Get Mystery Box with random crypto!

አቢሲኒያ - Times

የቴሌግራም ቻናል አርማ abisiniya_times — አቢሲኒያ - Times
የቴሌግራም ቻናል አርማ abisiniya_times — አቢሲኒያ - Times
የሰርጥ አድራሻ: @abisiniya_times
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 38.51K
የሰርጥ መግለጫ

Description
• ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ፣
•በአለማችን የተከናወኑ አስደናቂ ክስተቶች፣
•የስፖርት እና መዝናኛ መረጃዎች፣
•24 ሰዓት ትኩስ እና አዳዲስ መረጃ ያገኛሉ፣
•እንዲሁም ጠቅላላ እውቀት፣
ለማንኛውም መረጃ፦
#ለአስተማማኝ የመረጃ ምንጭ
https://t.me/abisiniya_times

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 15

2022-11-14 16:00:43 በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፤ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አስተዳደር ፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ህዝብን የናቀ መግለጫውን እንዲያስተካክል በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ በአቶ አሸተ ደምለው የተፃፈ እና የተፈረመበት ይህን ይፋዊ ደብዳቤ ለባንኩ ስራ አስኪያጅ ፅፏል።

ከ 80% በላይ ደንበኞቹ በአማራ ክልል የሆነው ፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚሰጠውን ምላሽ እንጠብቃለን ።

-----------------------------------
ቁጥር ወ/ጠ/ሰ/ሁ/01051/15
ቀን 5/03/2015ዓ.ም

ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መስሪያ ቤት
አዲስ አበባ

ጉዳዩ፡- በአስቸኳይ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ ስለመጠየቅ
አገልግሎት መስጠት ላይ የተሰማራ ማንኛውም ለትርፍ የተቋቋመ የንግድ ድርጅት በሚሰራበት አካባቢ የሚገኙ ማህበረሰብን ስነ ልቦና እና እሴት ማክበር ግዴታው ነው።
በዋናነት ለንግድና ለማኀበረሰብ አገልግሎት የተቋቋመ በይበልጥ ደግሞ መንግሥታዊ የሆነ ተቋም የሚሰራበትን አካባቢ ማህበረሰብ የወል ፍላጎቶች ማክበር፣ እሴትና ባህሉን መጠበቅ ትንሹ ተቋማዊ ኃላፊነት ነው። ይህን አለማድረግ የንግድ ተቋሙ በአካባቢው ህዝብ ዘንድ በጥርጣሬ እንዲታይ ብሎም ከገበያ ውድድር መውጣትን ያስከትላል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአገሪቱ የፋይናንስ ተቋም ትልቁ ተቋም መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም ባንኩ በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ላለፉት ሁለት ዓመታት ከአከባቢው አስተዳደርና ህዝብ ተቀራርቦ ያለምንም የፀጥታ እንከን ሲሰጥ የነበረውን አገልገሎት በጎንደር ዲስትሪክት በኩል ሲሰራ መቆየቱ ይታወቃል። ይሁን እንጂ ይህ አንጋፋ ባንክ ለስሙ ክብር የማይመጥን እና ከእውነት የራቀ ለፖለቲካ ፍጆታ የሚውል ረብ-የለሽ መግለጫ በኢትዮጵያ ፕረሬስ ድርጅት በኩል አውጥቷል።
ባንኩ አሰራሩን ህቡዕ በሆነ አካሄድ በመቀየር በጎንደር ዲስትሪክት ሲሰጥ የነበረውን አገልግሎት በመካድ በ"ሽሬ ዲስትሪክት" በኩል አገልግሎቱን እንደሚሰራ አስታውቋል።
በዚህም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደንበኛ ተኮር ( customer based) የንግድ አሰራርን ሳይሆን ፖለቲካዊ አቋምና ፍላጎት የሚያራምድ ከዝንባሌም ከፍ ያለ ሚና ለማሳየት ቃጥቷል። ይህ ኢትዮጵያችን ከምትኮራበት ግዙፍ የንግድ ተቋም የማይጠበቅ፣ ለተቋሙ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያዊነቱ ለሚኮራው ሕዝባችን ጭምር አሳፋሪ ክስተት ነው። ተቋሙ በዚህ ሁነቱ፣ ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ለሁለት ዓመት አገልግሎት ሲሰጥ የነበረ መሆኑን እያወቀ አዲስ እንደ ሚጀምር አስመስሎ መግለጫ ማውጣቱ ለወልቃይት ጠገዴ አማራ ህዝብም ያለውን ንቀትም በጉልህ ገልጿል።
የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ለዘመናት በዘረኛ የትግሬ ልሂቃን የደረሰበትን ዘግናኝ ግፍ የሚያስታውሰው አይፈልግም ብቻ ሳይሆን አምርሮ ይጠላል፤ ይታገላል። ከባርነት ወደ ነፃነት የተሸጋገረበትን ታሪካዊ ምዕራፍ ሊያደናቅፈበት የሚፈልግ የትኛውም ኃይል አይታገስም። ለነፃነቱ ቀናኢ እና ሟች የሆነው የወልቃይት ጠገዴ አማራ ህዝብ የባንኩን መግለጫ በፅኑ ያወግዛል። ባንኩ የታላቋ ኢትዮጵያን መጠሪያ የያዘ እንደመሆኑ መጠን፣ ስሙን የሚመጥን ግብር (መገለጫ) ሊኖረው ይገባል ብለን እናምናለን። በእስካሁኑ ቆይታውም ከዘር፣ ኃይማኖትና ሌሎች ቡድናዊ ወገንተኝነቶች በራቀ መንገድ ኢትዮጵያዊ ቀለምና ገፅታ ተላብሶ አገልግሎት ሲሰጥ እንደነበረ እንረዳለን። ከዚህ መልካም ገፅታውና ከፍታው ሊያወርደው በሚችል መልኩ በኢትዮጵያፕሬስ ድርጅት በኩል ያወጣውን መግለጫ እንደሚያስተካክለው እምነት አለን። ይህን ማድረግ ካልቻለ ግን ባንኩ እንደ ተቋም
ፀረ-ወልቃይት ጠገዴ አማራቱን በግላጭ እንዳሳየ ይቆጠራል። እንደ አስፈላጊነቱም መላው የአማራ ህዝብ እና ፍትህ ወዳድ የኢትዮጵያ ብሔር ብሄረሰቦች በባንኩ ያልተገባ ሁነት ላይ ቁጣቸውን እንዲያሰሙ ንቅናቄ ወደ መፍጠር ለመሻገር እንደምንገደድ እናስታውቃለን።

ከሰላምታጋር//
ቅጅ
ለአብክመ ርዕሰ መስተዳድር
ለአብክመ ገንዘብ ቢሮ
ባህርዳር
ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ም/አስተዳዳሪ
ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ገንዘብ መምሪያ
ሰቲት ሁመራ
822 views13:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-12 19:40:59
@abisiniya_times
637 views16:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-12 07:38:50
@abisiniya_times
1.5K views04:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-07 18:37:23
ለዋልድባ ገዳም አባቶች ድጋፍ አድርጉ

ድጋፋችሁን በአይነት በተለይም በምግብ በአልባሳትና በተለያዩ ቁሳቁሶች ማድረግ ለምትፈልጉ በሙሉ በጎንደርና በአዲርቃይ በአካል በመገኘት ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ።

በጎንደር ልደታ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 16 ዮሐንስ መጥምቅ ቤተ ክርስቲ ያን አካባቢ የዱሮው ቴሌ ወይም ጉሩፕ ሰፈር የዋልድባ አብረንታንት አንደነት ገዳም ዘቤተ ሚናስ ቤተ ብለው ቢመጡ (ቢጠይቁ) የገዳሙን መነኮሳት ያገኛሉ።

ተጨማሪ መረጃለማግኘት -0982171945 መምህር ቆሞስ አባ ገብረ ማርያም ዮሐንስ
-0910648966 አባ ገብረ ኢየሱሰ ኪዳነ ማርያም ጋ መደወል ትችላላችሁ።

ሼር በማድረግ እንተባበር
1.2K views15:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-06 20:44:55
አንጋፋው የኢትዮጵያ አርቲስት የክብር ዶክተር አሊ ቢራ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

ክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ በአዳማ አጠቃላይ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ የቆየ ሲሆን ዛሬ ምሽት ላይ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ከኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ አሳውቋል።

@abissiniya_times
2.3K views17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-06 08:47:30
@abisiniya_times
1.1K views05:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-03 21:19:41
@Skylight Hotel
2.1K views18:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-03 21:17:25
2.1K views18:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 22:05:32
2.3K views19:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 22:05:26 ዶናልድ ሌቪን በኢትዮጵያ የበላይ ገዢ የሆነ አንድ ብሔር አለ የሚለውን ለማሳየት የግድ ‹‹መንዙና ጎንደሩ፣ ጎጃሙና ይፋቱ፣ ወዘተ.›› የሚገናኝበት የጋራ ‹‹አማራ›› የሚባል ህዝብ መፍጠር ስላለበት፣ እንዴት የሸዋ ንጉሦች ከጎንደር ቡራኬ እያገኙ የሚገዙ ነገሥቶች መሆናችን፣ ዝምድናቸውንና መተጋገዛቸውን፣ የባህላቸውን ተመሳሳይነት ለማስረዳት እጅጉን ይጋጋጣል ዶናልድ ሌቪን!

ይህቺንም አማራ የሚባል በደምና በባህል የተሳሰረ ገዢ መደብ አለ የምትል ትርክቱን፣ ህወሃት ወስዶለት ‹‹የአማራው ገዢ መደብ›› ብሎ በማኒፌስቶው አስገብቷታል፡፡ ከነወልቃይቷ፣ ከነአማራ ገዢ መደብ፣ ህወሃት ከዶናልድ ሌቪን ቀብ አድርጎ በማኒፌስቶው በእስኪሪብቶ ከነተሳለ ካርታ ጭምር ኮፒ አድርጎት እናገኛለን፡፡ ለዚህም ነው ዶናልድ ሌቪንን ሞት ከመቅደሙ በፊት፣ ኢትዮጵያ በመጣበት ወቅት ህወሃቶች የንጉሥ አቀባበል፣ የንጉሥ መስተንግዶና የንጉሥ ሽኝት ያደረጉለት፡፡

እና አሁን ይህን የአለን ሙርሄድ የናፒየር ዘመቻ ካርታ ስመለከት፣ ቀደም ብሎ ‹‹አማራ›› እየተባለ ይጠራ የነበረው ኋላ ‹‹በጌምድር››ም ‹‹ጎንደርም›› እየተባለ የሚጠራው የጎንደር ጠቅላይ ግዛት ብቻ ነበር ማለት ነው ወይ? የሚል ብርቱ ጥያቄ አጫረብኝ፡፡ እንዲያ ቢሆን ነው እንጂ፣ ያ ዶናልድ ሌቪን ሸዋውም፣ ጎንደሩም፣ ጎጃሙም በጥቅል የአማራ ወገንነት የሚሰማቸው ‹‹አማሮች ናቸው›› የሚለውን ለማስረዳት እንዲያ የተጋጋጠው! እውን ለዚያ ይሆን?

ባይሆን ኖሮማ፣ ግልጽ ቢሆን ኖሮ፣ ለምን እንዲያ የጎንደርንና የመንዝን ግንኙነት ከሰማይ ከምድር እየቧጠጠ ለማስረዳት ተጣጣረ? ለምን አጠቃልሎ ‹‹አማራ›› ብሎ የጠራቸው ግዛቶችና ገዢ መሳፍንት ለዘመናት እርስ በርስ ሲፋለሙ የመኖራቸውን ነገር ለምን አልገለጸውም? በነገራችን ላይ ህወሃቶች ‹‹አማራ ክልል›› ብለው ሲያሰምሩም፣ ያንንም የኮረጁት (በብዙ መልኩ) ይኸው ጠንቀኛ አሜሪካዊ ዶክተር ዶናልድ ሌቪን በጻፈላቸው ‹‹የአማራነት›› ትርጉምና ማንነት መሠረት እንደሆነ አምናለሁ በግሌ፡፡

ከሰውየው ትንተናና፣ መሬት ላይ በህወሃት ዘመን ተተግብሮ ካየነው ነገር በመነሳት ነው ይህን የምለው፡፡ እና ዶናልድ ሌቪን ታላቅ ጀብዱ የሠራ የተከበረ ንጉሥ ተደርጎ ‹‹እንደ ባለውለታ›› በመለስ ዘመን ከተቸረው ልዩ ክብርና እንክብካቤ ሁሉ ተነስቼ ነው ይህን የምለው፡፡ እንጂ ከእርሱ ነው ተከዜንም መሻገር እንዳለብን፣ አማራ የሚባል ገዢ መደብ እንዳለ፣ አማራ የሚባለው ክልል ከየት እስከ የት መሆን እንዳለበት፣ ትግራይስ ከየት እስከየት መሆን እንዳለበት የኮረጅነው ከዶናልድ ሌቪን ነው የሚል ጽሑፍም ሆነ ማስረጃ አግኝቼ አይደለም፡፡

ከዶናልድ ሌቪን ሁሌ የሚገርመኝ ነገር፣ ዶናልድ መጽሐፉን ሲያሳትም በወቅቱ ኤርትራም የኢትዮጵያ አካል ነበረች፡፡ በዶናልድ መጽሐፍ በሰፈረው ካርታም ላይ ትታያለች፡፡ ዶናልድ ግን ከተከዜ ወዲህ በአማራው ግዛት ያለውን የወልቃይት-ሑመራ-ወዘተ. በትግርኛ ተናጋሪነቱ ወደ ትግራይ ሊካለል ይገባዋል - ብሎ ነጥሎ በሰንጠረዥ አስምሮ መጻፉ - እጅግ ይደንቀኛል!

ዶናልድ አንድ ቋንቋ የሚናገሩ በአንድ ክፍለሀገር ሥር መተዳደር አለባቸው ብሎ ካመነ - በካርታው ኤርትራንስ ለምን በሰንጠረዥ አላመለከታትም? ኤርትራውያንም ትግርኛ ተናጋሪ ናቸው (ብዙዎቹ)! የዶናልድ መርዝ በአማራው ላይ ተረጭቶ፣ በኤርትራ ላይ ግን ፎረሸ! ሁልጊዜ የሚገርመኝ - ይሄን ከዋለልኝም የቀደመ መርዘኛ ሰውዬ - ነሆለል የአማራ ካድሬዎች - ‹‹መንዜው ሌቪን›› የሚል ሁሉ ማዕረግ ጨምረውለታል! ኧረ ሌላም ሀገር-በቀል የማዕረግ ስም አውጥተውለታል!

ይህ ዓይነቱ መንፈዝ (መጃጃል) ሁልጊዜ ሲገርመኝ ይኖራል! ለማንኛውም በአለን ሙርሄድ ‹‹The Blue Nile›› መጽሐፍ ባገኘሁት የተከዜ ወሰንን የሚያሳይ ካርታ ተመስርቼ፣ ስለዚህ ርዕሰ-ጉዳይ ካነሳሁ ሳልወድ የግድ ስሙን ማንሳት የነበረብኝን የዶናልድ ሌቪንን ስም ከነጦሰኛው ‹‹WAX & GOLD...›› (ሰምና ወርቅ - ብሎ ሰይሞ - ጦስ አመንጭቶብን ያለፈውን) መጽሐፉንም ጨምሬ አነሳሁ፡፡

በተረፈ ያነሳኋቸው ሁሉ በግላጭ በካርታና በመጽሐፍት ከቀረቡት እውነታዎች ውጭ፣ ድምዳሜዎቹ በራሴ እምነት በምክንያት የማምንባቸው መሆናቸውን መግለጼ እንዳይዘነጋብኝ፡፡ የተለየ ሀሳብ ያለው ካለ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ፡፡ ያለውን የሰጠ ንፉግ አይባልም፡፡ ከፀቦቻችን ባሻገር የተሰወሩ፣ ለዘመን የታሹ፣ ረዥም የውጪ የክፋት እጆች አሉ፡፡

እነዚያን የክፋት እጆች በእውነት ላይ ተመስርተን ማብቃት፣ እና በህዝባችን መካከል ጦርነትን ሳይሆን ፍቅርን፣ መቃቃርንና መለያየትን ሳይሆን መቀራረብንና መተጋገዝን፣ ጥላቻን ሳይሆን ወገንነትን፣ ቂምበቀልን ሳይሆን እርቅን፣ ሽምግልናን፣ እርቀ-ሠላምን፣ ምህረትን ማስፈን የዚህ የእኛ ትውልድ ኃላፊነት ይመስለኛል፡፡ ለኛ ከራሳችን በላይ ማንም መፍትሄ ይዞ አይመጣልንም፡፡

እውነትንና ቅንነትን ተጠምተናል፡፡ ሠላምን ተርበናል፡፡ እርቅንና መረዳዳትን ታርዘናል፡፡ ፈጣሪ ይርዳን፡፡

እዚሁ ላይ ላብቃ፡፡

#Assaf Hailu
2.2K viewsedited  19:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ