Get Mystery Box with random crypto!

አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe

የቴሌግራም ቻናል አርማ addiszeybe — አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe
የቴሌግራም ቻናል አርማ addiszeybe — አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe
የሰርጥ አድራሻ: @addiszeybe
ምድቦች: የልጅ እንክብካቤ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 11.27K
የሰርጥ መግለጫ

ለፈጣን መረጃዎች አዲስ ዘይቤ
Twitter : https://twitter.com/AddisZeybe
Facebook : https://bit.ly/2SeU3Ev
Website : https://addiszeybe.com/
YouTube : https://youtube.com/c/AddisZeybe
Instagram : https://bit.ly/3D1tEwC
ስልክ 251954903850
ኢሜይል info@addiszeybe.com

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 93

2022-09-22 17:27:31
#Update
ዘመነ ካሴ ህገ ወጥ ቡድን በማደራጀት እና ኬላ ዘርግቶ ገንዘብ በመሰብሰብ መጠርጠሩ ተገለፀ

መስከረም 12 ቀን 2015 ዓ.ም

(አዲስ ዘይቤ፡ ባህር ዳር) ትላንትና በአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በቁጥጥር ስር የዋለው ዘመነ ካሴ ፍርድ ቤት ቀርቦ የአስር ቀናት ቀጠሮ የተሰጠው ሲሆን ምርመራውን የያዘው የክልሉ ፖሊስ ዘመነ ካሴን "ህገ ወጥ ቡድን በማደራጀት እና "ኬላ ዘርግቶ ገንዘብ በመሰብሰብ" እንዲሁም "በፌስ ቡክ ቅስቀሳ ማድረግ" በሚሉ ወንጀሎች ጠርጥሬዋለሁ በማለት ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።

የዘመነ ካሴ ጠበቆችም እነዚህን ወንጀሎች ለማጣራት በሚል ፖሊስ ላለፉት አራት ወራት ምርመራ ያደረገ መሆኑን እና ሌሎችን መከራከሪያዎችን በማቅረብ የጊዜ ቀጠሮ መስጠት ሳያስፈልግ አርበኛ ዘመነ በዋስ እንዲለቀቅ ጥያቄ አቅርበዋል።

ፍርድ ቤቱ የምርመራ ቡድኑ ያቀረበው ምክንያት በቂ አለመሆኑን ጠቅሶ የ10 ቀናት ጊዜ ቀጠሮ በመስጠት ፖሊስ በእነዚህ ቀናት ውስጥ ምርመራውን እንዲያጠናቅቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል። ዘመነ ካሴም ወደ 2ኛ ጣቢያ ተመልሷል።
@AddisZeybe
758 viewsedited  14:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 17:03:24
#ሰበርዜና
ዘመነ ካሴ ፍርድ ቤት ቀርቦ የ10 ቀናት ቀጠሮ ተሰጠው

መስከረም 12፤ 2015 ዓ.ም.

(አዲስ ዘይቤ፡ አዲስ አበባ) በትላንትናው እለት በአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በቁጥጥር ስር የዋለው ዘመነ ካሴ በከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ከሰዓት ቀረበ።

ፍርድ ቤቱ የ19 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቅዶ ቀጠሮ መሰጠቱን አዲስ ዘይቤ ከባህር ዳርና አካባቢው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሰምታለች።

አዲስ ዘይቤ ጉዳዩን ተከትትላ በዝርዝር ትዘግባለች
740 views14:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 14:59:45 የመሰረታዊ ሸቀጦች ዋጋ ከዕለት ዕለት በአስገራሚ ፍጥነት እየጨመረ ባለበት በዚህ ወቅት፤ በኮንዶም ምርት ላይ ባለተለመደ መልኩ የታየው የዋጋ ጭማሪ አስገራሚ ሆኗል። የአዲስ ዘይቤ ሪፖርተር በአዳማ፣ በደሴ፣ በሐዋሳና በጎንደር ከተሞች ያለውን የኮንዶም እና የወሊድ መቆጣጠሪያ ምርቶችን ዋጋ ተመልክቶ እንዲህ አጠናቅሮታል። ሙሉ ጽሑፉን እነሆ
https://bit.ly/3qZ7hTK
#Ethiopia #Adama #AddisAbaba
@AddisZeybe
785 views11:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 14:32:22
የቴዲ አፍሮ ‘ናዕት’ ሙዚቃ ለአህጉር አቀፍ ሽልማት እጩ ሆነ

መስከረም 12፤ 2014 ዓ.ም.

(አዲስ ዘይቤ፡ አዲስ አበባ) ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) እና ሔዋን ገብረወልድን ጨምሮ ስድስት የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች በየዓመቱ በሚካሄደው የመላው አፍሪካ የሙዚቃ ሽልማት (አፍሪማ) ላይ እጩ መሆናቸው ታወቀ።

ቴዲ አፍሮ ከጥቂት ወራት በፊት የለቀቀው ‘ናዕት‘ የተሰኘው ነጠላ ዜማ በአፍሪማ አዋርድ በአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ የሬጌ እና ዳንስሆል ሙዚቃ ዘርፍ ታጭቷል። ድምፃዊት ቤቲ ጂ ‘አዲስ ሰማይ’ በሚለው ስራዋ እና ሌንጮ ገመቹ ‘ሳግሊ’ በተባለው የኦሮሚኛ ቋንቋ ሙዚቃው በሀገረሰብ ዘርፍ እጩ ሆነዋል።

ድምፃዊት ሔዋን ገብረወልድ ‘ሼሙና’ በሚለው ሙዚቃዋ “በአመቱ ጎልቶ የወጣ ሙዚቀኛ” እና “የምስራቅ አፍሪካ ምርጥ ሴት ሙዚቀኛ” በሚሉ ዘርፎች በእጩነት ቀርባለች።

ድምፃዊ አዲስ ለገሰ ‘እንጃ’ በሚለው ሙዚቃው ምርጥ የአፍሪካ ጃዝ ሙዚቃ እንዲሁም ካስማሰ ‘ሠዋሠው‘ በተሰኘው ሙዚቃው “የመነሳሳት ስሜት በሚፈጥር የሙዚቃ ዘርፍ” የታጨ ሲሆን ሁለቱ ድምፃውያን በየግላቸው የምስራቅ አፍሪካ ምርጥ ወንድ ሙዚቀኛ ለመሆንም ይፎካከራሉ።

ለእጩ ድምፃውያን በኦንላይን ድምፅ መስጠት የሚቻልበት ስርዓት ከእሁድ መስከረም 15 የሚጀመር ይሆናል።
___
ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የአዲስ ዘይቤ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ።
Twitter : https://bit.ly/3uQBnvj
Facebook : https://bit.ly/2SeU3Ev
Telegram : https://bit.ly/3JX93LY
Website : https://bit.ly/3JOUavm
YouTube : https://bit.ly/37rIyBa
771 viewsedited  11:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 12:17:57
የኮማንደር ዋጋዉ ታረቀኝ ስርዓተ ቀብር በወታደራዊ ስነ-ስርዓት ተፈፀመ

መስከረም 12፤ 2015 ዓ.ም.

(አዲስ ዘይቤ፡ ባህር ዳር) ትላንት ምሽት በግለሰብ ተተኩሶባቸው የተገደሉት የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ዋና ክፍል ኀላፊ ኮማንደር ዋጋዉ ታረቀኝ የቀብር ስነ-ስርዓት ተፈፀመ።

ተጠርጣሪን በቁጥጥር ስር ለማዋል በስራ ላይ በነበረበት ወቅት በተፈጠረ የተኩስ ልውውጥ ነው ኮማንደር ዋጋው ትላንት ሌሊት 6 ሰዓት አካባቢ ነበር የተገደሉት።

የኮማንደር ዋጋዉ ታረቀኝ ስርዓተ ቀብር በወታደራዊ ስነ-ስርዓት ዛሬ መስከረም 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በአፄ ቴዎድሮስ ክፍለ ከተማ በአየር ጤና ቀበሌ ተፈጽሟል። በቀብር ስነ-ስርዓቱ ላይ የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶክተር ድረስ ሳህሉ፣ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደጀኔ ልመንህ እና ሌሎች አመራሮችም ተገኝተዋል።
___
ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የአዲስ ዘይቤ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ።
Twitter : https://bit.ly/3uQBnvj
Facebook : https://bit.ly/2SeU3Ev
Telegram : https://bit.ly/3JX93LY
Website : https://bit.ly/3JOUavm
YouTube : https://bit.ly/37rIyBa
803 views09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-11 16:01:17 ልዩ የበዓል ቆይታ ከሀቅቼክ ጋር
ሙሉ ቪድዮውን ለመመልከት ሊንኩን ይጫኑ


269 views13:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 17:17:39 በድጋሜ ካገረሸው ጦርነት ጋር በተያያዘ ህወሓት ትላንት ባወጣው መግለጫ የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት በኃይል ጣልቃ እንዲገባ መጠየቁና የተኩስ አቁም ኃሳብ ማቅረቡ ይታወሳል።
@AddisZeybe
682 views14:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 17:17:02
ከጦርነቱ ጋር ተያይዞ በባለስልጣናትና አመራሮች ላይ የተጣለው ማዕቀብ እንዲቀጥል ፕሬዝዳንት ባይደን ወሰኑ

ጳጉሜ 4፤ 2014 ዓ.ም.

(አዲስ ዘይቤ፡ አዲስ አበባ) ከአንድ አመት በፊት መስከረም 2014 ዓ.ም ላይ ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር በተያያዘ በጦርነቱ ለተፈጠሩ ችግሮች ተጠያቂ ናቸው ባላቸው የኢትዮጵያና የኤርትራ ባለስልጣናት ላይ በአሜሪካ መንግስት የተጣለው ማዕቀብ እንዲቀጥል መወሰናቸውን ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስታወቁ።

ፕሬዝዳንቱ በመግለጫቸው እንዳሉት በሰሜን ኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ጦርነት ለአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነትና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ላይ እጅግ ከፍተኛ አደጋ መፍጠር በመቀጠሉ የማዕቀብ ውሳኔው ፀንቶ ለአንድ አመት እንዲቀጥል ወስነዋል።

የዛሬ አመት በተላለፈውና Executive Order 14046 የተባለው የማዕቀብ ውሳኔ በሰሜኑ ጦርነት ለተፈጠሩት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ የሰብአዊ እርዳታ ፍሰት መሰናከሎች፣ የሰላማዊ ዜጎች ጥቃትና መፈናቀሎች እንዲሁም የኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋት ላይ አደጋ በመፍጠር የአሜሪካ መንግስት ተጠያቂ ናቸው ባላቸው የኢትዮጵያና የኤርትራ ባለስልጣናት ላይ የተጣለ ማዕቀብ ነው።

በዚህም መሰረት ማዕቀቡ የሚመለከታቸው የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግስታትና ገዢ ፓርቲዎቻቸው፣ የአማራ ክልላዊ መንግስት እና የህወሓት ባለስልጣናት፣ አመራሮች፣ የቀድሞ አመራሮችና ቤተሰቦች እንደሆኑ በጊዜው የተላለፈው ውሳኔ ያስረዳል።

በማዕቀቡ ከተጣሉ እገዳዎች መካከል ወደ አሜሪካ ግዛት የመግባት፣ በአሜሪካ የሚደረጉ የገንዘብና ንብረት እንቅስቃሴ፣ ግብይት፣ ብድርና የፋይናንስ ድጎማ ክልከላዎች ይገኙበታል።

ውሳኔው ከተላለፈ አንድ አመት ቢሆነውም የትኞቹ ባለስልጣናትና አመራሮች ላይ ተግባራዊ እንደሚደረግ በስም የተገለፀ ነገር የለም።
671 views14:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 12:03:17 ኢትዮጵያ ከቀረው ዓለም ተለይታ ባላት የራሷ ብቻ የሆነ የ13 ወር የዘመን መቁጠሪያ ቀመር መሰረት በአመቱ የመጨረሻዎቹ ቀናት የአዲስ ዘይቤ ሪፖርተሮች በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች ያለውን የአመት በዓል ገበያ ቃኝተዋል። በሁሉም ገበያዎች ልጓም አልባው የዋጋ ንረት የቀጠለበት ሁኔታ እንዳለ ሆኖ ሁሉም እንደአቅሙ በዓሉን ለማሳለፍ ሽር ጉድ ማለቱን ቀጥሏል። ሙሉ ጽሑፉን እነሆ
https://bit.ly/3DeOo6E
#AddisAbaba #DireDawa #Gondar #Hawassa #Dessie #Adama #Bahirdar #NewYear
708 viewsedited  09:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 21:23:54 In a letter addressed to the Security Council, TPLF appealed for the Council’s intervention towards peace. It is also stated in the letter that the government unleashed a full-scale and highly coordinated offensive on Tigray and peace will be the lasting solution. Read more
https://bit.ly/3TYthLF
#Ethiopia #AddisAbaba #Tigray
@AddisZeybe
810 viewsedited  18:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ