋርካ ነበር ፤ዋርካዋው ስር ጋደም እልና ማንጎራጎር እጀምራለሁ፤ ገዴ የተባለችው አሞራ እየበረረች ትመጣና ዛፉ ላይ ጉብ ብላ ታዳምጠኛለች፤ ለረጅም ጊዜ ስራ ፈትታ ስለምታደምጠኝ ይርባታል፤ ራቡ ሲጠናባት ከዛፉ አጠገብ ካለው ከሚገማሸረው ወንዝ ስር ከሚርመሰመሱ አሶች አንዱን ባፏ ይዛ ወደ ዛፉ ትመለሳለች፤ ወድያው ወንጭፌን አውጥቼ አነጣጥሬ እጥላታለሁ፤ አሳውን ለግብጽ ግምበኞች፥ ወፊቱን ለኩባ ወታደሮች እሸጣለሁ”

ጠጋ አለችኝና ትስመኝ ጀመር፤
አንባቢ ሆይ! ታሪኩን እዚህ ላይ ልጨርሰው አስቤ ነበር፤ ግን ደስታ በራቀው ዘመን በደስታ እሚጠናቀቅ ታሪክ መጻፍ አልፈቅድም፤

ለሁለት ሳአት ያክል ስትሰመኝ ከቆየች በሁዋላ፤ ከንፈሯን ከግንባሬ ላይ አንስታ፥
“መጀመርያ ስታገኘኝ ፥ ምኔ ነው አይንህን የሳበው? “ የሚል ጥያቄ ደቀነችብኝ ፤

“ ሁለመናሽን ወድጄው ነበር ፤ ግን “ ቶ “ የሚለውን ምልክት አንገትሽ ላይ ተነቅሰሽ ሳይ ተረታሁ”

“ እንዴት ?”

“ ምን ብየ ላስረዳሽ ፤ አየሽ “ ቶ” የሚለው ምልክት ለኔ ከጌጥ በላይ ነው፤ በጥንታዊ የኩሽ ህዝቦች ዘንድ “ የሕይወት ቁልፍ ‘የሚል ትርጉም አለው፤ እና ምልክቱን ሳይ “ እቺ ሴት የተዘጉ በሮችን ሁሉ የምትከፍትልህ ቁልፍ ናት የሚል ሃሳብ ብልጭ አለልኝ”

አሜክስ ትንሽ ስታመነታ ከቆየች በሁዋላ እንዲህ አለች፥

“ህምምምም! To be honest with you “ ቶ “ የሚለውን ምልክት የተነቀስኩት “ ቶፊቅን “ ለማስታወስ ነው “

“ቶፊቅ ደሞ ማን አባቱ ነው ?’

“ የመጀመርያ ፍቅረኛየ ነበር”

እሷ የሞተ ፍቅረኛዋን አስባ፥ እኔ የሞተ ፍቅሬን አስቤ መላቀስ ጀመርን፤

Bewuketu Siyum
1.3K views10:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 22:26:09 #ካነበብኩት

የሳይኮሎጂ ፕሮፌሰሩ ወደ ክፍል ገብቶ የእለቱን ወሳኝ ትምርት ለመጀመር ወደ ቦርድ እንደዞረ ፉጨት ሰማ። ወደ ተማሪዎቹ ዞሮ ማን እንዳፏጨ ጠየቀቃቸው። ሁሉም ዝም አሉ። ፕሮፊሰሩ ተረጋግቶ ፣ እስክሪቢቶውን ወደ ኪሱ እየከተተ "የዛሬው ሌክቸር እዚ ላይ ያበቃል" አለና ፈገግ ብሎ "ነገር ግን መጀመሪያ አንድ ታሪክ እነግራችኋለው" አላቸው። ሁሉም በጉጉት መጠበቅ ጀመሩ።
□ □ □
"ትላንት ቤቴ እንቅልፍ ስላስቸገረኝ ዝም ብዬ ተነስቼ ነዳጅ ሞልቼ በዛውም ልናፈስ ብዬ ከመሽ ወጣሁ። ነዳጅ ከሞላሁ በኋላ ከትራፌክ ነጻ የሆነው መንገድ ላይ እየተንሸራሸርኩ እያለ ከሆነ ድግስ ቦታ የወጣች የምትመስል ቆንጂዬ ወጣት አየሁ። መኪናዬን አዙሬ እርዳታ እንደምትፈልግ ጠየኳት" ታክሲ እንዳጣች እና ቤቷ እንዳደርሳት ጠየቀችኝ። ጋቢና ገባች ... ማውራት ጀመርን ... ውበት ብቻ ሳይሆን ባወራነው ርእስ ሁሉ በጣም ስማርት የሆነ ጭንቅላት እንዳላት ከምታወራው ነገር መገመት ቻልኩ። ቤቷ እንደደረስን በጣም ጥሩ ሰው እንደሆንኩ ነገረችኝ። እኔም ጥሩ አስተሳሰብ እንዳላት ነግሬያት በሌላ ጊዜ ተገናኝተን ሻይ ቡና እንድንል ጠየኳት። በሀሳቤም ተስማማች። ዩኒቨርስቲ ፕሮፌሰር እንደሆንኩ አውርተን። ስልክ ተለዋወጥን።
◎ ◎ ◎
እና..ልንለያይ ስንል አንድ ነገር ላስቸግርህ ስትለኝ ምንም ችግር የለውም አልኳት። "ወንድሜ አንተ የምታስተምርበት ዩኒቨርስቲ ውስጥ ተማሪ ነው። በኛ ግንኙነት እንዳይጎዳ ቃል ግባልኝ !" አለችኝ። ...ችግር የለም ብዬ ስሙን ጠየኳት ስሙንም ነገረችኝ።ምናልባት ብዙ ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው ውስጥ ስለሚማሩና ተመሳሳይ ስም ሊኖራቸው ስለሚችል ወንድምሽን እንዴት ልለየው እችላለሁ ? ስል ጠየኳት። እሷም:- ወንድሜ አንድ መለያ ባህሪ አለው። በሱ ታውቀዋለህ። ፉጨት ማፏጨት ያዘወትራል" አለችኝ። ... ከዛ ሁሉም ተማሪ ወደ አፏጨው ልጅ ዞሮ ማየት ጀመረ።
◊ ◊ ◊
ፕሮፌሰሩም :- "የሳይኮሎጂ PHDዬን ተምሬ እንጂ ገዝቼ አይደለም ያገኘውት። ና ውጣ" ብሎ ጆሮውን ይዞ ከክፍል አስወጣው
1.4K viewsedited  19:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ