2021-11-30 23:16:19
. ሀሊማ
ክፍል አምስት
፡
፡
፡
ሰሚራ አሁን ትንሽም ቢሆን እፎይታ ተሰማተ መጅሊሱ ላይ
ተደለድላ ደገፍ ብላ ተቀመጠች ከከድር ፊት ለፊት ዘይነባ
እንደምትቀመጠው ተቀምጣለች...ከድር የልጁ ጉዳይ በጣም
አስጨነቀው ሰሚራ ገና በመጀመሪያ ቀን እንዲ ግዴለሽ መሆኗ
ገረመው ዛሬ በጣም ከባድ ቀን ነው ያሳለፍኩት እራት ለቅርብ ?
ደክሞኛል ልተኛ ነው አለችው ምንም አይነት ነገር አልመለሰላትም
አታወራም እንዴ..... በዝምታ ይመለከታታል እንጂ መልስ
አልሰጣትም መብላት ስትፈልግ ንገረኝ ብላው ወደ መኝታ ቤቱ
ሄደች ሁሉም ነገሯን ከ ዘይነባ ጋር እያመሳሰለ ነው ይሄኔ ዛይነባ
ብትሆን ከድር ዝም የሚለው ሲከፋው እንደሆነ ስለምታውቅ
አጠገቡ ሄዳ "ወዴ ምነው ማን ነው ያስከፋብኝ ንገረኝ ለሰው
ሲነግሩት ይቀላል" እያለች እንደ ህፃን እያባበችትጠይቀው ነበር
እሱ ግን እሱን ለመቆጣጠር አድርጎ ነበር የሚያስበው ያኔ
በመለሰላት መልስ አሁን ፀፀተው ሰሚራ የዘይነባን ያአዳር ልብስ
እና የእሷን ፎጣ ለብሳ ምንቅር ምንቅር እያለች ወደ ሳሎኑ
መጣች ከድር ልክ እንዳያት ከተቀመጠበት ብድግ ብሎ ተነሳው
ሰሚራም ግራ ገብቷት ምን ነው አለችው ከድር ገና ዘይነባ
ከሞተች 24 ሰአት ሳይሞላ ስራው የፀፀተው ይመስላል ኧረ
ምነው ደገመችው አውልቂ ብሎ ፎጣውንም በጃማውንም
አውልቆ ቢወስድባት ምኞቱ ነው ግን አልቻለም መልሶ ተቀመጠ
ሰውዬ ምን እየሆንክ ነው ዘይነባ እንዲ ብላው አታውቅም አይኑ
እንባ አቀረረ እሱም በተራው ወደ መኝታ ቤቱ ሄደ ግን ሌላ ቀን
ወደ መኝታ ቤቱ ሲገባ የሚያውደ ጥሩ መአዛ ያለው የሚስቱ ሽቶ
ዛሬ የለም አልጋው ጫፍ ላይ ተቀምጣ በፈገግታ የምትቀበለው
ሚስቱ ዛሬ የለችም መኝታ ቤቱ የተለቀቀ ቤት መስሏል መጋዘን
መስሏል አልጋው ጫፍ ለይ ተቀምጦ ከ ልብ ተንሰቅስቆ አለቀሰ
ከዘይነባ ውጪ ማንም ሊረዳው እንደማይችል አሁን ነው የገባው
ግን ምን ያደርጋል ይቅርታ ጠይቆ እንኳ ወደ መትመለስበት ሀገር
እራሱ ሸኛት በእጅ ያለ ወርቅ.......አለ ያገሬ ሰው
ከድር ፊቱን ታጥቦ ተመለሰ ሰሚራ እዛው እንደተቀመጠች ናት
ቦታው ላይ ተመልሶ ተቀመጠ ሰሚራ የጎሪጥ እያየችው ሰአቱ
እየሄደ እኮ ነው እንተኛ እንጂ አለች በሁኔታዋ በጣም ተበሳጨ
እንዲ ይሆናል ብሎ አልጠበቀም ነበር በጣም ደስተኛ
እንደምታደርገው ነበር ስትነግረው የነበረው ግን አሁን እንኳን
ደስተኛ ለማድረግ እንደ ባል እራሱ ልታከብረው አልቻለችም ልክ
እንደ ታናሽ ወንድሟ ነው የምታናግረው ድጋሚ ልታወራ ስተዘጋጅ
ይበቃኛል ዝም አልኩሽ እኮ ለምን አይገባሽም መብላት
ከፈለግሽም ቢይ መተኛት ከፈለግሽም እንደዛው ብሏት አንገቱን
ደፎቶ ማሰብ ጀመረ
እንዴ አንተስ አለችው ሰሚራ........ ሚስቴም ልጄም አጠገቤ የሉም እንዴት ነው እንደቀላል
ያየሽው.... የሚስትህን እንኳ ተወው ባይሆን ልጅህን ብትል ያምርብሀል...እንዴት ማለት
ወደህና ፈቅደህ መስሎኝ እስከመጨረሻው የሸኘሀት በስራው
በጣም አፈረ ያቺ ሚስኪን ሚስቱ አነጋገሯ ትህትናዋ ፈገግታው
ሁሉ ነገሯ ናፈቀው ሰሚራ እሱ እንደተቀመጠ ትታው ለነገሩ ያህል
ምግቡን ቀመስ ቀመስ አድርጋ ገብታ ተኛች "ሀሊማ የት ነሽ የኔ
ልጅ" እያለ ማልቀስ ጀመረ ሰሚራ ለጥ ብላ ተኝታለች.....
ሰአቱ ከለሊቱ 8፡00 ይላል ፋጡማ ሀሊማን እንዳቀፈች እንቅልፍ
ይዟት ሄደ ሊነጋጋ ሲል ከድር እንቅለፍ ሸለብ አደረገው ብዙም
ሳይቆይ ነቃ ድጋሚ እንቅልፍ ሸለብ አደረገው አሁንም ነቃ ዘይነባ
በህልሙ እየመጣች እንቅለፍ ነሳቸው ትንሽ ቁጭ እንዳለ የሱብሂ
አዛን ተአዘነ እንደ ማይነጋ የለም ነጋ፡፡ ፈጡማ ቁርስ ለመስራት
ሽር ጉድ ማለት ጀመረች ሀሊማ ከነገጋ ወዲህ ነው ጥሩ እንቅልፍ
የወሰዳት ሰሚራም ቁርስ ሰርታ አቀረበች እሷ መመገብ ጀመረች
እሱ ግን የሚጠብቀው ነገር እንዳለ ነገር ምግብን አይን አይኑን
ያየዋል ብላ እንጂ የአለችው ሰሚራ ሊናገራት ቀና ሲል ሰሚራ ናት
ዘይነባ ብትሆን የመጀመሪያ ጉርሻዋ ለሱ ነበረ ከ እሷ ቀጥላ
ሀሊማ እኔም ካለጎረስኩ ብላ ታጎርሰው ነበር እሱም እንደዘው
ለሁለቱም ካጎረሰ በኃላ ነበር የሚበለው ዛሬ ግን የሚያጎርስም
ጎራሽም የለም ውስጡ በሀዘን ኩምሽሽ አለ ምግብን ትቶ ተነሳ
አትበላም እንዴ በቃኝ ብሎ ልብሱን ለመቀየር ወደ ወስጥ ገባ
አሁንም ቢሆን ተመሳሳይ ነገር ነው የገጠመው ሁሌም
የሚለብሰውነ ልብሰ ዘይነባ ነበር መርጣ የምታስቀምጥለት ከ
ለበሰ በኃላም እሷ ነበር የምታስተካክልለት ዛሬ ግን ከ የት ይምጣ.......
ሀሊማ ትንሽ ረፈርፈድ ሲል ከ እንቅልፏ ነቃች ፈጡማ
ያዘጋጀችላትን ምግብ በላች፡፡ መጣሁ አሺ እሰከዛው ቴሌቨዥን
እያየሽ ጠብቂኝ ብላ ወጣች ከድር ወደስራ የሚሄደው
እንደወትሮው ለመስራት ሳያሆን ትንሽም ቢሆን ከተረጋጋሁ ብሎ
ነው የሀሊማ እህትና ወንድም አሁንም እያለቀሱ ነው ሌሊት
ለይም በጣም ሲያለቅሱ ነበረ አባብሎ ለማስተኛት እየሞከረ
ነበር፡፡ ለነገሩ ማን እንደ እናት ይሆናል ሊነጋጋ ሲል ነበር የተኙለት
እነርሱን ለማስተኛት ሲሞክር ነበር ሰውነቱ የዛለው ለዚህም ነው
የተወሰነም ቢሆን የተኛው ፡፡
ፋጡማ ከ ቤቱ የተወሰነ እራቅ ብላ ዘይነባ ጋር በድጋሚ ደወለች
በሰአቱ ከድር ወደ ስራ ለመሄድ ዝግጅቱን ጨርሶ በሳሎን ቤት
በኩል ለመውጣት በሩ ላይ እንደቆመ ነበር የዘይነባ ስልክ
መጥራት የጀመረው መውጣቱን ትቶ ወደ ውስጥ ተመልሶ ገብቶ
ስልኩ ወደ ሚጠራበት አቅጣጫ ተመለከተ ስልኩን ሰሚራ
ይዛዋለች...ማን ነው?..አላት የትላንቷ ሴትዮ ናት
ከድር ስጪኝ ሰጪኝ ምን ልትላት የምላትን እኔ አውቃለሁ ሁኔታው
ስላላማራት
አልሰጥህም ምን እንደምትላት ካልነገርከኝ አልሰጥህም አለችው.... ኧረ ሊዘጋ ነው ስጭኝ..... አይቻልም አለች ከድር ተናዶ በጩሀት ያደረኩትን ሀሉንም
ነግሪያት ቢያንስ በስነ ስርአት ትቀበር ብሎ ተናግሮ ሲጫርስ ስልኩ
ተዘጋ ፋጡማ ድጋሚ ደወለች እሺ ነገርኩሽ አይደል አሁን ስጪኝ........
Yketlalll
:
· · • • • ጣፋጭ ቃላት • • • · ·
╰── ──╯
••●◉Join us share◉●••
@wubyefkr_kalat // ,, @zii_zuo
✶⊶⊷ ⊶⊷ ❍ ⊶⊷⊶ ⊷✶
••●◉Join us share◉●••
2.9K views20:16