Get Mystery Box with random crypto!

Natnael Mekonnen

የሰርጥ አድራሻ: @natnaelmekonnen21
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 173.42K
የሰርጥ መግለጫ

በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ሲፈልጉና ማስታወቂያ ማሰራት ከፈለጉ 👉 @NatnaelMekonnen7
Facebook.com/natnaelmekonnen.et
Instagram.com/natnaelmekonnen21

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 403

2022-05-14 09:54:03
ናሽ የጥርስ እና የዓይን ህክምና ክሊኒክ
        Nash Dental and Optometry Clinic
 
ናሽ የጥርስ እና የዓይን ህክምና ክሊኒክ ዘመኑ ባፈራቸው መሳሪያዎ ች በመታገዝ ሙሉ የጥርስና የአይን ህክምናን በመስጠት ላይ ይገኛል::  ከምንሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል በከፊል
➢  
➢ መጥፎ የአፍ ጠረንን ማከም
➢ የቆሸሹ ጥርሶችን በማሽን እናፀዳለን
➢ በህክምና መዳን የማይችሉትን ጥርሶች መንቀል
➢ ወጣ ገባ ያሉ ጥርሶችን በ ኦርቶዶንቲክ አፕላይንስ እና በብሬስ ማስተካከል
➢ የጥርስ ስር ህክምናን መስጠት
➢ የተቦረቦሩ ጥርሶችን እንሞላለን
➢ የተነቀሉ ጥርሶችን በሰው ሰራሽ አርተፊሻል መተካት
➢ የጥርስ ራጅ አገልግሎት መስጠት
 
➢ የረዥም እርቀት፤ የአጭር እርቀት እና ከእድሜ ጋር ተያይዞ የሚመጣ የቅርብ እይታ መቀነስ ምርመራ እና ህክምና
➢ ሁለት ዓይኖች ተቀናጅተው ያለመስራት ችግር ምርመራ እና ህክምና
➢ በተለያዩ ምክንያቶች የሚከሰት የእይታ መቀነስ ችግርን ምርመራና ህክምና
➢ የህፃናት የአይን ምርመራና ህክምና
➢ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የአይን መነጽሮች የሎው ቪዥን ድጋፍ መስጫ የቪዥን ቴራፒ መሳሪያዎች መለካት ማስተካከል እና ማዘዝ
 
 
በሁሉም የህክምና አይነቶች ቅናሽ አድርገናል
      አድራሻ: ቁጥር 1 ሜክሲኮ ገነት ሆቴል ፊት ለፊት ካሳ ግራንድ ሞል 4ኛ ፎቅ
                       ቁጥር 2 ሰሚት ሳፋሪ ፍርድ ቤት ፊት ለፊት ገሊላ ፕላዛ
                       Tel: 0905262626, 0913858561
9.6K views06:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 09:53:42
ለ 3 ቀን ብቻ የሚቆይ ልዩ ቅናሽ ከ @habmartofficial

አዳዲስ ዘመናዊ ስልኮችን በተመጣጣኝ ዋጋ ከ HABMART :: ከሙሉ አክሰሰሪ እና ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር

REDMI 9A ( 64/4gb ) … 10,800br

A51 5g (128/6gb )….. 17,000br
A71 5g (128/8gb )….. 19,500br
A90 5g (128/6gb )…. 16,000br

Iphone X 256gb … 25,500br
Iphone 11 128gb …. 37,000br

Note 10+ 5g ( 256gb/12gb )… 29,000br

Redmi note 7 pro (128/6gb )… 14,500br
Redmi note 9 ( 128/4gb )…. 16,000br
Redmi note 10 pro (128/6gb 108mp camera ) … 18,800br
Redmi note 10 ( 128/6gb )…. 16,900br

ሌሎችም አሉን ለበለጠ መረጃ ይደውሉልን 0913849228 @habworld
Join our channel for more products @habmartofficial

ቦሌ መድሃኒአለም Selam city mall, 3rd floor
ልደታ AIA የገበያ ማዕከል , ground floor
9.7K views06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 09:53:26
Tedsport ቴድ-ስፖርት Tedsport

መልካም ዜና! ቦርጭን ባጭር ጊዜ!

SWEAT MAKER
(ውፍረት እና ቦርጭን መቀነስ ፈልገዋል?)

በእንቅስቃሴ ወቅት የሰውነት ሙቀት በመጨመር ውፍረትን ባጭር ጊዜ ይቀንሳል
በትንሽ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ካሎሪ ያቃጥላል
ሆዳችን ላይ ያለን ስብ (Fat) በማቅለጥ ያማረ የሆድ ቅርፅ ያላብሰናል

ያሉበት በነፃ እናደርሳለን
(1200ብር 0961276575 @theo41)

አድራሻ
ቁ-1: ቦሌ ት/ቤት ፊት ለፊት አለምነሽ ፕላዛ ምድር ላይ ሱ.ቁ - 014
ቁ-2:ቦሌ(አትላስ) ግሬስ ፕላዛ 1ኛ ፎቅ ላይ

ሌላ እቃ https://t.me/tedtechofficial
11.2K views06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 01:43:02

#dialog
2.6K views22:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 01:41:22 ኢትዮጵያ ከራሷ ባለፈ ለአፍሪካ ዘላቂ ሰላምና ፀጥታ ግንባር ቀደም ሚናዋን ለመወጣት ትሰራለች።

የመከላከያ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ

አፍሪካ ተኩስ የማይሰማባት አህጉር ለመሆን ግብ ብታስቀምጥም የታሰበው ሳይሳካ የግጭት፣ የሰላምና መረጋጋት እጦት የሚታይባት አህጉር ሆና ቀጥላለች።

የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራት የመከላከያ፣ የፀጥታና ደህንነት ሚኒስትሮችና ወታደራዊ መኮንኖች በአህጉራዊ የሰላምና ፀጥታ ችግሮች ላይ መፍትሔ ለማምጣት ሰሞኑን በአዲስ አበባ ሲመክሩ ሰንብተዋል።

ዛሬም የመከላከያ፣ ፀጥታና ደህንነት ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ 14ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል።

በስብሰባው በአፍሪካ ኢ-ሕገ-መንግሰታዊ የመንግስት ግልበጣ ሙከራዎች፣ ሽብርተኝነት፣ የባህር ላይ ወንበዴዎች መበራከት፣ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ ፖለቲካዊ ሁከትና ብጥብጦች አሳሳቢ እየሆኑ መምጣታቸው ተነስቷል።

የፀጥታና ደህንነት ችግሮችን ለመፍታትም አህጉራዊ የሆነ በዘመናዊ መልኩ የተደራጀ የተጠንቀቅ ወታደራዊ ኃይልን ከማቋቋም ጀምሮ ዘላቂ ጠንካራ እርምጃዎችን መውሰድ እንደሚገባ ተገልጿል።

በጉባኤው ላይ የታደሙት #የኢፌዴሪ የመከላከያ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ፤ ኢትዮጵያ አህጉራዊ የፀጥታና ደህንነት ልዩ ኮሚቴ ስብሰባውን በማስተናገዷ ደስተኞች ነን ብለዋል።

አፍሪካ ካለችበት አስቸጋሪ ሁኔታ እንድትወጣ የጋራ መፍትሔ ለማምጣት መመካከርና በቀጣይነት አብሮ መሥራት እንደሚገባም ተናግረዋል።

ለዚህም የመከላከያ፣ ፀጥታና ደህንነት ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴው ስብሰባ ለአህጉሪቱ ባስፈላጊ ወቅት የተካሄደ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ በውስጧ ያሉ የፀጥታና ደህንነት ችግሮችን ለማስወገድ እየሰራች መሆኗን ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ሀገሪቱ ከራሷ አልፋ በሶማሊያ የአልሸባብን አሸባሪዎች በመዋጋት በሀገሪቱ ሰላም እንዲሰፍን ዛሬም ድረስ የሰላም ማስከበር ሚናዋን በብቃት እየተወጣች መሆኗን ጠቅሰዋል።

በሌሎችም የአፍሪካ ሀገራት የሚከሰቱ ሽብርተኝነትና ጽንፈኝነትን ለማስወገድና ፀጥታና ደህንነት በአህጉሪቱ ለማስፈን በግንባር ቀደምነት ስትሰራ መቆየቷንም አስታውሰዋል።

በቀጣይም በአፍሪካ አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍንና ሽብርተኝነት እንዲወገድ ዝግጁ ናት ያሉት #ዶክተር አብርሃም ግንባር ቀደም ሚናዋንም አጠናክራ ትቀጥላለች ብለዋል።

በስብሰባው ለአፍሪካ ዘላቂ ሰላም በትብብር መሥራት የሚያስችል ሰነድ እንዲጸድቅ ኢትዮጵያ አቋሟን አንጸባርቃለችም ነው ያሉት።
2.7K views22:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 23:14:37
ጎተራ አካካቢ ተገኝታለች
8.7K views20:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 21:56:09
የኢትዮጲያ አየር መንገድ በ አውሮፕላን አብራሪነት ሞያ ዘርፍ መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ማስታወቅያ አውጥቷል

ከ 12 ኛ ክፍል መመዝገብ ይቻላል ? የመመዝጋቢያ መስፈርቶች ; የትምህርት ደረጃ እና ሌሎችን ዝርዝር መረጃዎችን ከስር ባለው ቪዲዮ ይመልከቱ

https://corporate.ethiopianairlines.com/eaa/announcement/application-announcement
20.3K views18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 21:51:40
ቱርክ ፤ የፊንላንድ እና ስውዲን NATOን መቀላቀል እንደማትደግፍ አስታወቀች።

የቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ፤ ሀገራቸው ስዊድን እና ፊንላንድን NATOን በአባልነት የመቀላቀል እቅድ እንደማትደግፍ ገልፀዋል።

ምንም እንኳን ፕሬዝዳንቱ በግልፅ ባያብራሩም የኖርዲክ ሀገራት የብዙ አሸባሪ ድርጅቶች መገኛ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።

ዛሬ አንካራ ውስጥ ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ኤርዶጋን ፥ " ስዊድን እና ፊንላንድን በሚመለከት ያለውን ሂደት እየተከታተልን ነው ፤ ነገር ግን በጉዳዩ ላይ አዎንታዊ አመለካከት የለንም " ብለዋል።

ከዚህ ቀደም NATO ግሪክን በአባልነት መቀበሉ ስህተት ነበር ሲሉም ተደምጠዋል። " እንደ ቱርክ ተመሳሳይ ስህተቶችን መድገም አንፈልግም " ሲሉ አክለዋል።

ከዚህም በተጨማሪ በዝርዝር ባያብራሩም " የስካንዲኔቪያ አገሮች የአሸባሪ ድርጅቶች ማረፊያ ናቸው " ሲሉ የተደመጡት ፕሬዜዳንት ኤርዶጋን ፤ " እንደውም በአንዳንድ ሀገራት የፓርላማ አባላት ናቸው ፤ እኛ ደጋፊ መሆን አንችልም (NATOን የመቀላቀል ጉዳይ) " ብለዋል።

ቱርክ ስውዲንን እና ሌሎች የምዕራብ አውሮፓ ሀገራትን አሸባሪ ስትል የፈረጀቻቸውን እንደ ኩርዲሽ ሚሊሻ ቡድን PKK እና YPG ፤ እንዲሁም በአሜሪካ መቀመጫቸውን ያደረጉትን የፈቱላህ ጉለንን ተከታዮች ይደግፋሉ/ያስተናግዳሉ ስትል በተደጋጋሚ ስትወቅስ ይደመጣል።

አንካራ ጉሌኒስቶች እ.ኤ.አ. በ2016 መፈንቅለ መንግስት ሙከራ አድርገዋል ስትል የምትከስ ሲሆን ጉለን እና ደጋፊዎቹ ክሱን አይቀበሉትም።
19.3K views18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 21:47:16 መድፍ ተኩሶ ወደኃላ መሮጥ
18.5K views18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 19:58:04 ሕዝባችን ዳግም ለወያኔ ወረራ እና ጥቃት እንዳይዳረግ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደወትሮው ሁሉ የፀጥታ መዋቅሩ እና ደጀኑ ሕዝብ የራሱን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ ይሁን - የአማራ ክልል የፀጥታ ምክር ቤት

ሕዝባችን ዳግም ለወያኔ ወረራ ለጥቃት እንዳይዳረግ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደወትሮው ሁሉ የፀጥታ መዋቅሩ እና ደጀኑ ሕዝብ የራሱን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ እንዲሆን የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት አስታውቋል፡፡

ሕዝባችን ዳግም ለወያኔ ወረራ ለጥቃት እንዳይዳረግ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደወትሮው ሁሉ የፀጥታ መዋቅሩ እና ደጀኑ ሕዝብ የራሱን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ እንዲሆን የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት አስታውቋል፡፡

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ ጉዳይ መግለጫ ሰጥቷል።

የምክር ቤቱ መግለጫ ቀጥሎ ቀርቧል:-

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የፀጥታው ምክር ቤት ባደረገው ስብሰባ የክልሉን ሰላምና ፀጥታ ሁኔታ በዝርዝር ገምግሟል፡፡ የወያኔ ወራሪ ቡድን በየቀኑ የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ የትግራይን ሕዝብ ለጦርነት እያነሳሳ በአማራ ክልል ላይ ዳግም ጦርነት አውጇል፡፡ ይህን አደገኛ ቅዠቱን ለመመከትና ለመቀልበስ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የክልሉ መንግሥት የፀጥታ ምክር ቤት በአንክሮ ተወያይቶበታል፡፡ የጸጥታ ምክር ቤቱ በየደረጃው ያለው የፀጥታ መዋቅር ዝግጁ መሆን እንዳለበት አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

በሌላ በኩል በየደረጃው በተደረጉ ሕዝባዊ ውይይቶች ላይ ጎልተው ከወጡ ወሳኝ ጉዳዮች መካከል አንዱ የሕግ ማስከበር ሥራ መላላት ተጠቃሽ መሆኑን የጸጥታ ምክር ቤቱ በጥልቀት አንስቷል፡፡

በቅርብ ጊዜ ደግሞ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የአማራን የውስጥ አንድነት ለማዳከም፣ ሕዝብ ከሕዝብ በማጋጨትና በማጋደል ላይ ተሰማርተው ለጠላት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እየሠሩ ያሉ የተደራጁና ያልተደራጁ ኃይሎች እየተበራከቱ መምጣታቸው ተጨባጭ የፀጥታ ስጋት እየፈጠሩ መሆኑን በዝርዝር ተወያይቶበታል፡፡

እነዚህ ኃይሎች በእምነት፣ በፖለቲካ፣ በብሔር ሕዝባችን እየከፋፈሉ የአማራን የውስጥ አንድነት በማዳከም ለጥቃት ተጋላጭ እንዲሆን የሚያደርጉት ሙከራ በአጭር ካልተቀጨ በሕዝባችንና በክልላችን ሰላምና ደኅንነት ላይ ዘላቂ ጉዳት ሊያስከትል እንደሚችል ድምዳሜ ላይ ደርሷል፡፡

የሕገ-ወጥ ንግድን በማስፋፋት ካለው ሀገራዊ የምርት እጥረት በተጨማሪ ሰው ሠራሽ የምርት እጥረት በመፍጠር የኑሮ ውድነት የሚያባብሱ፣ ምርትን ለጠላት በኮንትሮባንድ አሳልፈው የሚልኩ፣ የሕዝብን ሃብት የሚዘርፉ፣ የዜጎችን ነጻ እንቅስቃሴ የሚገድቡ ድርጊቶች በየአካባቢው እያቆጠቆጡ መጥተው ለክልሉ የፀጥታ ስጋት መሆናቸውን ጸጥታ ምክርቤቱ ለይቷል፡፡ ከዚህም በላይ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች እየተስፋፋ የመጣው ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር የክልሉን ሰላምና ደኅንነት ስጋት ውስጥ እየጣለ ይገኛል፡፡

በተጨማሪም መሳሪያን ለመሞከር በሚል በሐዘንና በደስታ ላይ በግዴለሽነት በሚተኮስ ጥይት የንጹሐንን ህይወት እየቀጨ እና የሕዝባችን የፀጥታ ስጋትና የሐዘን ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ጸጥታ ምክር ቤቱ በአንክሮ ተመልክቷል፡፡

ሕገ-ወጥነትና ሥርዓት አልበኝነት ሥር እየሰደደ በመምጣቱ ሕገ-ወጥ ታጣቂዎች በሚያደርጉት ያልተገባ እንቅስቃሴ የክልሉን ልማቶች እያዳከመ፤ የዜጎችን ነጻ እንቅስቃሴ እየገደበ ፤ የኢንቨስትመንት እድሎችን እየዘጋ፣ የተፈጠረውን የሥራ ዕድል እያጠፋ፣ ለቀጣይ ልማትም እንቅፋት በመሆንና በአጠቃላይ የአማራን ክልል ልማት በአደገኛ ሁኔታ እየተፈታተነ እንደሚገኝ አጽንኦት ሰጥቶ ተመልክቷል፡፡

እነዚህ ሕገ-ወጥ ተግባራት በከተማም ሆነ በገጠር በአጭር ጊዜ ማረም ካልተቻለ የአማራ ክልል ልማት የሚያስቀጥል ሳይሆን የነበረውንም የሚያመክን የሕገ-ወጥነትና የሥርዓት አልበኝነት መናኸሪያ የሚያደርግ መሆኑን በመረዳት ለሕዝብ ሰላምና ደኅንነት ሲባል መልክ መያዝ እንዳለባቸው ታምኖበታል፡፡ በጦርነቱ ምክንያት ተፈናቅለው የሚገኙ ወገኖቻችንም በአግባቡ ምግብ እንዲያገኙ አድርጎ ወደ ቀያቸው ጊዜ መመለስ ካልተቻለ የፀጥታና ሰብዓዊ ቀውስ እንደሚያስከትል ፀጥታ ምክር ቤቱ ተወያይቶበታል፡፡

ከዚህ አንጻር መንግሥት በየደረጃው ሕግ የማስከበር ሥራውን በጥብቅ በመፈጸም የሕዝቡን ሰላምና ደኅንነት ማስከበር አለበት በማለት ሕዝቡ በተለያዩ መድረኮች ያነሳቸውን ጥያቄዎች መርምሮ ትክክለኛ ጥያቄ መሆኑን አስምሮበታል፡፡

ስለሆነም የክልሉ ጸጥታ ምክር ቤት የአማራ ክልል ያለበትን የፀጥታ ሁኔታ በጥልቀት በመገምገም የወያኔን ዳግም ወረራ ለመቀልበስና ለመከላከል የውስጥ አንድነትን ማጠናከር፣ ሰላምና ደኅንነትን መጠበቅ ቁልፍ ጉዳይ ነው ብሎ ያምናል። ሕዝባችን ዳግም ለወያኔ ወረራ ለጥቃት እንዳይዳረግ ቅድሚያ ሰጥቶ እንደወትሮው ሁሉ የፀጥታ መዋቅሩ፣ ደጀኑ ሕዝብ የራሱን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆን እንዳለበት አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

በመሆኑም በአንድ በኩል ከፌደራል የጸጥታ መዋቅር ጋር በመቀናጀት ከወያኔ የሚሰነዘርብንን ጥቃት ለመከላከል በተጠንቀቅና በዝግጁነት መቆም፤ በሌላ በኩል ደግሞ በውስጣችን ለወያኔ ሴራ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥሩትን ሕገ-ወጦችንና ሥርዓት አልበኞችን በመቆጣጠር የክልላችን ሰላምና ደኅንነት ማስጠበቅ ግንባር ቀደም የትኩረት አቅጣጫ እንዲሆኑ ወስኗል፡፡

ስለሆነም የክልሉ የጸጥታ ምክር ቤት በየደረጃው የጸጥታ ግብረ ኃይል አቋቁሞ ሕገወጥነትን ለመቆጣጠርና ሕግን ለማስከበር ተገቢ ነው ያላቸውን ሕጋዊ ርምጃ እንዲወስድ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

በመሆኑም የክልላችን ሕዝብ፣ ወጣቶች፣ የገጠርና የከተማ ነዋሪዎች ሰላምና ደኅንነታችን ለመጠበቅ እና የውስጥ አንድነታችን ለማጠናከር የፀጥታ መዋቅሩ በሚወስደው እርምጃ ሁሉ ተባባሪ እንድትሆኑ ጥሪያችን እናስተላልፋለን፡፡

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የፀጥታ ምክር ቤት

ግንቦት 5 ቀን 2014 ዓ.ም

ባሕር ዳር
8.7K views16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ