Get Mystery Box with random crypto!

አቢሲኒያ - Times

የቴሌግራም ቻናል አርማ abisiniya_times — አቢሲኒያ - Times
የቴሌግራም ቻናል አርማ abisiniya_times — አቢሲኒያ - Times
የሰርጥ አድራሻ: @abisiniya_times
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 38.51K
የሰርጥ መግለጫ

Description
• ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ፣
•በአለማችን የተከናወኑ አስደናቂ ክስተቶች፣
•የስፖርት እና መዝናኛ መረጃዎች፣
•24 ሰዓት ትኩስ እና አዳዲስ መረጃ ያገኛሉ፣
•እንዲሁም ጠቅላላ እውቀት፣
ለማንኛውም መረጃ፦
#ለአስተማማኝ የመረጃ ምንጭ
https://t.me/abisiniya_times

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 16

2022-11-01 22:05:26 ተሰውረው ያልተሰወሩ የሁለት ካርታ ሐቂቆች!

ይህን ካርታ ያገኘሁት ከየት ነው? ከመጽሐፍ፡፡ ከAlan McCrae Moorehead መፅሐፍ ነው፡፡ በ1956 ዓመተ ምህረት ላይ ካሳተመው መጽሐፉ፡፡ አለን ሙርሄድ ማነው? ትውልዱ ከአውስትራሊያ የሚመዘዝና የተማረ፣ በእንግሊዝ የኖረና የሞተ፣ ባካበተ ልምዱና ተመራምሮ ለህትመት ባበቃቸው አያሌ የጦርነት ታሪኮች፣ በተለይም እጅግ በታወቀባቸው ሁለት ተከታታይ መጽሐፎቹ የታወቀ ነው፡፡

የመጀመሪያው መፅሐፉ ‹‹The White Nile›› የተሰኘው ነው፡፡ አስከትሎ ያሳተመው ‹‹The Blue Nile›› የተሰኘው መጽሐፍ ስለራሳችን የአባይ ወንዝና በእርሱ ዙሪያ የተደረጉ አያሌ ጦርነቶችን ከተርኪሽ ኢምፓየር እስከ ፈረንሣዩ ናፖሊዮን የግብጽ ወረራን ተከትሎ ከእንግሊዝ ጋር የተደረገውን የጦፈ ውጊያ ይተርካል፡፡

ከዚያም አልፎ በሁለተኛው መጽሐፉ፣ የእንግሊዙን (የህንዱን እዝ) ጄነራል ናፒየርን ወደ ሀበሻ ምድር የተደረገ የጦርነት ጉዞ ከመነሻው እስከ ፍጻሜው በሚገርም ዝርዝር ማስረጃዎች እያስደገፈ ለዓለም ያስነበበ ብርቱ የታሪክ ተመራማሪና፣ ጉምቱ ፀሐፊ ነው፡፡ የጥንት ታሪኮቹን ልክ አሁን ያሉ አስመስሎ ነው የሚተርካቸው፡፡ ደግሞ የዕውቀት ሀብቱ፡፡ የመረጃው ብዛቱ፡፡ ጉድ ነው፡፡

እነርሱ መቼም ሰው ማክበር ያውቁበታል፡፡ ለዚህ ታላቅ አበርክቶቱ፣ አለን ሙርሄደ የብሪትሽ ኢምፓየርን እጅግ ከፍተኛውን ‹‹ኦርደር›› ከንግሥቲቱ እጅ (እንደ ፕ/ር ሪቻርድ ፓንከርስት)፣ እንዲሁም የአውስትራሊያን ከፍተኛውን ‹‹ኦርደር›› ጨምሮ፣ በርካታ የዕውቅና ሽልማቶችን ተቀብሏል፡፡ በአለን ሙርሄድ የህይወት ታሪክ ፊልም ተሠርቶለታል፡፡ መጽሐፍ ተፅፎለታል፡፡

ሙርሄድ የናፒየርን የአቢሲንያ ዘመቻ ሲጽፍ ኢትዮጵያ ድረስ መጥቶ፣ ግብጽን፣ ህንድን፣ ሱዳንን፣ የብሪትሽ ሙዝየሞችንና የዘማቾችን የግል ማስታወሻዎች አስሶ ነው፡፡ በመጨረሻ የዛሬ 40 ዓመት ገደማ በ73 ዓመት ዕድሜው እዚያው እንግሊዝ ውስጥ በሞት ተለየ፡፡ የዚህን ሰው በተለይ በሁለተኛ መጽሐፉ በአባይና በአፄ ቴዎድሮስ የመቅደላ ታሪክ ዙሪያ የጻፋቸውን ታሪኮች ወደፊት ወዳገርኛ የሚተረጉመው ቢገኝና ትውልድ ቢማርበት እያልኩ አስባለሁ፡፡

ታዲያ ይህን ሁሉ መግቢያ ስለ አለን ሙርሄድ ጻፍኩ፡፡ ለዛሬ ብዙም የምጨምረው የለኝም፡፡ ግን የታሪክ ፀሐፊው Alan Moorehead የመጽሐፉን ገጽ በሚያክል መጠን እንዲሆኑ፣ ሶስት ጊዜ በታጠፉ በብሪትሽ ካርቶግራፈሮች የተሠሩ ሁለት ታሪካዊ ካርታዎችን በመጽሐፉ ሸጉጦልን ነው ያለፈው፡፡

ይህ ከዚህ ጽሑፍ ጋር ፎቶ አንስቼ ያቀረብኩት ሁለተኛው ካርታው ነው፡፡ የናፒየርን የዘመቻ መስመር - ከዙላ ወደብ እስከ መቅደላ አፋፍ ድረስ ያለውን በዚህ ታሪካዊ ካርታ ላይ ሰፍሮ እናገኛለን፡፡ ግን አሁን ከዚህ ካርታ ላይ እጅግ የመሰጠኝ ነገር የናፒየር የዘመቻ መስመር አይደለም፡፡ በወቅቱ የአማራና የትግሬ መካለያ ተደርጎ በካርታው የሰፈረው የተከዜ ወንዝ የመሆኑ ነገር ነው ቀልቤን የሳበው፡፡

ይህን ካርታው የሚያመለክተውን ታሪካዊ ሀቅ፣ ቢያንስ ከዚህ ቀደም ጨምሮ ከሶስተኛ መጽሐፍ ላይ አግኝቼ ሳቀርበው ነው፡፡ በነዚህ ብቻ ሳይሆን፣ በብዙዎችም ሌሎች ቀደምት ሥራዎች ውስጥ ተደጋግሞ የምናገኘው የታሪክ ሀቅ ነው ይህ፡፡ የአማራና የትግሬ ታሪካዊ የአስተዳደር ወሰን፣ ‹‹ከተከዜ መልስ›› እና ‹‹ከተከዜ ማዶ›› እየተባለ፣ የተከዜን ወንዝ ተከትሎ እንደተሠራ - ተብሎ ተብሎ የተሰለቸ ጉዳይ ነው፡፡

እነዚህን እውነቶች የማቀርበው ለምንድነው? በእውነት ላይ የተመሠረተ፣ ሀቀኛ ንግግርና ድርድር እንዲኖር ከመመኘት ነው፡፡ እውነትን በማደባበስ ሳይሆን፣ በእውነት ላይ ቆሞ መወያየት፣ ከዚያ ስለመልካም ጉርብትና፣ ስለ ቀጣዩ የጋራ ኑሮና የህዝቦች ትስስር ከልብ ተማምኖ፣ በሰከነ መንፈስ ተወያይቶ ብዙ አማራጮች ያሉት መፍትሄ ማበጀት ይቻላል፡፡ የሚል እምነት ስላለኝ ነው፡፡

ከሰው ጋር ትጣላለህ፡፡ ከፈለግክ ከእግዜርህም ጋር ትጣላለህ፡፡ ሰው ከራሱም ጋር ይጣላል፡፡ ከእውነት ጋር ግን አትጣላም፡፡ እውነት ነው መውጪያችን፡፡ እውነት ነው መዳኛችን፡፡ በአንድ ወቅት የዶክተር አረጋዊ በርሄን የዶክትሬት ጥናት በአስረጅነት እንደጠቀስኩት፣ ብዙ ይህን ካርታውን የሚያመለክተውን እውነት አምነው የሚቀበሉ፣ ከእውነት ጋር እርቅ የፈጸሙ ሰሜነኞች አሉ፡፡ እልህ በእውነት አስታራቂነት መብረድ አለበት፡፡

እውነቱ ይህ ከሆነ፣ ለህዝቦቻችን እንዲጠቅም ምን ብናደርግ ይሻላል? እኔ ይሄ ስጋት አለብኝ? ካንተ ይሄንን እፈልጋለሁ፣ እኛ ይሄን ጥቅም ማግኘት እንሻለን፣ ይሄኛው ለወደፊቱ ሁላችንንም ይጠቅማል፣ ያ በእንዲህ ያለ መልኩ ቢኬድበት፣ ... እያሉ በእውነት ላይ ቆሞ መደራደርም ሆነ፣ ስለመጪው የጋራ ሀገርና የህዝብ ትስስር መወያየት፣ ነገርን ዳግም ላያቆጠቁጥ ያደርቀዋል፡፡

አለበለዚያ በድርቅና የተነሳ፣ ስንት ተዓምር ሊሠራ የሚችል ትኩስ ወጣት ነው የሚያልቀው፡፡ ሌላ ትርፍ የለውም፡፡ በድርቀት የሚደርቅ ጠብ የለም፡፡ አበቃ ሲባል ዳግም እያቆጠቆጠ የሚነሳ የእርስበርስ መናጨትና የዜጋ እልቂት ብቻ ነው ትርፉ፡፡

መጽሐፉን ለጊዜው ትቼ፣ በካርታው መነሻነት ይህን ያህል ካልኩ፣ ከዚህ ታሪካዊ ካርታ ላይ ጥያቄ ያጫረብኝን ሌላውን ተጨማሪ ነገር አንስቼ ላብቃ፡፡ የናፒየር ካርታ ላይ ‹‹AMHARA›› ብሎ ከተከዜ መለስ ያሰፈረበት ሥፍራ አለ፡፡ ‹‹ጎንደር›› በሚለው ፋንታ ‹‹አማራ›› ብሎ እናገኘዋለን፡፡ እና በወቅቱ ‹‹አማራ›› ተብሎ የሚጠራው ጎንደር ብቻ ነበር ማለት ነው? ምክንያቱም በዚህ ካርታ ‹‹ጎንደር›› ተብሎ የተጠቀሰ ነገር የምናገኘው ጎንደር ከተማዋን ነው፡፡ እንጂ ጎንደርን አጠቃላዩን አይደለም፡፡

በመተማ በኩል ያለው የቴዎድሮስ ሀገር ጎንደር በዚህ ካርታ ‹‹ቋራ›› በሚል ተቀምጧል፡፡ በእርግጥ ያ አካባቢ የጎንደር አካል ይሁን እንጂ በስም ግን እስካሁንም ቋራ እየተባለ የሚጠራ ይመስለኛል፡፡ ከተሳሳትኩ እታረማለሁ፡፡ ይህ ካርታ ‹‹DAMOT›› ይለናል፡፡ ‹‹GOJAM›› ይላል፡፡ ‹‹SHOA››ን ያስቀምጣል፡፡ ከተከዜ ማዶ ያለውን ‹‹TIGRĔ››ን ያሳያል፡፡

ይህ የካርታው አገላለጽ ጥያቄን ያጫረብኝ፣ ከዚህ ቀደም አካፍዬው የነበረውንና፣ ‹‹WAX & GOLD...›› በሚል በ1950ዎቹ ባሳተመው መጽሐፉ የፊት የውስጥ ገጽ ላይ የአማራና የትግራይ ወሰን ከተከዜ ወዲህና ወዲያ እንደሆነ በካርታው አስፍሮ ሲያበቃ፣ የሑመራ-ወልቃይት-ፀገዴ-ፀለምትን ሥፍራ በካርታው ላይ በሰንጠረዥ ለይቶ በማመልከት፣ እነዚህ ስፍራዎች ትግርኛ ተናጋሪ ያለባቸው ቦታዎች ስለሆኑ፣ ከትግሬ ጋር ሊከለሉ ይገባል የሚል ብይን ሰጥቶ ያለፈው - የዶ/ር Donald Nathan Levine ነገር ሁልጊዜ ስለሚመጣብኝ ነው፡፡

እስካሁን ይህን የዶናልድ ሌቪንን መጽሐፍ በጥልቀት ያሄሰው ሰው ባያጋጥመኝም፣ ነገር ግን ሌቪን ‹‹አማራ›› የሚባል የሸዋውን፣ የጎንደሩን፣ የጎጃሙን ግዛትና ህዝብ ያጠቃለለ የጋራ የገዢ ነገሥታት ማንነት እንዳለ ለማሳየት የተሟሟተውን ነገር - አሁን ይህን የአለን ሙርሄድን የናፒየር ካርታ እያየሁ ደጋግሞ አቃጨለብኝ፡፡ ህወሃት ከመመሥረቷ በፊት ይህን ከተከዜ ወዲህ ያለውን ጭምር የትግራይ ሊሆን ይገባል የሚል ሀሳብ በመጽሐፉ አትሞ ያቀበላቸው ዶናልድ ሌቪን ነው፡፡
2.1K views19:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 18:49:59 “ወንበዴውን ቀይ ባሕር እንጨምረዋለን!”

የኢሠፓ ሰዎች መፈክር ይወዱ ነበር፡፡ በወቅቱ ብዙዎች ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለማርያም የሚናገሩትን እያስተጋቡ የሰሜኑን ጦርነት አቃለው በማቅረብ “ወንበዴውን ቀይ ባሕር እንጨምረዋለን!” እያሉ አገሪቱን ለአማጺያኑ አስረክበዋታል፡፡ ሊቀመንበር መንግሥቱ ሁሉን-አወቅ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የሚሊተሪ ስትራቴጂስት ሆነው ይታዩ ስለነበር፥ በቅርቡ አቶ ፋሲካ ሲደልል ባሳተሙት መጽሐፍ እንደገለጹት፥ ደፍሮ የሚሞግታቸው አልነበረም፡፡ ኢትዮጵያን ውድ ዋጋ ያስከፈለ የፖለቲካ ሥርዓት ነበር፡- የደርጉ የአገዛዝ ሥርዓት፡፡

ዛሬም ጠላትን በበቂ ሁኔታ ያለመገንዘብ አደጋ ገጥሞናል፡፡ ትናንትና “ዱቄት ሆኗል፤ ተኗል” የተባለው ቡድን ምን ያህል ዋጋ እንዳስከፈለን እናውቃለን፡፡ ሆኖም ዛሬም የጠላትን አቋምና አቅም በበቂ ሁኔታ አልተረዳነውም፡፡ ዛሬም የጦርነቱን መሠረታዊ ባሕርይ በበቂ ሁኔታ አልተገነዘብነውም፡፡ በመሆኑም ዛሬም እንደ ትናንቱ ውድ ዋጋ እየከፈልን እንገኛለን፡፡ ራስን መፈተሽ ያስፈልጋል።

ወያኔና አጋሮቹ የሚያካሂዱት ጦርነት ልዩ ባሕርይ ያለው መሆኑ ሊገባን ይገባል፡፡ ወያኔ ጦርነቱን ሕዝባዊ ማድረጉን፣ በዚህም ከፍተኛ ውጤት ያገኘበት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ዋነኛው የወያኔ ተዋጊ ኃይል ከየግንባሩ ተበታተነ ማለት የመዋጋት አቅሙና አቋሙ አበቃለት ማለት እንዳልሆነ ከመጀመሪያው ጦርነት መማር ያስፈልጋል፡፡

የወያኔ ታጣቂ ልክ እንደ አልሻባብ ሚሊሻ ልብሱን እየቀየረ በየቤቱና በየአካባቢው ከተሰራጨ በኋላ በኢትዮጵያ ጦር ላይ የደፈጣ ጥቃት እየከፈተ ጉዳት እንደሚያደርስ ግልጽ ነው፡፡ ወያኔ ቤተ እምነቶችን፣ የአርሶ አደር መኖሪያ ቤቶችን፣ የሕክምናና የትምህርት ተቋማትን ወዘተ. እንደ መደበቂያ ይጠቀማል፡፡

ከመፈክሩና ጭብጨባው ቀነስ አድርጎ የጠላትን አቅም በሚመጥን ሁኔታ መዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡ ጦርነቱ ልዩ ባሕርይ ያለው በመሆኑ መዘናጋትና ጥቃቅን ስህተቶችን መፈፀም ውድ ዋጋ ያስከፍላል፡፡

ከመፈክሩ ቀነስ፤ ከዝግጅቱ ጠበቅ!

(በሪሁን አዳነ)
@abisiniya_times
3.2K views15:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 11:50:32 ወያኔዎች በትግላቸው ይቀጥላሉ!

የወያኔ መሪዎች ፍፁም ኢፍትሐዊ፣ ፀረ ዴሞክራቲክና ፀረ እኩልነት መሆናቸው የማያከራክር ቢሆንም፤ ለቆሙለት ዓላማ እስከመጨረሻው እንደሚዋደቁ የታወቀ ነው፡፡ ስለሆነም ባልጠበቁትና ባልገመቱት ሁኔታ ሠራዊታቸው በየግንባሩ ቢፍረከረክም የጦርነቱን ዘይቤ ቀይረው ወደኖሩበት የሽምቅ ውጊያ ይገባሉ እንጂ እጅ ይሰጣሉ ማለት ከባድ ይሆናል፡፡

አውደ-ውጊያውን አሸንፎ በጦርነቱ መሸነፍ እንዳይመጣ ከወገን ጎራ በጣም ብዙ ሥራ ይጠበቃል፡፡ ከሁሉ አስቀድሞ፣ ጦርነቱ ተራዛሚ ባሕርይ ያለው መሆኑን መገንዘብ መሠረታዊ ነው፡፡ እንዳለፈው ጊዜ “ዱቄት ሆነዋል፤ ተነዋል” ወዘተ. የሚል ትጥቅ አስፈቺ ትንተናና ትርክት መያዝ ውድ ዋጋ ያስከፍላል፡፡ ጦርነቱ በወገን ድል እስኪጠናቀቅ ድረስ ሁሉም ሰው ሁልጊዜም በየመስኩ እንዲታገል ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ጦርነቱ በአጭር ጊዜ እንደማይጠናቀቅ ግንዛቤ ከተያዘ ደጀኑ ሕዝብ ሳይዘናጋ ራሱን እንዲያደራጅ፣ እንዲሰለጥን፣ ልማቱን በሠራዊት ዲሲፕሊን እንዲያለማ ወዘተ. ማድረግ ይቻላል፤ መዘናጋትና የእርስ በርስ ሽኩቻና መጠፋፋት አይኖርም፤ በደስታውም በለቅሶውም በከንቱ እየተኮሱ ጥይት ማባከን አይታሰብም፡፡

ጦርነቱ ተራዛሚ ባሕርይ ስላለው፥ ከጭፈራው ቀነስ አድርጎ ራስን ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡ ካለፈው ውድቀት መማር ብልህነት ነው፡፡ በተለይ የአማራ ክልላዊ መንግሥት አመራሮች የሰመረ የመንግሥትና ሕዝብ ግንኙነት ለመፍጠርና አሸባሪ የማይደፍረው ጠንካራ ኅብረተሰብ ለመገንባት ሌት ከቀን መሥራት ይገባቸዋል፡፡

አውቀን እንታረም!
3.5K views08:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-15 21:02:00 የፓስፖርቱና የቪዛው ባለቤት ተገኝቷል የ @abisiniya_times ቤተሰቦች እናመሰግናለን።

@abisiniya_times
6.4K views18:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-15 20:42:34
#Inbox ዛሬ ጠዋት አካባቢ 22 ጎላጎል አካባቢ የአንድ ግለሰብ ፓስፖርትና ቪዛ ወድቆ አግኝቻለሁ የጠፋበት ሰው ካለ ይደውልልኝ 0943180031
@abisiniya_times
6.0K viewsedited  17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-12 18:53:34 በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ማንዱራ ወረዳ በደረሰ ጥቃት የወረዳ አስተዳዳሪን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ተገደሉ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት የወረዳ አስተዳዳሪውን ጨምሮ ስድስት ሰዎች መገደላቸውን አንድ የክልሉ ባለስልጣን እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ። ትላንት ማክሰኞ ጥቅምት 1፤ 2015 በተፈጸመው ጥቃት ከተገደሉ ስድስት ሰዎች መካከል አራቱ የጸጥታ ኃይሎች መሆናቸውንም አስታውቀዋል።

አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የክልሉ ኃላፊ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንዳሉት፤ ትላንትና ከሰዓት የተፈጸመው ጥቃት ኢላማ ያደረገው በመከላከያ ሰራዊት እና በፌደራል ፖሊስ አባላት ታጅበው በማንዱራ ወረዳ ከሚገኘው ቱኒ ቀበሌ ወደ ወረዳው ማዕከል በመጓዝ ላይ የነበሩ የወረዳው አመራሮችን ነው። በጥቃቱ የማንዱራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሂስ ሄጮ እና ሹፌራቸው እንዲሁም አንድ የመከላከያ ሰራዊት እና ሶስት ፌደራል ፖሊስ አባላት መገደላቸውን ኃላፊው ተናግረዋል።

ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የአካባቢው ነዋሪም በተመሳሳይ ስድስት ሰዎች መገደላቸውን አስታውቀዋል። በጥቃቱ ቁጥራቸውን በወል ያላወቋቸው የጸጥታ ኃይሎች ጉዳት እንደደረሰባቸው የሚገልጹት እኚሁ ነዋሪ፤ “ማታ ቁስለኞችን ሲያነሱ ነበር። ወደ ዘጠኝ አምቡላንስ አይቼያለሁ” ሲሉ የዓይን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። ከትላንቱ ጥቃት በኋላ ከመተከል ዞን ቡለን ወረዳ ወደ ግልገል በለስ ከተማ የሚወስደው የተሽከርካሪ መንገድ ለትራፊክ ዝግ መደረጉን ነዋሪው አክለዋል።
1.1K views15:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 09:08:45
* HYLEYS SLIM TEA ( 25 Percent Discount )
* Raspberry flavor , drink hot or cold
* Weight loss Herbal supplement cleanse and detox and 3 natural ingredients like Green tea , senna leaves and natural fruit flavors
* 100 percent Natural product
*  No sugar , no Gluten
* Imported from USA
* NET WT 25 pcs foil Envelope tea bags
* Price 1400
* Contact me @ fasilshopping2 or call using 0967323232
* we are located around 22 area or you can use our free delivery on selected areas or 100 to 250 birr based on your location .
@abisiniya_times
784 views06:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 14:48:42
* VITAMIN D3  , 25 mcg ( 1000 IU )
* 365 by Whole foods market
* Once Daily
* Support for Maintenance of strong bones
* Supports Healthy Immune system Function
* Dietary Supplement
* Imported from USA
* Price 1500
* NET WT. 100 Softgels
* Contact me @fasilshopping2 or call using 0967323232
* We are located around 22 area or you can use our free delivery on selected areas or 100 to 250 birr based on your location .
@abisiniya_times
1.3K views11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 20:03:42
* AVEENO BABY DAILY MOISTURE LOTION
* For delicate skin with Natural Oatmeal colloidal and Dimethicone
* Hypoallergenic moisturizing baby lotion and non Greasy
* Fragrance  free , Phthalate free and paraben free
* Moisturizes baby's skin for 24 hours
* Number 1 pediatrician recommended brand
* Imported from USA
* NET WT 227 gm
* price 500
* Contact me @ fasilshopping2 or call using 0967323232
* we are located around 22 area or you can use our free delivery on selected areas or 100 to 250 birr based on your location .
@abisiniya_times
728 views17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 20:03:00
* VITAMIN C SERUM
* Radha beauty Natural Vitamin c serum for Face
* 20 percent Organic Vitamin C + Vitamin E + Hyaluronic acid
* Professional Anti-Aging brightening serum
* Facial serum for Anti-Aging , Wrinkles and fine lines
* Imported from USA
* NET WT 60 ml
* Price 2300
* Contact me @fasilshopping2 or call using 0967323232
* we are located around 22 area or you can use our free delivery on selected areas or 100 to 250 birr based on Your location .
@abisiniya_times
712 views17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ