Get Mystery Box with random crypto!

Campus love ❤ Stories

የቴሌግራም ቻናል አርማ campus_love — Campus love ❤ Stories C
የቴሌግራም ቻናል አርማ campus_love — Campus love ❤ Stories
የሰርጥ አድራሻ: @campus_love
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.51K
የሰርጥ መግለጫ

@Juliiian

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-03-02 08:11:54
የጥቁር ህዝቦች ድል...!

ሀገራችን ኢትዮጵያ ሁሉም የአፍሪካ ሀገራት እየተወረሩ በነበረበት ጊዜ ሁሉም የአፍሪካ ህዝቦች እንደ ባሪያ በሚቆጠሩበት ሰዓት በጣሊያን ተወረረች።

በየካቲት 22 ቀን 1888 ዓ.ም ጣሊያን ኢትዮጵያን ወረረች የወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት አጤ ሚኒሊክ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለቤተሰቡ , ለሀይማኖቱ እና ለሀገሩ ሲል መሳሪያውን ይዞ እንዲመጣ እና የማይመጣ ካለ ከእርሳቸው ጋር የመጨረሻው እንደሆነ በማርያም ስም እየማሉ ተናገሩ።

የወቅቱ የአጤ ሚኒሊክ ባለቤት የነበሩት እቴጌ ጣይቱ ሴትነቴን ሳይሉ ሀገራቸው ተደፍራ ዝም እንደማይሉ ተናገሩ።

የአጤ ሚኒሊክን ጥሪ የሰማው በሀገሩ ጉዳይ የማይደራደረው የኢትዮጵያ ህዝብም በ1888 የካቲት 21 ወደ አድዋ ተራራ ለመሄድ ቢያስብም በዝናቡ ምክንያት ይህን ማድረግ ስላልቻለ ክንዱን ሳይተራስ የካቲት 22 1888 ዓ.ም ወደ አድዋ ተራራ ማምራት ጀምሮ ለሊቱን ሙሉ ተጉዞ የካቲት 23 አድዋ ተራራ ደረሰ።

የንጋት ጮራ እንፈነጠቀ ኢትዮጵያ በጀነራል አሉላ እየተመራች የአድዋ ጦርነት ተጀመረ ምድር ድብልቅልቅ አለች ጦርነቱም ቀጥሎ ንጋት 4 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ድል ማድረጓ ተሰማ ፤ ንጋት 5 ሰዓት ኢትዮጵያ የጣሊያንን ወታደሮች ሙሉ ለሙሉ መማረኳ ተሰማ።

አድዋ በዛሬው እለት ለ126ኛ ጊዜ የአጤ ሚኒሊክ አደባባይ ጋር በደማቅ ሁኔታ በመላው ኢትዮጵያዊያን ይከበራል።

- ምኒሊክ ተወልዶ ባያነሣ ጋሻ

ግብሩ እንቁላል ነበር ይሄን ጊዜ አበሻ፤

- ገበየሁ ቢሞት ተተካ ባልቻ

መድፍ አገላባጭ ብቻ ለብቻ፤

- የአድዋ ሥላሴን ጠላት አረከሰው

ገበየሁ በሞቴ ግባና ቀድሰው

ለአድዋ ከተገጠሙ ግጥሞች ዋነኞቹ ናቸው።

ለመላው ኢትዮጵያዊያን እንኳን ለአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!
1.1K viewsJulian , 05:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-02 06:21:38 የሀዘኔ መጨረሻ....


ክፍል 14

.......3 ሰዐት አካባቢ የወ/ሮ ኤልሳ ወንድም መጣ፡፡ እናም ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ "ይልማ እባላለው" አለኝ፡፡ እኔም የውሸት ፈገግታ ፊቴ ላይ ጣል እያደረግኩኝ "እኔ ደግሞ ሰላም እባላለው" አልኩት፡፡ ሲጀመር ይልማን ቀልቤ አሎደደውም ይሄን ደግሞ ብሩኬ አውቋል፡፡ ግን ግድ ስለሆነብኝ ቁጭ አልኩኝ ከትንሽ ቆይታዎች በኀላ ይጨንቀኝ ጀመር፡፡ ይልማ በሚያስጠላው ፊቱ ፈገግ ሲልብኝ የምሰራው ስራ አለ ብዬ ተነስቼ ወደክፍሌ ሄድኩኝ፡፡ ብሩኬም ተከትሎኝ መጣ፡፡ " ሰሊ አጎት ተብዬውን አልወደድሽውማ" አለኝ ፡፡ በአዎንታ አንገቴን ነቀነቅኩለት፡፡ በፈገግታ እያየኝ ግንባሬን ስሞኝ ወጣ፡፡ ወዱያው አቤል መጣና video game መጫወት ጀመርን፡፡

ከዛን ቀን ጀምሮ ይልማ እቤት ይመላለስ ጀመር፡፡ በቀን2 3 ጊዜ መምጣት ጀመረ፡፡ እኔም በራስ መተማመኔ እየተመናመነ ሄደ፡፡ ጭራሽ ወደ ክፍሌ እየወጣ በኩራት "ሰላም እንዴት ነሽ" ይል ጀመረ፡፡ እኔም እየተሳቀቅኩኝ "ደና" እለዋለው፡፡ የኔና የብሩክ ክፍል አጠገብ ለአጠገብ ስለነበረ ድምፅ ያሰማል ብሩክ የይልማን ድምፅ ሲሰማ ወድያው ይመጣል፡፡ ይልማ ብሩክ መምጣቱን ሲመለከት በፍጥነት ይሄዳል፡፡ ብሩክም ይልማ እንደማይመቸው ሁኔታዏች ያሳብቃሉ፡፡ ብዙን ጊዜ የማሳልፈው ክፍሌ ነው፡፡

ቅዳሜ ቀን ጠዋት አካባቢ ነበር ....አቤልና ብሩኬ ሳይክል ለመንዳት ወጥተው ነበር፡፡

ይልማም እንደ ሁል ጊዜው በጠዋት ነው የመጣው፡፡ ይልማ እንደመጣ ወ/ሮ ኤልሳ ብርቄን ጠርታት ወደገበያ ሄድ፡፡ በቤቱ ውስጥ የነበርነው እኔና ይልማ ብቻ ነበርን፡፡ከክፍሌ እንደወጣሁኝ ይልማን አገኘሁት፡፡ እየተርበትበትኩኝ ሰላም አልኩት፡፡ እሱም ሰላምታ ሰጠኝ፡፡ ቶሎ ብዬ ወደ ታች ወረድኩኝ፡፡ ታች ስወርድ ማንም አልነበረም፡፡ እሱም ተከትሎኝ መጣ፡፡ በፍርሀት "ማንም የለም እንዴ" አልኩት፡፡ እሱም እየተጠጋኝና እየሳቀ "አ.....ው ማንም የለም" አለኝ፡፡ ፈርቻለው ግን ፍርሀቴ እንዲታወቅብኝ አልፈለኩም ነበር፡፡ ፈገግ ብዬ "እሺ" አልኩትና እየሮጥኩኝ ወደ ክፍሌ ገባሁኝ ክፍሌንም ቆለፍኩት፡፡

ከ5 ደቂቃ በኀላ የክፍሌ በር ተንኳኳ፡፡ በድንጋጤ "ማነው" አልኩኝ፡፡ "ይልማ ነኝ ክፈቺልኝ" አለኝ፡፡ እየተንቀጠቀጥኩኝ ሆዴን አሞኛል ልተኛ ነው" ስለው በቁጣ ስሜት "ክፈቺ ብዬሻለው አለበለዚያ በሩን እሰብረዋለው" አለኝ፡፡ በጣም ፈራሁ መልስም አልሰጠሁትም ፡፡ በሩን ለመክፈት ትግል ጀመረ የማደርገው ጠፍቶኝ አልጋዬ ላይ ቁጭ አልኩኝ፡፡ ከብዙ ትግል በኀላ ክፍሌን ሰብሮት ገባ፡፡ በአን እጁ ቢራ በአንዱ ደግሞ ቢላ ይዞ ነበር ፈገግ እያለ "... ዛሬ .....ብቻችንን ተገናኘን አይደል ቆንጂዬ .....አለን፡፡ ከክፍሉ ለመውጣት ስሞክር ገፍትሮ አልጋው ላይ ጣለኝ፡፡ መጮህ ጀመርኩኝ ፡፡ እየታገለ ሱሪዬን በያዘው ቢላ መቆራረጥ ጀመረ፡፡ እያለቀስኩኝ ተወኝ አልኩት እሱ ግን ጭራሽ የያዘውን ቢራ እላዬ ላይ ማፍሰስ ጀመረ..........

ክፍል 15 እንዲቀጥል like ማድረግ አትርሱ


Any comments inbox @Juliiian
1.0K viewsJulian , edited  03:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-02 06:21:35 ..የሀዘኔ መጨረሻ......

ክፍል 13

ሄድን፡፡ ይመስለኛል ........አቶ ሄኖክ እና ወ/ሮ ኤልሳ ስለ ህይወታችን ነበር ሲያወሩ የነበረው፡፡ እኔና ወ/ሮ ኤልሳ አቶ ሄኖክ አስገብተውኝ ወደነበረው ክፍል አስገባችኝ ፡፡ ቅድም ደንግጬ ስለነበር የክፍሉን ውበት አላየሁትም ነበር ግን አሁን ሳደው በጣም ያምራል፡፡ ወ/ሮ ኤልሳ ፍልቅልቅ እያለች " የምታርፊበት ክፍል ይሄ ነው የወንድምሽም ክፍል ከጎንሽ ያለው ክፍል ነው ማለቴ በስተግራ ያለው< ብላ በእጅዋ ጠቆመችልኝ፡፡ ወድያው ከክፍሉ ወጣች፡፡ ተመልሳ መጥታ "የብሩኬ ክፍል በቀኝ በኩል ያለው ነው የሚቸግርሽ ነገር ካለ ጠይቂው" ብላኝ ሄደች፡፡ በጣም ደስ አለኝ ፈጣሪ ከላይ ሆኖ እንዳየኝ ተሰማኝ፡፡

በሩን ዘጋ አድርጌ አልጋው ላይ ጋደም አልኩኝ፡፡ ትንሽ የሰላም እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡ ከክፍሉ ልወጣ ስል ብርቄ ሻንጣዬን ይዛልኝ መጣች፡፡ ቶሎ ብዬ ከሻንጣው ውስጥ የቤዚን እና የሙሌን ፎቶ አውጥቼ በፈገግታ መመልከት ጀመርኩኝ፡፡ ወደላይ ቀና ብዬ" ፈጣሪዬ እንደዛ እንዳላዘንኩኝ አሁን ደስታው በተራው ተፈራረቀብኝ ተመስገን" አልኩት፡፡ ምግብ ክፍሌ ድረስ መጣልኝ እሱን በልቼ ሰሀኑን ለመመለስ ወደ ኩሽና አመራሁ ሳላስበው ከብሩክ ጋር ተጋጭተን ወደቅኩኝ " ውይ አላየሁሽም ነበር በጣም ይቅርታ "ብሎ አነሳኝ፡፡ እኔም ቆፍጠን ብዬ "ምንም አይደል " አልኩት፡፡ መንገዴንም ቀጠልኩኝ፡፡ እጄን ያዘኝ ዞር አልኩኝ፡፡ አይኖቹ በጣም ያምራሉ አፈጠጥኩባቸው "ስለ ቤተሰቦችሽ ስለ ሁሉም ነገር ዳድ ነግሮኛል አይዞሽ" አለኝ፡፡ አይኔን ከአይኖቹ መንጭቄ "አመሰግናለው " አልኩት፡፡ ፊልም አብረን እንድናይ ጋበዘኝ እኔም ትንሽ ከተግደረደርኩኝ በኀላ ግብዣውን ተቀበልኩኝ፡፡

ወደ ኩሽና ሄዶ ቺብስ ይዞ መጣ መብራቱን አጠፋፍተን ማየት ጀመርን፡፡ አጠገብ ለአጠገብ ነበር የተቀመጥነው እውነት ለመናገር ፊልሙን አየው ማለት አይቻልም እሱም ያየ አይመስለኝም፡፡ሁለታችንም እየሰረቅን ስንተያይ በልባችን ደግሞ ስናወራ ነበር፡፡ ፊልሙ አለቀ አቤልም ከት/ቤት ተመልሶ መጣ ፡፡ አቶ ሄኖክ እና ወ/ሮ ኤልሳ ያደረጉልንን ሲመለከት በጣም ደስ አለው፡፡ እሱ ስለተደሰተ የኔ ደስታ እጥፍ ድርብ ሆነ፡፡አቤል እና ብሩክ በጣም ተግባብተዋል አብረው ጌም ኳስ መጫወት ነው ስራቸው፡፡


በንደዚ አይነት ሁኔታ ለ3 ወር ኖርን፡፡ በአንድ እሁድ ቀን የጥቁር ልብሴን እንዳወልቀው አቶ ሄኖክና ወ/ሮ ኤልሳ ኮስተር ብለው ነገሩኝ፡፡ እኔም ሀዘኔን ለመግታች ወስኜ ጥቁር ልብሴን አወለቅኩኝ ፡፡ እናትና አባቴንም ያገኘሁኝ ያህል ተሰማኝ፡፡

አቶ ሄኖክ ስራቸው ፊልድ ነው እና ብዙም ጊዜ እቤት አይገኙም እኔና ብሩክም ከ3 ወር በፊት እንደነበርነው አይደለንም በጣም ተግባብተናል፡፡ ት/ት ቤታችንም አንድ ላይ ስለሆነ ተለያይተን አናውቅም፡፡ ብሩክ 12 ክፍል ሲሆን እኔ ደግሞ 11 ነኝ ስለዚህም በጣም ተግባብተናል፡፡

የት/ት አመት ግማሽ ላይ ደረስን፡፡ እናም እረፍት ወጣን፡፡ አቶ ሄኖክ እንደ ሁል ጊዜው ፊልድ ላይ ናቸው፡፡

እረፍት ከወጣን ከ 2 ቀን በኀላ የወ/ሮ ኤልሳ ወንድም ከጠዋቱ 3 ሰዐት አካባቢ መጣ.........

ክፍል 14 እንዲቀጥል like ማድረግ አትርሱ
959 viewsJulian , 03:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-01 07:39:34 ..........የሀዘኔ መጨረሻ......

ክፍል 12

........ክፍል ውስጥ አስገብተውኝ ....." እኔ የአባትሽ ጓደኛ ነኝአይዞሽ እኔ አለሁላቹ አባትሽ እንድንከባከባቹ ቃል አስገብቶኝ ነበር ስለዚህ አብራቹ እዚ ከኛ ጋር ትኖራላችሁ፡፡ ደግሞ ትምህርትሽን እንዳቋረጥሽ ማታ ኤልሲ ነግራኛለች እና አሁን ትቀጢዋለሽ ብሩኬ የሚማርበት ት/ቤት ትገቢያለሽ " አሉኝ ፡፡ እውነት ለመናገር አቶ ሄኖክ እንደዛ ሲሉኝ በቃላት ልገልፃቸው የማልችለው ስሜት ተሰማኝ፡፡ ትንሽ ከቆየሁ በኀላ ቀና ብዬ " እና ለምን ለአባቴ ለቅሶ እቤት መጥተው አላፅናኑንም " አልኳቸው ፡፡ አቶ ሄኖክም " የኔ ስራ ፊልድ ነው እና ብዙ ጊዜ እዚህ ሀገር አልገኝም ለዛነው እና ለናትሽም ለቅሶ ጊዜ አልመጣሁም እና ይቅርታ አድርጊልኝ " አሉኝ፡፡ ፊት ለፊት የሚገኘው ወንበር ላይ ቁጭ ብለው በሀዘን ተውጠው "አባትሽ እስር ቤት አስጠረቶኝ ነበር....አው ከማረፉ ከ 2 ቀን በፊት አስቀድሞ የኔ ውድ ጓደኛ መሞቱ ታውቆት ነው መሰለኝ " ልጆቼን አደራ ....አደራ ሲለኝ ነበር ፡፡ ከዛ እኔ በንጋታው ወደ ሌላ ሀገር ለስራ ሄድኩኝ ፡፡ መሞቱን የሰማሁት እራሱ እዚህ ከመጣሁኝ በኀላ ነው " አሉኝ ፡፡ ሳላስበው እንባዬ ድብ ድብ አሉ፡፡


ከተቀመጡበት ተነስተው አጠገቤ ቁጭ አሉ ደረታቸው ላይ ለጥፈውኝ "እኔ እንደ አባትሽ ልሆንልሽ አልችል ይሆናል ግን እንደ አባትሽ እይኝ ምክንያቱም እኔ እንደ ልጄ ነው የማይሽ " አሉኝ፡፡ እቅፍ አደረግኳቸው፡፡

ወደ ማዕድ ቤት ተመለስን ብሩክ አቤልን ጉልበቱ ላይ አስቀምጦ ስልኩን ሰጥቶት ጌም እያጫወተው ነበር፡፡ ወ/ሮ ኤልሳ ደግሞ ቡና እየጠጣች ነበር ፡፡ አቶ ሄኖክ ወ/ሮ ኤልሳን " ውዴ አንዴ ነይ "አሉዋት፡፡ተነስታ ሄደች፡፡

አቤልም ት/ቤት ስለረፈደበት የብሩክ ሹፌር ወደ ት/ቤት ይዞት ሄደ፡፡ በፍጥነት ተነስቼ ቁርስ የበላንበትን እቃዎች ላነሳሳ ስል ብርቄ መጥታ " ተይው እኔ አነሳሳዋለው ጋሼ ምንም እንዳትሰራ ብለውኛል " ብላ እጄ ላይ ያለውን ሰሀን ተቀበለችኝ ፡፡ እኔም እሺ አልኳት፡፡ ማዕድ ቤቱና ሳሎን ቤቱ ብዙም አይራራቅም፡፡ ብሩክ ሳሎን ቤት ውስጥ ቁጭ ብሎ እያየኝ ነበር፡፡ ከዛ በአይኖቹ ነይ አለኝ፡፡ እኔም ሄጄ ሶፋው ላይ ቁጭ አልኩኝ፡፡

ሁለታችንም መነጋገር ፈልገናል ግን ፈርተናል የተቀመጥኩት ፊት ለፊቱ ስለነበር በጣም ጨነቀኝ የሆነ እንከን ያለብኝ ይመስል ተርበተበትኩኝ፡፡ ከትንሽ ቆይታ በኀላ "አስታወስሽኝ " አለኝ፡፡ እኔም በአዏንታ አንገቴን ነቀነቅኩለት፡፡ የሆነ እንግዳ ስሜት ተሰማኝ ፡፡

ወድያው ወ/ሮ ኤልሳ እየተፍለቀለቀች መጣች፡፡ "ሰላም" አለችኝ ከመቀመጫዬ ተነስቼ "አቤት " አልኳት፡፡ ፈገግ እያለች " ነይ" አለችኝ፡፡ አቶ ሄኖክ ወደ ብሩክ ጠጋ ብለው ትከሻውን መታ መታ እያደረጉ " ሰላምን ተንከባከባት እሷ ማለን ......" ብለው ጀመሩለት፡፡ እኔና ወ/ሮ ኤልሳ ወደ ላይኛው ክፍል ሄድን፡፡ ይመስለኛል ..........

ክፍል 13 እንዲቀጥል like ማድረግ አትርሱ
939 viewsJulian , 04:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-01 07:39:33 ....የሀዘኔ መጨረሻ......

ክፍል 11

.....ብሩክም እኛን ለማየት ዞር አለ ....ሲያየን በጣም ደነገጠ የሱ ሲገርመኝ የወ/ሮ ኤልሳም ባለቤት በትኩረትና በትዝብት ይመለከቱን ጀመር፡፡ ...... ትንሽ ከተፋጠጥን በኀላ የወ/ሮ ኤልሳን ባለቤት አጠገቡ ሄዴ እጄን ለሰላምታ ዘርግቼ " ሰላም እባላለው "አልኳቸው እሳቸውም እጄን ለመጨበጥ እየተጣደፉ "ሰላም እንዴት ነሽ " አሉኝ፡፡ እኔም "ደህና " አልኳቸው ፡፡ አቤልን "ና የኔ ልጅ " ብለው አገላብጠው ሳሙት፡፡ ዞር አልኩኝና እጄን እንደመዘርጋት እያልኩኝ ብሩክን " ሰላም እባላለው አልኩት"እሱም እጄን ይዞኝ በሀሳብ ነጎደ ቶሎ ብዬ እጄን ከእጁ ላይ መነጨቅኩት

የወ/ሮ ኤልሳ ባለቤትም "እኔ ሄኖክ " እባላለሁኝ አሉን፡፡ እኔም ፈገግ ብዬ አቤልን ይዤ ልወጣ ስል አቶ ሄኖክ "ይቅርታ ሰላም " አሉኝ እኔም ሊያዙኝ መስሎኝ ዞር ብዬ "አቤት " አልኳቸው ፡፡ " ባልሳሳት የኮንስትራክሽን ባለሞያው የሙሉጌታ ልጆች ናችሁ አይደል " አሉን፡፡ ይህን ስሰማ አባቴ ትዝ ብሎኝ ማልቀስ ጀመርኩኝ፡፡ አቤልም አለቀሰ ከትንሽ ደቂቃዎች በኀላ እንባዬን እየጠራረኩኝ በኩራት "አዎ" አልኳቸው፡፡ አቶ ሄኖክም " ስለ ሙሉጌታ ሁሉንም ነገር ሰምቻለው እንደውም ላፈላልጋቹ ነበር "አሉን፡፡ ወ/ሮ ኤልሳ ወደ አቶ
ሄኖክ ዞር እያለች " ለምንድን ነው ልታፈላልጋቸው የነበረው ውዴ " አለቻቸው ፡፡ " የአባታቸው አደራ አለብኝ " ብለው ፈገግ አሉ፡፡ ብሩክ አሁንም ደንግጦ አፉን ከፍቶ እየተመለከተን ነው ፡፡ እኔም ባላየ ባላወቀ ማለቴን ቀጥያለው፡፡ ቁርስ አብረናቸው እንጅንበላ አቶ ሄኖክ ጋበዙን፡፡ እኔና አቤልም አሻፈረን አልን ፡፡

ኮስተር ሲሉብን አብረናቸው መመገብ ጀመርን፡፡ የተቀመጥኩት ከብሩክ ፊት ለፊት ነበር፡፡በጣም ጨነቀኝ ብሩክም ቁርሱን ትቶ እኔን በዝምታ ማየቱን ቀጥሎል፡፡ እያየኝ መሆኑን ለማወቅ ቀና ስል አይን ለአይን እንገጣጠማለን በፍጥነት አይኔን ከአይኖቹ ነጥዬ ምግቡነ መመልከት እጀምራለው፡፡ ከትንሽ ደቂቃዎች በኀላ ወ/ሮ ኤልሳ ብሩክን "በላ የኔ ልጅ እንዳይረፍድብህ ሂድ" አለችው ፡፡ እሱም እኔ ላይ እያፈጠጠ ማም ዛሬ ክላስ አልሄድም" አላት፡፡ ከመቀመጫዋ ተነስታ የብሩክን ጭንቅላት እየነካካች በድንጋጤ "ምነው ልጄ አመመክ እንዴ " አለችው ፡፡ አይኑን ሰበር አድርጎ " አይ ትንሽ ስለደበረኝ ነው " አላት፡፡ አቶ ሄኖክም " በቃ ተይው ውዴ ዛሬ እረፍት ያድርግ "አሏት፡፡ "እሺ በቃ" ብላ ተቀመጠች፡፡

ወድያው አቶ ሄኖክ ከመመገቢያ ክፍሉ ወጡ፡፡ እኔም እቃውን ለማነሳሳት ተነሳሁኝ፡፡ አቶ ሄኖክ ብቅ ብለው "ሰላም እሱን ተይውና አንዴ ነይ እፈልግሻለው " አሉኝ፡፡ እኔም " እሺ" ብዬ ሄድኩኝ፡፡

ከብሩክ አጠገብ ያለ ክፍል ውስጥ አስገብተውኝ...........

ክፍል 12 እንዲቀጥል like ማድረግ አትርሱ
908 viewsJulian , 04:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-28 07:10:49 ....የሀዘኔ መጨረሻ .......

ክፍል 10

......ዞር ብዬ "አቤት" አልኳት "እንግዲህ.....ደሞዝሽ 1500 ብር ነው፡፡ ወንድምሽን እኔ አስተምረዋለው አታስቢ" አለችኝ፡፡ የማደርገው ግራ እንደገባኝ "እሺ" ብያት ሄድኩኝ ፡፡ ግን በቀን ውስጥ የምሰራውን ስራ ሳስበው በጣም እንደሚከብደኝ ተረዳሁኝ፡፡ ግን ለአቤል ብዬ መስራት አለብኝ አልኩና እራሴን አፅናናሁኝ፡፡

ሰዐቱ 12:30 ይሆናል ወ/ሮ ኤልሳ እኔንና አበራ ወደ ገበያ ላከችን፡፡ እኛም ሄድን ግን ታክሲ አጥተን ስለነበር ከምሽቱ 3 ሰዐት ነበር የተመለስነው የግቢውን ቀር ከፍተን እንደገባን ወ/ሮ ኤልሳ እሳት ለብሳ እሳት ጎርሳ "ለምንድን ነው በዚህ ሰዐት የመጣችሁት አንደኛችሁን አታድሩም ነበር" አለችን፡፡ አበራም " ታክሲ አጥተን ነው እኮ እሜቴ" አላት፡፡አበራ ማለት የቤቱ ዘበኛ ነው፡፡ እኔ ግን አንገቴን ዘቅዝቄ ዝምታን መረጥኩኝ ወ/ሮ ኤልሳ እየተኮሳተረች "በይ አሁን ወደውስጥ ገብተሽ እራትሽን በልተሽ ተኚ ነገ ብዙ ስራ ይጠብቅሻል" አለችኝ ፡፡እኔም አንገቴን እ! ዳቀረቀርኩኝ "እሺ" ብያት ገባሁኝ፡፡ ቀጥታ ወደ መኝታ ክፍሌ ነበር የገባሁት የእውነት ቀዛ ሰዐት ማልቀስ ፈልጌ ነበር፡፡ ግን ፊትለፊቴ አቤል ተኝቶ ሳየው እና የቤዚ ቃል ትዝ ሲለኝ አቤልዬን እቅፍ አድርጌው ተኛው፡፡

በለሊት ብርቄ መጥታ ቀሰቀሰችኝ እኔም ተነስቼ ምግብ ቀመስራት አገዝኳት ...ከዛ የወ/ሮ ኤልሳን ልጅ ለመቀስቀስ ወደ መኝታ ክፍሉ ሄድኩኝ ፡፡ ..ስገባ በጣም ደነገጥኩኝ ያ እንዳውም ሁለት ጊዜ ቤተክርስቲያን አግኝቼው ሊያዋራኝ ፈልጎ ጥዬው የሄድኩት ልጅ ነበር፡፡ በፍጥነት ከክፍሉ ወጣሁኝ በሩ ጋር ቆሜ ተገረምኩኝ፡፡ በፍጥነት ወደ መክታ ክፍሌ ሄጄ ሻርፕ ኮፍያ ያለው ሹራብ ምናምን አድርጌ ተመልሼ ብሩክን ለመቀስቀስ ወደ ክፍሉ አመራሁኝ፡፡ ቀሰቀስኩት መነሳቱን እንዳረጋገጥኩኝ ከክፍሉ ልወጣ ስል .... እጄን ያዘኝ እኔም የለበስኩትን ሻርፕ አስተካክዬ ወደሱ ዞርኩኝ "አቤት " አልኩት እሱም ማነሽ አለኝ ፡፡ ፊቴን እየሸፋፈንኩኝ "አዲስዋ የቤት ሰራተኛ ነኝ" አልኩት፡፡ እጄን ለቀቀኝና እጁን በቀሽም ስሜት ፀጉሩ ላይ ጣል አድርጎት "ይቅርታ ማም ነግራኝ ነበር ፡፡ በጣም ይቅርታ " አለኝ፡፡ እኔም " እሺ" ብዬው ብዬ ከክፍሉ ወጣሁኝ ፡፡ ከክፍሉ እንደወጣሁኝ ተሰምቶኝ የማያውቅ የሆነ ደስ የሚል ስሜት ተሰማኝ፡፡

በመቀጠል ትላንት ወ/ሮ ኤልሳ ስትዘረዝርልኝ የነቀረውን ስራ ወስራት ጀመርኩኝ፡፡ ወደ ምግብ መመገቢያው ክፍል ልገባ ስል ብሩክ እንደሚያውቀኝ ትዝ ሲለኝ ወደ ውስጥ መግባት ደበረኝ፡፡ ውጪ ቁጭ አልኩኝ ፡፡ አቤል ከእንቅልፉ ተነስቆ ዩኒፎርሙን ለብሶ ወደኔ መጣ ፡፡ "የኔ ቆንጆ በጣም አምሮብሀል" ብዬ እቅፍ አደረኩት፡፡ ወድያው ብርቄ መጣችና ወ/ሮ ኤልሳ እየጠራቺኝ መሆኑን ነገረችኝ ፡፡ መሄድ አልፈለኩም ነበር ግን ግድ ስለሆነ አቤልን ይዤው ወደ ምግብ መመገቢያው ክፍል አመራሁ፡፡ ልክ ክፍሉ ውስጥ እንደገባሁኝ ወ/ሮ ኤልሳ "ውይ መጣቹ ኑ ልጄንና ባለቤቴን ተዋወቁዋቸው " አለችን ፡፡ እኔም ወደ ጠረቤዛው ቀረብ አልኩኝ ብሩክም እኛን ለማየት ዞር አለ .........


ክፍል 11 እንዲቀጥል like ማድረግ አትርሱ .....
944 viewsJulian , 04:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-28 07:10:47 ..የሀዘኔ መጨረሻ .....

ክፍል 9

.....አንኳኳን.... የግቢውን በር የከፈተልን የጥበቃ ሰራተኛው ነበር፡፡ ከማስቴ አክስት ጋር ሰላምታ ከተለዋወጡ በኀላ ወደ ውስጥ ገባን ወድያው የቤቱ ባለቤት መጣች ፡፡ የማስቴን አክስት በግርምት እየተመለከተቻት ''እንዴት ዛሬ መጣሽ አለቻትጠ'' የማስቴ አክስትም የመጣችበትን ጉዳይ ነገረቻት፡፡ ከዛ ወደ ውጪ እንነጋገር አለቻት፡፡ ካወሩ በኀላ ተመልሰው መጡ፡፡ ሴትየዋ እጄን እንደመጨበጥ አያለች "ኤልሳ እባላለው "አለችኝ ፡፡ እኔም እራሴንና አቤልን አስተዋወቅኩዋት፡፡ ''ዘነቡ ሁሉንም ነገር ነግራኛለች አይዟቹ አሺ" አለችን፡፡ እኔም እሺ አልኳትና እጄን የአቤል ትከሻ ላይ ጣል አደረኩት፡፡ ዘነቡ ማለት የማስቴ አክስት ናት፡፡

ትንሽ ቁጭ ካልን በኀላ ዘነቡ በይ ማስቴ ተነሺ እንሂድ" አለቻት፡፡ ማስቴም "እንዴ አክስቴ ግን እኮ"ብላ ልታወራ ስትል ወ/ሮ ኤልሳ "መስታወት ሁሉን ነገር ዘነቡ ነግራኛለች አይዞሽ እኔ አለው "አለቻት፡፡ ማስቴ በሀሳቡ ባትስማማም ግን ምንም ማድረግ ስላልቻለች እኔንና አቤልን ተሰናብታ ከአክስቷ ጋር ሄደች፡፡ወ/ሮ እስከግቢው በር ድረስ ሸኘቻቸው፡፡ ወደ እኛ ጋር መጥታ እኔና አቤል የምንናልፍበትን ክፍል አሳየችን ፡፡ በመቀጠል የስራ ድርሻዬን መዘርዘር ጀመረች፡፡

"ጠዋት ከእንቅልፍሽ 12 ሰዐት ትነሻለሽ ከብርቄ ጋር ቁርስ ትሰሪያለሽ " ብርቄ ማለት እነሱ ቤት የምትሰራ የቤት ሰራተኛ ናት፡፡ ከዛ ብላ ትዕዛዝዋን ቀጠለች፡፡ "ልጄን መኝታ ክፍሉ ሄደሽ ትቀሰቅሺዋለሽ እሱ ከመኝታ ክፍሉ እንደወጣ ክፍሉን በደንብ ታፀጃለሽ፡፡ በመቀጠል እኛ ቁርስ ልንበላ ወደ ማዕድ ቤት ስንሄድ የኔና የባለቤቴን መኝታ ክፍል ታፀጃለሽ፡፡እሱን እንደጨረሽ ከብርቄ ጋር ሆናችሁ እቃውን አጣጥባቹ ቤቱን በደንብ አስተካክላቹ እንደጨረሳቹ ምግባቹን ትበሉና አንቺ ከዘበኛው ጋር ገበያ ሄደሽ የሚያስፈልጉ ነገሮችን ገዛዝተሽ ትመጫለሽ፡፡ እዚህ ቤት ምሳ ብዙም አይደለንም ብሩኬ ት/ቤት ይዞ ይሄዳል ባለቤቴ ደግሞ ውጪ ነው የሚበላው ስለዚህ ምሳ ሰዐት ላይ ብዙም ስራ አይበዛብሽም" አለችኝ ብሩኬ ያለችው ልጆን ነው፡፡

" ከሰዐት በኀላ ብዙም ስራ የለም ግቢውን ታፀዳጃለሽ ከዛ 11 ሰዐት አካባቢ ብርቄን የሚታገዝ ነገር ካለ ታግዢያትና እረፍት ታረጊያለሽ ከዛ እራትሽን በላልተሽ ትተኛለሽ" አለችኝ፡፡ እኔም በእሺ ስሜት አንገቴን ነቀነቅኩላት፡፡ "በይ እሺ ለዛሬ ከብርቄ ጋር ሁኚ " ብላ የኩሽናውን በር አሳየችኝ እሺ ብዬ ልሄድ ስል "ሰላም" አለችኝ እኔም ዞር ብዬ "አቤት" አልኳት "እንግዲ.........

ክፍል 10 እንዲቀጥል like ማድረግ አትርሱ
956 viewsJulian , 04:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-01 14:33:06 የሀዘኔ መጨረሻ......


ክፍል 8

......."ልጄ እናትሽ.....የምትለኝን አልሰማሁም ለዚህ ሁሉ ነገር ተጠያቂው እኔ ነኝ እባክሽ ይቅር በይኝ "አለኝ፡፡ በስስት እየተመለከትኩት "የኔ አባት ምንም አላጠፋህም እኮ" አልኩት:: ወድያው ትንፋሹ መቆራረጥ ጀመረ፡፡" አባ" ብዬ ፊቱን ደባበስኩት ፡፡ አባቴ ጨክኖ የዛን ቀን ወደማይመለስበት ጥሎን ሄደ፡፡ ላብድ ደረስኩኝ እግዛብሄር ምን አድርጌው ይህንን ሁሉ ስቃይ እንዳመጣብኝ ማወቅ ፈለኩኝ ፡፡ ወድያው እራሴን ሳትኩኝ ፡፡

ከነቃሁኝ በኀላ ለመጠንከር ወሰንኩኝ፡፡ የወንድሜ ሀላፊነት አለብኝና ጠንካራ ለመሆን ለራሴ ቃል ገባሁኝ፡፡ ሙሌ ተቀበረ ቤታችንም ሀዘን ላይ ስለነበርን ለ1 ሳምንት ተጨማሪ ጊዜ ሰጡን ፡፡ ሳምንቱም አለቀ ያ ሰውዬ መጥቶ ከቤቱ አሶጣን ፡፡ እንደቀልድ ከተወለድንበት ያ ብዙ ደስታ ካየንበት ቤት ወጣን ፡፡ ስንወጣ የቤዚን እና የሙሌን ፎቶ ብቻ ይዘን ነበር የወጣነው ፡፡ ማስቴ ማልቀስ ጀመረች "በቃ አይዟቹ እኔ አንድ የማውቃት ዘመዴ አለች እሷ ጋር እንሄዳለን" ብላ ይዛን ሄደች፡፡ እዛ ስንደርስ ቤቱ 1 ክፍል ነበር ማስቴ ዘመዴ ያለችው አክስትዋን ነበር በጣም ደግ ናት፡፡ ምግብ ሰጥታን አሳደረችን፡፡ግን እንደዚህ ሊቀጥል እንደማይችል ገባኝ በንጋታው ስራ ለመፈለግ ሄድኩኝ ፡፡ ቀኑን በሙሉ ስዞር ዋልኩኝ ግን ስራ ላገኝ አልቻልኩም፡፡ አቤልም ተጨነቀብኝ ለኔ ከባድ የህይወት ደረጃ ላይ የደረስኩኝ ያህል ተሰማኝ፡፡

ይህንን ያየች የማስቴ አክስት በጣም አሳዘንናት "በሉ አሁን አንድ ቦታ እንሂድ "አለችን ማስቴም "የት ነው የምንሄደው "አለቻት ፡፡ "አንድ ልብስ የማጥብላት ሴት አለች እና ሰራተኛ ትፈልጋለች፡፡ ደግሞ እነሱም ማረፊያ ያገኛሉ" አለቻት ፡፡ ማስቴ ሳቅ እያለች "አይ አክስቴ ሰሊ እኮ ምንም ስራ መስራት አትችልም "አለቻት ከተቀመጥኩበት ተነስቼ "ችግር የለውም ማስቴ 2 ቀን ሰው ካሳየኝ ሁሉንም ነገር ማድረግ አያቅተኝም" አልኳት ፡፡እሷም" ሰሊ ይሄ ስራ እኮ ላንቺ አይገባሽም" አለችኝ፡፡ኮስተር ብዬ አቤልን እየተመለከትኩት " አቤል አንዴ ውጣ "አልኩት እሱም እየተነጫነጨ ወጣ፡፡ እሱ እንደወጣ የማስቴን እጅ ይዣት "ማስቴ እኔ እኮ ትንሽ ልጅ አይደለሁም ወንድሜን ማስተዳደር ያለብኝ ትልቅ ሴት ነኝ፡፡ "አልኳት አይኗ ውስጥ እንባዎች ተጠራቀሙ "ማስቴ አንቺ እኮ ቤተሰቤ ነሽ ለዛ አይደል እስከዛሬ ያልተለየሽን "ስላት "እንዴት እተዋችኀለው" አለችኝ" እኮ አሁን ዕድል ሲመጣልኝ ፍቀዲና ሸኚኛ" አልኳት እቅፍ አደረገችኝ "ግን ሰሊ እራስሽንም ወንድምሽንም መጠበቅ አለብሽ እሺ" አለችኝ ማስቴ ወደ አክስቷ ዞር አለችና "ግን ሁሉን ነገር እስክትለምደው አብሬያት እሆናለው" አለቻት አክስቷም "ችግር የለውም ሴትየዋን ስለምግባባት እናስፈቅዳታለን" አለቻት፡፡ ትንሽ ቁጭ ካልን በኀላ ወደ ሴትየዋ ቤት ሄድን ፡፡ ቤቱ በጣም ትልቅ ነበር ፡፡ አንኳኳን.....

ክፍል 9 እንዲቀጥል ማድረግ አትርሱ...

━━━━━━━✦✿✦━━━━━━━
1.7K viewsJulian, edited  11:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-01 14:33:06

.......የሀዘኔ መጨረሻ.......

ክፍል 7

..........መንገዴን ቀጥያለው ... በድንገት ቆም ብዬ "አቤት" አልኳቸው ማስቴ "ምን ሆነሻል ልጁን ልትገይው ነው እንዴ" ብላ እጄን ከአቤል እጅ ላይ አስለቅቃ አቤልን ያዘችው ፡፡ ተንበርክኬ "ውይ አቤልዬ ይቅርታ "አልኩት:: መንገዳችንንም ቀጠልን እቤት እንደደረስን 2 ፖሊሶች እና አንድ ቀን ቤታችን መቶ የቤቱን ካርታ የወሰደውሰውዬ መጡ፡፡በሩን የከፈትኩላቸው እኔ ነበርኩኝ:: "አቤት" አልኳቸው:: ሰውዬው በኩራት "አባትሽ ብሬን በጊዜው ስላልከፈለኝ አሁን ቤቱን አወርሰዋለው" አለኝ::

በመንግስት ደረጃ አራጣ አበዳሪ መሆን ያስቀጣል ግን ለምን ፖሊሶቹ ለምን እንደመጡ አልገባኝም ስገምት በገንዘብ ገዝቷቸው ነው መሰለኝ ::

ከዛ ብዬ ላወራ ስል አንደኛው ፖሊስ ቤቱን" በ 1 ሳምንት ልቀቁ አለበለዛ የማይሆን ነገር ይፈጠራል" አለኝ ፡፡ ከዛ ሶስቱም ሄድ በሩን ዘግቼ በርስር ቁጭ ብዬ ማልቀስ ጀመርኩኝ ወድያው አቤል መጣ:: መምጣቱን ሳይ ከተቀመጥኩበት ተነስቼ እንባዬን ጠራረኩኝ" አቤልዬ አልኩት"፡፡ "ሰሊ ምነው አለኝ ""ምንም አልሆንኩም አልኩት" "ሰሊ ቤተክርስቲያን እንሂድ "አለኝ ::እኔም እሺ አልኩት ወድያው ለባብሰን ወደ ቤተክርስቲያን ሄድን ፡፡አቤል ለመሳለም ሄደ እኔም ተንበርክኬ "ምን አጠፋን ምን ለምን እንደዚ ታደርጋለህ "እያልኩ ማልቀስ ጀመርኩኝ ፡፡ አቤል እየሮጠ መጣና "እህቴ እባክሽ ተነሺ" አለኝ፡፡ እኔም ቶሎ ብዬ ተነስቼ ወደ መቀመጫ ቦታው ሄደን ተቀመጥን አቤል "እህቴ እባክሽ እንደዚህ አትሁኚ" ብሎ እቅፍ አደረገኝ:: ማልቀሴን ማቆም አልቻልኩም አታልቅሺ አለኝ ሳቅ እያልኩኝ እንባዬን እንደመጠራረግ አድርጌ "ይኜው ካሁን በኀላ አላለቅስም" አልኩት....

ትንሽ ቁጭ እንዳልን ያ እንዲየውም አንድ ቀን መጥቶ እጄን የያዘኝና ሰዐት የጠየቀኝ ልጅ አጠገቤ መጥቶ ተቀመጠ ፡፡ ብዙም አላስተዋልኩትም ነበር ፡፡ "ሰላም" አለኝ ፡፡ እኔም ዞር ብዬ "አቤት "አልኩት ሳየው ደነገጥኩኝ "ስምሽ ሰላም ነው እንዴ" አለኝ "አው ምነው" አልኩት ፡፡ አይ ምንም ብሎ "እኔ ደግሞ ብሩክ እባላለው" ብሎ እጁን ለሰላምታ ሲዘረጋ አቤልን በል ተነስ አሁን እንሂድ አልኩት፡፡ አቤልም ተነሳ የአቤል ትከሻ ላይ እጄን ጣል አድርጌ ዞር ስል ብሩክ እጁን እንደዘረጋ ነው፡፡" መጨባበጡ አስፈላጊ አይመስለኝም ስለዚህ እጁህን ሰብስበው" ብዬ አቤልን ይዤ ሄድኩኝ፡፡ቀናት እንደጉድ እየፈጠኑ ቤቱን ልቀቁ የተባልንበት ቀን ደረሰ፡፡ ሙሌን ለማግኘት ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሄድኩኝ፡፡

ናፍቆታችንን ከተወጣን በኀላ ስለ ቤቱ ሁሉንም ነገር ነገርኩት፡፡ በጣም ደነገጠጠ ከዛ እራሱን ሳተ በመሀከላችን የብረት አጥር ስለነበረ ልይዘው አልቻልኩም ፡፡ "ወይኔ አባቴ" እያልኩኝ መጮህ ጀመርኩኝ ፡፡ ወድያው ፖሊሶቹ አንስተው ወሰድት፡፡ ወደ አንድ ክፍል ነበረ ያስገቡት ተከትያቸው ገባሁኝ ሊያሶጡኝ ሞከሩ አልወጣም አልኳቸው ጉልበት መጠቀም ጀመሩ ወድያው ሙሌ ነቃ ፡፡ ከእጃቸው እራሴን ፈንጥቄ አውጥቼ ሙሌን አቀፍኩት ፡፡" አባ እኔ አልችልም አንተንም ቤዚንም አጥቼ መኖር አልችልም" አልኩት፡፡ በትኩረት እያየኝ "ልጄ እናትሽ ......

ክፍል 8 እንዲቀጥል like ማድረግ አትርሱ..

━━━━━━━✦✿✦━━━━━━━
••●◉Join us share
1.5K viewsJulian, 11:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ