Get Mystery Box with random crypto!

አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe

የቴሌግራም ቻናል አርማ addiszeybe — አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe
የቴሌግራም ቻናል አርማ addiszeybe — አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe
የሰርጥ አድራሻ: @addiszeybe
ምድቦች: የልጅ እንክብካቤ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 11.27K
የሰርጥ መግለጫ

ለፈጣን መረጃዎች አዲስ ዘይቤ
Twitter : https://twitter.com/AddisZeybe
Facebook : https://bit.ly/2SeU3Ev
Website : https://addiszeybe.com/
YouTube : https://youtube.com/c/AddisZeybe
Instagram : https://bit.ly/3D1tEwC
ስልክ 251954903850
ኢሜይል info@addiszeybe.com

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 94

2022-09-09 15:25:09 በበዓል ወቅቶች በከተሞች የሚዘጋጁት የባዛር ገበያዎች ዋና አላማ በርካታና የተለያዩ እቃዎችንና ሸቀጦችን በቅናሽ ዋጋ በአንድ ስፍራ ለሸማቹ ማቅረብ እንደሆነ ይታሰባል። ነገር ግን በዘንድሮዎቹ ባዛሮች የዋጋ ቅናሽ አለ በሚለው ላይ ሁሉም ሸማቾች አይስማሙም። በተለያዩ ከተሞች ያሉትን ባዛሮች የሚጎበኙት ሰዎች ቁጥርም እንዳለፉት አመታት እንዳልሆነ ታዝበናል። ለዚህም የዋጋ ግሽበቱ የደረሰበት ደረጃ እና ሃገሪቷ ያለችበት የፀጥታ ሁኔታ እንደ ምክንያት ይነሳሉ። የአዲስ ዘይቤ ሪፖርተሮች ይሄንን ዘገባ አዘጋጅተዋል
https://bit.ly/3AY8TBI
#Ethiopia #AddisAbaba #Bahirdar #Hawassa #Adama
@AddisZeybe
883 views12:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-09 14:36:37
ህወሓት ለፀጥታው ምክር ቤት የተኩስ አቁም ኃሳብ አቀረበ

ጳጉሜ 4፤ 2014 ዓ.ም.

(አዲስ ዘይቤ፡ አዲስ አበባ) የህወሓት ሊቀ መንበር አቶ ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ለተባበሩት መንግስታት የፀጥታ ምክር ቤት በፃፉት ደብዳቤ የሰላም እና ሰብዓዊ መብቶች መረጋገጥ በሚፈጥር ሁኔታ በቅድመ ሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የተኩስ አቁም ኃሳብ አቀረቡ።

ለቀመንበሩ በደብዳቤያቸው እንዳሰፈሩት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እና የኤርትራ መከላከያ ሰራዊት በጋራ ሆነው ካለፈው ዓመት አስከፊ በሆነ ደረጃ በትግራይ የተቀናጀ ጥቃት እየፈፀሙ ነው ብለዋል። በአሁኑ ወቅትም ምንም ዓይነት የሰብዓዊ እርዳታ ተግባራት መቋረጣቸውንም አስገንዝበዋል።

“የተመድ የፀጥታ ምክር ቤት ጦርነቱን ለማስቆም ጫና በማድረግ የኤርትራ ሰራዊት ከኢትዮጵያና ከትግራይ መሬት እንዲወጣ፣ ከበባው እንዲቆምና መሰረታዊ አገልግሎቶች እንዲጀመሩ፣ በምክር ቤቱ ስር የሰላም ድርድር እንዲጀመር፣ ያልተገደበ ሰብዓዊ እርዳታ እንዲቀርብ ማድረግ ይገባዋል” በማለት ለተኩስ አቁሙ ያስቀመጧቸውን ቅድመ ሁኔታዎች አቶ ደብረፅዮን በደብዳቤያቸው አስፍረዋል።

የሰላም ድርድሩን በሚመለከት የፀጥታው ምክር ቤት በሂደቱ ላይ ሚና እንዲኖረው እና ያንን የማስፈፀም አቅም እንዳለው እምነታቸውን ገልፀዋል። ሊቀ መንበሩ ከዚህ ቀደም ለድርድር በቅድመ ሁኔታ ህወሓት ያስቀመጣቸው ነጥቦች አሁንም እንዲከበሩ ጥሪ አቅርቧል።

ለአምስት ወራት ለሰባዊ እርዳታ ሲባል የተደረገው የተኩስ አቁም እንዲፈርስና ለሁለተኛ ዙር ለተጀመረው ውጊያ መነሻ የህወሓት ትንኮሳ መሆኑን የፌዴራል መንግስት መግለፁ የሚታወስ ነው።
@AddisZeybe
869 viewsedited  11:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 21:08:57
የእንግሊዟ ንግስት ኤልሳቤት ከዚህ አለም በሞት ተለዩ

ጷጉሜ 3፤ 2014 ዓ.ም

(አዲስ ዘይቤ፡ አዲስ አበባ) ለ 70 አመታት የእንግሊዝ ንግስት ሆና ያገለገሉት ንግስት ኤልሳቤት በ96 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት መለየታቸው ታወቀ።

የእንግሊዝ ንግስት ሆነው እ.አ.አ በ1952 የተሾሙት ንግስት ኤልሳቤት ሃገሪቱን ለረዥም ጊዜ ካስተዳደሩ ንጉሳዊ ቤተሰቦች ቀዳሚው ናቸው። የጤናቸው ሁኔታ በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ በተነገረው ንግስት የስኮትላንድ መኖሪያ ከትላንት ጀምሮ ቤተሰቦቻቸው ተሰባስበው ሁኔታቸውን ሲከታተሉ ቆይተዋል።

የንግስቲቷን ሞት ተከትሎ የቀድሞው የዌልስ ልዑል የነበረው ታላቁ ልጇ ልዑል ቻርልስ ንጉስ በመሆን ሃገሪቷን የሚያስተዳድር ይሆናል።

ንግስት ኤልሳቤት በትረ ስልጣኑን ከተረከቡ ጊዜ አንስቶ ከዊንስተን ቸርችል ጀምሮ 15 ጠቅላይ ሚኒስትሮች እንግሊዝን አገልግለዋል።

ሁኔታቸውን በቤኪንግሃም ቤተ መንግስት ሲከታተል የነበረው ህዝብ የንግስቲቱን ማረፍ እንደሰማ የተሰማውን ኃዘን በመግለፅ ላይ ይገኛል። ንግስት ኤልሳቤት እ.አ.አ በ1926 ነበር በሜይፌይር ለንደን የተወለዱት።
@AddisZeybe
953 viewsedited  18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 16:02:46 በአማራ ክልል በ2014 ዓ.ም በደረሱ የትራፊክ አደጋዎች 853 ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ 1,501 ሰዎች ደግሞ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል። የክልሉ ትራስፖርት ባለስልጣን መስሪያ ቤት የዘንድሮው አደጋ ከአምናው ጋር ሲነፃፀር እንደቀነሰና ለዚህም በክልሉ በነበረው ጦርነት የትራፊክ እንቅስቃሴው ደካማ መሆኑ አስተዋፅዖ አድርጓል ይላል። ሙሉ ጽሑፉን እነሆ
https://bit.ly/3RNlUEZ
#Ethiopia #Bahirdar
@AddisZeybe
938 views13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 13:23:44
እርሶዎ ምን ያስባሉ?
______
ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የአዲስ ዘይቤ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ።
Twitter : https://bit.ly/3uQBnvj
Facebook : https://bit.ly/2SeU3Ev
Telegram : https://bit.ly/3JX93LY
Website : https://bit.ly/3JOUavm
YouTube : https://bit.ly/37rIyBa
940 viewsedited  10:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 11:10:36
ለቤተሰቦቻቸው እና ለመላው አድናቂዎቻቸው አዲስ ዘይቤ መፅናናትን ይመኛል
____
ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የአዲስ ዘይቤ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ።
Twitter : https://bit.ly/3uQBnvj
Facebook : https://bit.ly/2SeU3Ev
Telegram : https://bit.ly/3JX93LY
Website : https://bit.ly/3JOUavm
YouTube : https://bit.ly/37rIyBa
908 viewsedited  08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 10:13:27 Channel photo updated
07:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 19:00:08 OrCam MyEye distributed by the Office of the First Lady-Ethiopia has brought new hope for Ethiopian blind people who have immense limitations in their day-to-day life. Addis Zeybe’s Reporter, who is the beneficiary of the device, has prepared a brief review of the device.
https://bit.ly/3RMVxzb
#Ethiopia #AddisAbaba
@AddisZeybe
327 views16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 15:35:33
ኦነግ ሸኔ በአርጆ ደዴሳ ስኳር ፋብሪካ ላይ ጥቃት ማድረሱ ተነገረ

ጷጉሜ 2፤ 2014 ዓ.ም

(አዲስ ዘይቤ፡ አዲስ አበባ) በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአሸባሪነት የተፈረጀው እና መንግስት “ሸኔ” እያለ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን ነሐሴ 24 ቀን 2014 ዓ.ም በአርጆ ዴደሳ ስኳር ፋብሪካ ጥቃት መፈፀሙ ተሰማ።

እራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው ቡድን በምሥራቅ ወለጋ ዞን የሚገኘውን ፋብሪካ ለሰዓታት ተቆጣጥሮ ከቆየ በኋላ ንብረት ማውደሙን እና ዘረፋ መፈጸሙን የስኳር ኮርፖሬሽኑ የሕዝብ ግንኙነት እና ተሳትፎ ዋና ክፍል ኃላፊ ረታ ደመቀ ተናግረዋል ሲል ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል።

ታጣቂው ቡድን ስድስት የአርጆ ደዴሳ ተሸከርካሪዎችን ጨምሮ ሌሎች ተሽከርካሪዎችንም ያቃጠለ ሲሆን የሠራተኞችን ሞባይልና ጫማ እንዲሁም ቁጥራቸ የማይታወቅ የድርጅቱን ላፕቶፕ እና ዴስክቶፕ ኮምፒዩተሮች ዘርፈዋል ነው የተባለው።

የቡድኑ ቃል አቀባይ ኦዳ ተርቢ በትዊተር ገፃቸው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አባላት በስኳር ፋብሪካው እርምጃ መውሰዳቸውን ተከትሎ በቅጥር ግቢ ውስጥ የነበሩ የመንግሥት ኃይሎች አካባቢውን ጥለው ወደ ደቡብ ሸሽተዋል ሲሉም አስታውቀው ነበር።
_______
ለወቅታዊ እና ለፈጣን መረጃዎች የአዲስ ዘይቤ የማህበራዊ ሚዲያዎችን ይቀላቀሉ።
Twitter : https://bit.ly/3uQBnvj
Facebook : https://bit.ly/2SeU3Ev
Telegram : https://bit.ly/3JX93LY
Website : https://bit.ly/3JOUavm
YouTube : https://bit.ly/37rIyBa
579 views12:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 15:23:59 የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች በበኩላቸው ደንበኞቻቸው ከአንድ ወር በላይ በስር መቆየታቸውን ገልጸው የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ጠይቀዋል። ከሳሽ ዓቃቤ ህግ የተጠረጠሩበት በከባድ ሙስና ወንጀል የሚያስከስስ መሆኑን ጠቅሶ ዋስትና ጥያቄያቸውን ተቃውሟል።

ጉዳያቸውን የተመለከተው የጊዜ ቀጠሮ ችሎት የዓቃቤ ህግ ክስ መመስረቻ ጊዜ ላይ መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለከሰዓት በኋላ ቀጥሯል።

በተመሳሳይ ሌሎች በዚሁ ጉዳይ የተጠረጠሩት የአዲስ አበባ ከተማ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉቀን ሀብቱ፣ የሶፍትዌር ባለሙያ የነበረው አቶ አሚ አምባዬ፣ የዳታ ቤዝ ሰራተኛ አቶ ዮናስ ወ/ጊዮርጊስ እና አብረኸት ልዑልን በሚመለከት ጉዳያቸው በፖሊስ ምርመራ እየተደረገ ይገኛል።
@AddisZeybe
490 views12:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ