Get Mystery Box with random crypto!

ዘሪሁን ገሠሠ

የቴሌግራም ቻናል አርማ zerihunkocha — ዘሪሁን ገሠሠ
የቴሌግራም ቻናል አርማ zerihunkocha — ዘሪሁን ገሠሠ
የሰርጥ አድራሻ: @zerihunkocha
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.77K
የሰርጥ መግለጫ

በመረጃ እንቀራረብ! በመረጃ እንተሳሰር!

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2023-04-09 15:32:01 ልዩ ልዩ የአማራ አደረጃጀቶች፣ ወጣቶችና ምሁራን ሕዝባችን የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ እና ልዩ ኃይላችንን ትጥቅ የማስፈታት ዘመቻ ለመቀልበስ በአንድነት በመቆም ታሪካዊ አደራችሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

2. ለአገር መከላከያ ሠራዊት፦

አገር ተወረረ፣ ሰሜን ዕዝ ተደፈረ ሲባል ከፊት ቀድሞ አብሮህ መስዋዕትነት የከፈለው የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስ መሆኑ ፀሐይ የሞቀው፣ አገር ያወቀው ጉዳይ ከመሆኑም ሌላ ከጀርባህ በተወጋህ ጊዜ ተወርውሮ የደረሰልህ ኃይል መሆኑን ራስህ ምሥክር ነህ። በዚህ ወሳኝ ሰዓት በልዩ ኃይሉ ላይ እየተደረገ ያለውን ከሴራ ያልተፋታ ትጥቅ የማስፈታት ፖለቲካዊ ውሳኔ እንድትፈጽም ትዕዛዝ ቢተላለፍልህ በወንድሞችህ ላይ አፈሙዝ በማዞር ሕዝብን እንዳታሳዝን እንጠይቃለን። የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስ ለአንተ ስጋት ሳይሆን ቀኝ ክንድሀ፣ የምትጠራጠረው ሳይሆን ከጀርባህ ልታቆመው የምትችል፣ አገር አፍራሽ ሳይሆን አገር የታደገ፣ ጠባብ ሳይሆን በአገራዊ ርዕይ የታነፀ መሆኑን ራስህ ፈትሸህ አረጋግጠሃል፤ መስክረሃልም።

3. ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፦

በአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስ ላይ የሚደረገውን ሕገወጥ የማፍረስ ድርጊት መላው አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እንድትቃወሙና ከአማራ ሕዝብ ጎን እንድትቆሙ እንጠይቃለን።

ልዩ ኃይላችን ህልውናችን!

ሚያዝያ 01 ቀን 2015 ዓ.ም

ባሕርዳር፣ ኢትዮጵያ
4.6K views12:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 15:32:01 ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የአማራ ክልል ምክር ቤት አባላት የተሠጠ መግለጫ!

<< የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስን ለማፍረስ የብልጽግና ፓርቲ የሚያደርገው እንቅስቃሴ ሕገ መንግሥቱን፣ የክልሉን መንግሥትና የአማራን ሕዝብ ሉዓላዊነት የጣሰ በመሆኑ ተቀባይነት የለውም! >> // የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የአማራ ክልል ምክር ቤት አባላት//


የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስ የአገር ህልውና አደጋ ላይ በወደቀ ጊዜ ሁሉ ከፊት በመሰለፍ የጠላትን አከርካሪ በመስበር በደሙ የአገር ሉዓላዊነትን ለማጽናቱ የብልጽግና መራሹ መንግሥት ህያው ምስክር ነው። ሆኖም ይኼን ውለታ በካደ መልኩ ከሰሞኑ የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስን ትጥቅ ለማስፈታት ወስኖ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛል። የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ያሳለፈው ውሳኔ ወቅቱን ያልጠበቀ፣ ነባራዊ ሁኔታዎችን ሆን ተብሎ ወደጎን በመተው የአማራን ሕዝብ ቀጣይነት ላለው ጥቃት የሚዳርግ ብሎም እገዛበታለሁ የሚለውን የአገሪቱን ሕገ መንግሥት የሚጥስ ውሳኔ ነው። በመሆኑም ውሳኔው በሚከተሉት መሠረታዊ ምክንያቶች ተቀባይነት የለውም።

1. የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስን ለማፍረስ ገዥው ፓርቲ አንዳችም ሕጋዊ ሥልጣን የሌለው በመሆኑ፦

በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 52/2/ሰ መሰረት፣ የፖሊስ ኃይል የማደራጀትና የራሳቸውን ሠላም ፀጥታ የማስጠበቅ ኃላፊነት የክልል መንግሥታት ሥልጣን ነው። የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስም በዚህ ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌ መሠረት ክልሉና የአማራ ህዝብ ያሉበትን ስጋቶች በማጤን በክልሉ መንግሥት የተደራጀ የፖሊስ ኃይል ነው።

የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስን እንደገና ማደራጀትም ይሁን ማፍረስ አስፈላጊ መሆኑ ከታመነበት መላው የአማራ ሕዝብና የክልሉ ምክር ቤት በጉዳዩ ላይ ሰፊ ውይይት አድርጎበት በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ብቻ የሚተገበር እንጂ የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስን ለማፍረስና ትጥቅ ለማስፈታት ገዥው ፓርቲ አንዳችም ሕጋዊ ሥልጣን የለውም።

2. ውሳኔው ወቅቱን ያልጠበቀ፣ ነባራዊ ሁኔታዎችን ወደ ጎን ገሸሽ ያደረገ እና የሕዝብን ደኅንነትን አደጋ ላይ ለመጣል ያለመ በመሆኑ፦

2.1. ባለፉት 4 ዓመታት በአማራ ክልል በምስራቅ አማራ የምድረ ገኝ፣ በሰሜን ሸዋ ደራ፣ ምንጃር፣ ሸዋሮቢት፣ አጣዬ እና መሠል አጎራባች ወረዳዎች በኦነግ ሸኔ የሚፈፀሙ በከባድ መሣሪያ የታገዙ ጥቃቶች ሊቆሙ ባለመቻላቸው ከተሞች ወድመዋል፤ በርካታ ሕዝባችን ለሞት ብሎም ለስደት ተዳርጓል። ይኼ ጥቃትና ውድመት ዛሬም እንደቀጠለ ነው።

2.2. በዓባይ ሸለቆ ዙሪያ ሠርጎ ለመግባት የሚሞክረው የኦነግ ሸኔ የሽብር ቡድን አደጋ ያልተቀረፈ ችግር ነው።

2.3. በምዕራብ አማራ በሱዳን ሠራዊትና መነሻቸውን ሱዳን አድርገው በሚንቀሳቀሱ ውስጣዊና ውጫዊ ታጣቂ ቡድኖች የአገርን ሉዓላዊነት በመጣስ የአገሪቱን ግዛት ወርረው ይዘው የሚገኙ ሲሆን፣ በሕዝባችን ላይ ተጨማሪ ጥቃቶችን ለማድረስ የሚደረጉ ሙከራዎችን ለማስቆም ብልጽግና መራሹ መንግሥት ፍላጎት እንደሌለው ታይቷል።

2.4. በክልሉ የሚንቀሳቀሱ እና በተደጋጋሚ የሽብር ተልዕኮ በመውሰድ በሕዝባችን ላይ የማያባራ እልቂት በማድረስ የሚታወቁ የታጠቁ አሸባሪ ቡድኖች ወደ ተሟላ የሰላም አማራጭ የገቡ ባለመሆኑና በማንኛውም ጊዜ ጥቃት ሊያደርሱ የሚችሉባቸው ሁኔታዎች ክፍት ናቸው።

አማራን በጠላትነት ፈርጀው የሚታገሉ ኃይሎች፣ በተለይም ባለፉት አራት ዓመታት ቀጣይነት ባለው መልኩ በአማራ ሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት፣ የዘር ማሳሳት፣ የማንነት ገፈፋና ጅምላ ማፈናቀል ታይቶ በማይታወቅ ሀኔታ እየፈጸሙበት ይገኛሉ። እነዚህ ኃይሎች በትጥቅ የደረጁና የአገር ህልውና ሥጋት መሆናቸው በመንግሥት በተደጋጋሚ ሲገልጽ የቆየ ሲሆን መንግሥት በእነዚህን ኃይሎች ላይ የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ ለሕዝባችን ዘላቂ የደኅንነት ዋስትና ዛሬም ድረስ መስጠት አልቻለም። በዚህም ከሞት የተረፉት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ውሎ አዳራቸው በመጠለያ ካምፖችና በጎዳና ላይ መሆኑም የአደባባይ ሐቅ ነው።

በተጨማሪም በፕሪቶሪያው የሠላም ስምምነት መሠረት ትሕነግ ሙሉ ትጥቁን ያልፈታ መሀኑ የሚታወቅ ሲሆን ሂደቱም ግልጽነት የጎደለው መሆኑ እሙን ነው። የፌዴራሉ መንግሥት ከሚናገረው በተቃራኒ፣ የትሕነግ (የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር) አመራሮችና ሚዲያዎች በአማራ ሕዝብ ላይ የተጠናከረ የጥላቻ ቅስቀሳ እያካሄዱ እና አጎራባች የአማራ አካባቢዎችን በኃይል ለመንጠቅ እየተዘጋጁ መሆናቸውን በአደባባይ እየተናገሩ ይገኛሉ።
የአማራ ሕዝብ ከውስጥና ከውጭ እነዚህና የመሳሰሉትን ግልጽና ቀጥተኛ የደኅንነት ስጋቶች ተደቅነውበት እያለ፣ የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስን ለማፍረስ የሚደረግ ሙከራ የኢፌዴሪ መንግሥት እና የብልጽግና ፓርቲ ለአማራ ሕዝብ ደኅንነት ደንታ ቢስ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው።

ከላይ ከጠቀስናቸው መሠረታዊ ምክንያቶች በተጨማሪ ክልሉ የራሱን ሰላም የመጠበቅ ውስጣዊ ሉዓላዊ መብቶች ያሉት ከመሆኑ ባለፈ፣ ሕዝባችንን ከድኅረ-ጦርነት የሰላምና መረጋጋት ስጋቶች የመጠበቅ እና ሰላምና መረጋጋትን የማስጠበቅ ኃላፊነት ያለበት በመሆኑ፣ በክልሉ ያሉ ነባራዊ ሁኔታዎች ክልሉ የፀጥታ አቅሙን የማጠናከር እንጂ የማሳሳት ሁኔታን የሚፈቅዱ አይደሉም። በሌላም በኩል የክልሎችን የራስን ውስጣዊ ሰላም የማስጠበቅ ሉዓላዊ መብቶች የሚጋፋ እና ከዚህ ቀደም ክልሉን ለጥቃት ያጋለጡ አገራዊ እና ክልላዊ ክፍተቶችን ከግንዛቤ ያላስገባ፣ ከቀደመው የፀጥታ አቅም ጉድለት የተከሰተውን የሕዝብ ጥቃት የሚያቃልል እርምጃ በመሆኑ እኛ የአብን አማራ ምክር ቤት አባላት ውሳኔውን አጥብቀን እንቃወማለን።

ስለሆነም እኛ የአብን የአማራ ክልል ምክር ቤት አባላት፦

ሀ. የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስ የሕዝብ ደኅንነትና ሠላም ለማስከበር የተቋቋመ የሕዝብ ተቋም እንጂ የአንድ ፓርቲ የግል ንብረት አለመሆኑ በግልጽ ሊታወቅ ይገባል። ስለሆነም የብልፅግና ሥራ አስፈጻሚ በሌለው ሥልጣን በሕገ-ወጥ መንገድ በማናለብኝነት የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስን ትጥቅ ለማስፈታትና ለማፍረስ የሚያደርገው የጥድፊያ ሙከራ ከፍተኛ አገራዊ አደጋ የሚያስከትል መሆኑን በመገንዘብ ውሳኔውን እንዲቀለብስ በአጽንኦት እንጠይቃለን።

ለ. የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስን ትጥቅ ማስፈታት የአማራን ሕዝብ የህልውና አደጋ ላይ መጣል መሆኑን በመገንዘብ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እንዲህ ያለውን ኢ-ሕገ መንግሥታዊ፣ ወቅቱን እና ነባራዊ ሁኔታውን ያልጠበቀ ትጥቅ አስፈቺ ውሳኔ እንዳይተገበር እንዲያደርግ እናሳስባለን።
ሐ. የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ ምክር ቤት የወከለው ሕዝብ ህልውና ከመቼውም ጊዜ በላይ አደጋ ውስጥ መሆኑን በመገንዘብ አስቸኳይ የምክር ቤት ስብሰባ በመጥራት በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ውይይት እንዲደረግበት እንጠይቃለን።

በመጨረሻም፦

1. ለመላው የአማራ ሕዝብ፦

የአማራ ልዩ ኃይል ፖሊስ ሕዝባችን እና አገራችን ከፍተኛ ማጥ ውስጥ በገቡበት ወቅት ነፍሱን ሳይሰስት ጠላትን ተከላክሎ እንደ አባቶቹ አገር ያቀና ልጅህ መሆኑን አውቀህ እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ አፍ ተናጋሪ ሆነህ ከጎኑ እንድትቆም ጥሪ እናስተላልፋለን። የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ የወሰነው ውሣኔ ሕግን የጣሰ፣ የክለሉን መንግሥትና የአማራን ሕዝብ ሉዓላዊነት የደፈረ በመሆኑ ውሳኔው እንዲቀለበስ በጽናት እንድትታገል እንጠይቃለን።
4.3K views12:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 14:55:25
ፍኖተ-ሰላም!

#እምቢ
2.8K views11:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 20:14:58 አብይን ለመቀበል የሚወጣ የኮምቦልቻ ፥ የደሴና የሀይቅ ከተማ ነዋሪ ካለ እርሱ ባንዳና ሰላቶ ብቻ ነው!

ከነገወዲያ በሀይቅ ከተማ የመናፈሻ ግንባታ መሠረት ድንጋይ ለማስቀመጥ በሚል ፋሽስቱ ጠ/ሚኒስቴር ወደወሎ እንደሚመጣ ታውቋል፡፡ ከላይ በተገለፁት ከተሞች ያሉ በስም የተለዩ ካድሬዎች "ህብረተሰቡ ደማቅ አቀባበል ማድረግ አለበት!" በማለት በእድርና በመንግሥት አደረጃጀቶች ብሎም በሀይማኖት አባቶች በኩል ቅስቀሳ እያደረጉ መሆኑን አውቀናል፡፡ የደህንነት ሠዎቹም በዛሬው እለት አስቀድመው መግባታቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

ለዚህ ህዝብን የመነጠል ሴራ ተባባሪ መሆን በታረዱት ፣ በተሳደዱትና በገዛ ሀገራቸው ሀገር አልባ በተደረጉት ወገኖቻችን ላይ ከመቀለድ እኩል የሚቆጠር ባንዳነት ነው!

አንድም ሠው ከቤቱ ባለመውጣት የጉራጌ ህዝብ የሠራውን ገድል ወሎ ላይ እንደግመዋለን!

ጥቂት ሰዎች የሚሰባሰቡበት አውድ ከተፈጠረም የተለያዩ የተቃውሞ ባነሮችን ይዘን በመውጣት ድምጻችንን እናሰማለን !

ኮምቦልቻዎች ይሰማል ?
ደሴዎች ይሰማል ?
ተሁለደሬዎች ይሰማል ?

#ሼር ያድርጉት!
5.2K views17:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 18:22:31 ስለልዩ ኃይሎች የወሰነው ማን ነው?

//ውብሸት ሙላት - የህግ ባለሙያ //

ልዩ ኃይሎች የተቋቋሙት በክልል መንግሥታት ነው። በጀታቸውም የሚሸፈነው በክልል ነው። ተጠሪነታቸውም ለክልል መንግሥት ነው።

እነዚህን የክልል ልዩ ኃይሎች መልሶ ማደራጀትም ይሁን ትጥቅ ማስፈታት የሚችሉት፣ ሕጋዊ ሥልጣን ያላቸው የክልል መንግሥታት ናቸው።

ገዢው ፓርቲ (በሥራ አስፈጻሚው ይሁን ወይም በማዕከላዊ ኮሚቴ ወይም በሌላ) በመንግሥት (የክልሎችንም ጨምሮ) አማካይነት የሚፈጸሙ አቅጣጫዎችን ሊያስቀምጥ ይችላል- መንግሥትን የሚመራ ገዢ ፓርቲ ስለሆነ። ይህንን የፓርቲ ውሳኔ ተፈጻሚ እንዲሆን ወደመንግሥታዊ ውሳኔ መለወጥ/ማሸጋገር ግድ ይላል።

በዚህም መሠረት ልዩ ኃይሎችን መልሶ ለማደራጀት ወይም ትጥቅ ለማስፈታት ገዢው ፓርቲ (ብልጽግና) በሥራ አስፈጻሚ ወይም በሌላ መዋቅሩ አቅጣጫ ካስቀመጠ፤ ይህን ውሳኔ ተግባራዊ ለማድረግ የክልል መንግሥታት በካቢኔያቸው (በአስፈጻሚው አካል) ወይም በምክር ቤታቸው  ተስማምተው ማጽደቅ ይጠበቅባቸዋል። የተቋቋሙት በደንብ (Regulation)  በአስፈጻሚው  ከሆነ መልሶ ለማደራጀት ቢያንስ የተቋቋሙበትን ደንብ፣ የተቋቋሙት በክልል ምክር ቤት በአዋጅ (Proclamation) ከሆነ የተቋቋሙበትን አዋጅ ማሻሻል ያስፈልጋል። ለዚህም የክልሎቹ መንግሥታት አስፈጻሚው አካል ወይም ምክር ቤት ውሳኔ ማሳለፍ አለባቸው።

በተቋቋሙበት አግባብና ባቋቋማቸው አካል ነው ድጋሜ መደራጀት ወይም ትጥቅ መፍታት ያለባቸው፤ መወሰንም ማስፈጸምም የሚችለው። ከዚህ ውጭ የገዢው ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ወይም የፌደራል መንግሥት (ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ወይም መከላከያ ሠራዊት ወዘተ) ልዩ ኃይሎችን የማፍረስ ወይም መልሶ የማደራጀት ሕጋዊ ሥልጣን የለውም።

የክልል መንግሥታትም ፣ ሕዝብን ባያወያዩም  እና የሕዝብ ፍላጎትና ስጋት ግድ ባይላቸው እንኳን ፣ እጅግ በጣም ቢያንስ በአስፈጻሚያቸውም ይሁን በምክር ቤታቸው በመወሰን፣ ውሳኔያቸውን ለሕዝብና ለልዩ ኃይሎች ማሳወቅና መተማመን ነበረባቸው። ይኹን እንጂ ይህ ሲኾን አላየሁም ፤ አልሰማሁም። የክልል መንግሥታትም ማብራሪያ ሲሰጡ አልሰማሁም።

በመሆኑም፣ ልዩ ኃይሎች እንዲፈርሱም ይሁን ትጥቅ እንዲፈቱ አሊያም ድጋሜ እንዲደራጁ የወሰነው ማን ነው? ውሳኔውስ የት አለ? ይዘቱስ ምንድን ነው? ለምን ለሕዝብስ ይፋ አልተደረገም?
2.6K views15:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 17:53:00
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ አለልኝ ምህረቱ ታሰሩ።

በእስር ላይ የሚገኙት የፕሮፌሰር ማዕረጉ ቢያበይን፣ የረ/ፕ ሲሳይ አውግቸው እንዲሁም የሌሎች እስረኞች ጠበቃ የሆነው ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ አለልኝ ምህረቱ በአፋኙ መንግሥት ታስረዋል።

አለልኝ ምህረቱ ከ50 በላይ የሕግ ጉዳዮችን ኬዝ ይዘው በፍርድ ቤት በየዕለቱ እየተከራከሩ እንደሚገኙ የኢትዮ 251 ሚዲያ የመረጃ ምንጮች ገልጸዋል። አለልኝ ምህረቱ የታሰሩት ፕሮፌሰር ማዕረጉ ቢያበይን፣ የረ/ፕ ሲሳይ አውግቸው እና ዶ/ር አሰፋ አዳነን ጠይቀው ሲመለሱም እንደታፈኑ የመረጃ ምንጮቻችን ገልጸዋል።

ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ አለልኝ ምህረቱ በኢህአዴግ ዘመነ መንግሥት የኮ/ል ደመቀ ዘውዱ እና የወልቃይት አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ተከሳሾች ጠበቃ እንደነበርም ይታወሳል።

ምንጭ ኢትዮ 251 ሚዲያ
2.6K views14:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 16:53:28 << ማን ፈቺ ማን አስፈቺ ሊሆን ነው፡፡ ይልቅ ደፍረህ ከገባህ መውጣት የለም፡፡ ትግራይ መቀበሪያህ ትሆናለች! >> ብለው ወሽመጡን የቆረጡት እነደፂን አለማድነቅማ አይቻልም ! ከአሸባሪ - እጅ ጠምዝዘው ተደራዳሪና የሀገር መሪ ወደመሆን የመጡት በትግላቸው ነው!

የሚገርመውኮ አሁንም መንግስትን ጉሮሮውን በስተው " የትግራይ ክልል ታጣቂዎች የፀጥታ ስጋት ስላለባቸው ትጥቅ አይፈቱም!" እያስባሉት ነው!

የአማራ ህዝብ መከበሪያውና መታፈሪያው መራራ ትግሉ ብቻና ብቻ ነው!

መቼም ብአዴንማ ፦ የገዛ ቢሮው ውስጥ እንኳ 24 ሰአት እየጠበቀ መቆየት አልቻለም! "ጅብ የሰራውን ስለሚያውቅ በጨለማ ውስጥ ይሄዳል!" እንዲሉት ብሂል...!
2.8K viewsedited  13:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 16:08:08
ደጀን!

#እምቢ
4.6K views13:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 15:54:04
የነውረኛው ስርአት ገመና ይኸው ነው!

<< በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኙ የማዕድን ስፍራዎች ከደቡብ ሱዳን በመጡ ታጣቂዎች በመያዛቸው ኢትዮጵያ ከማዕድን ዘርፍ ብዙ እያጣች ነው፡፡ መንግስት ለችግሩ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲፈልግ ተጠይቋል፡፡ >> //ሸገር ኤፍኤም - መጋቢት 29/2015 ዓ.ም//

መከላከያ ፦

ያጎረሰህን ከምትነክስ ፥ ከሞት ያተረፈህን ከምትወጋ ፥ አብሮህ የተዋደቀውን ከምትክድ ፥ የሀገርን ሉአላዊነት ወደተዳፈረው የሱዳን ታጣቂ ሂድና ውል ሰርተህ አሳየን!
2.9K views12:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 14:59:31
2.9K views11:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ