Get Mystery Box with random crypto!

ውዳሴ ማርያም/wdasemaryam

የቴሌግራም ቻናል አርማ wdasemaryam — ውዳሴ ማርያም/wdasemaryam
የቴሌግራም ቻናል አርማ wdasemaryam — ውዳሴ ማርያም/wdasemaryam
የሰርጥ አድራሻ: @wdasemaryam
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18
የሰርጥ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን።
በዝህ ቻናል የተለያዩ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙሮች የሚያገኙበት ቻናል ነው።
መራግብራችን👇👇
✅የበገና መዝሙሮች
✅ የንስሐ መዝሙሮች
✅ ያሬዳዊ ዜማ
✅ ስብከቶች
✅ መፅሐፍ ሀይማኖት....የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን
አስተምህሮትን በተመለከተ፤ ስለ መላእክት፤ስለ ቅዱሳን፤ ያገኙበታል።

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2022-06-17 21:32:37 መንግሥተ ሥላሴ ዘለአለምዝማሬ:- መጋቤ ምስጢር መ/ር አብርሃም ስጦታው


3.1K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 18:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 17:19:48 ኢትዮጵያ ሀገርህ አትተዋት
+++++++++++++++++++++++++
ገና ህፃን ሳለህ ጌታ መርጦሀል
ተክለ ሐይማኖት ክብር ይገባሀል
ኢትዮጵያ ሀገርህ አትተዋት
ምህረት ከአምላክህ ለምንላት

" ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።"
(ያዕ 5: 16)


ዘማሪ ምንዳይ ብርሀኑ
join****share


<< የፃድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው >> ምሳሌ ፲፥፯
ኢትዮጵያ የብዙ ቅዱሳን ሀገር ነች።ከእነኝህ ቅዱሳን ውስጥ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንዱ ናቸው።አቡነ ተክለ ሃይማኖት በእግዚአብሔር ድንቅ ጥበብ፣ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ብሥራት፤ በኢትዮጵያ ምድር በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ልዩ ስሙ ኢቲሳ በሚባል ቦታ ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኀረያ መጋቢት ፳፬ ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ተወለዱ፡፡ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን እሑድ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹አሐዱ አብ ቅዱስ፤ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፤ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ፤ አንዱ አብ ቅዱስ ነው፤ አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው፤ አንዱ መንፈስ ቅዱስ ነው፤›› በማለት ሥላሴን አመስግነዋል፡፡

አቡነ ተክለሃይማኖት በሰባት ዓመታቸው ከግብፃዊው አቡነ ቄርሎስ ዲቁናን ከተቀበሉ በኋላ እግዚአብሔር በክህነት ሕዝቡን እንዲያገለግሉ መረጣቸው፡፡

#በረከታቸው አማላጅነታው አይለየን አሜን



4.5K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, edited  14:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 19:54:29

3.3K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 16:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 05:57:06 ግንቦት 21 . እመቤታችን ማርያም /እመቤታችን በድብረ
ምጥማቅ በምትባል ቦታ ወርቅ ወንበር ላይ ተቀምጣ ለአምስት
ቀን የታየችበት ነው።
ይህም በዓል ከ33ቱ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ሲሆን በዚህ
ቀን ግብጽ ደብረ ምጥማቅ በተባለ ቦታ በተሰራች ቤተክርስቲያን
እመቤታችን ጻድቃንን መልአክትን አስከትላ ትገለጽላቸው ነበር።
እስላምም ክርስቲያንም በግልጽ ይመለከቷት ነበር። ከየአገሩ ያሉ
ሰዎች ይሰበሰባሉ ድንኳን ተክለው ሰቀላ ሰርተው አጎበር ጥለው
ይከትማሉ ፤ድንግልም ከግንቦት 21 ቀን ጀምሮ ለአምስት
ተከታታይ ቀናት ሳታቋርጥ ትገለጽላቸው ነበር፤ህዝቡ የተለያየ
ጥያቄ ይጠይቆታል አዳም አባታችንን አሳይን ይሏታል ገሚሱ
ነብዩ ዳዊትን ገሚሱ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሳይን ይሏታል
አንዳንዱም ከዚህ ቀደም የሞተ ዘመዱን እንድታሳየው
ይጠይቃታል፤እርሷም ለሁሉም ፍቃዳቸውን ትፈጽምላቸው
ነበር፤አዳምን ስትጠራው ከሔዋን ጋር ዳዊትን ስትጠራው
ከበገናው ጋር ቅዱስ ጊዮርጊስን ስትጠራው ከጸአዳ ፈረሱ ጋር
ነው።የእመቤታችን ረድአት እና በርከቱ በሁላችን ላይ ይድርብን
አሜን፡፡ =>የአርያም ንግሥት: የሰማይና የምድር እመቤት:
የሰውነታችንም መመኪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በዚሕች ዕለት
በምድረ ግብፅ ለተከታታይ ቀናት ተገልጻለች::
+ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:
+ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ
ምድረ ግብፅና ኢትዮዽያ በተሰደደ ጊዜ ከድንግል እናቱ:
ከዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ዛሬ ደብረ ምጥማቅ በሚባለው ቦታ ላይ
አርፎ ነበር:: ቦታውን ባርኮ ለዘለዓለም ያንቺ መገለጫ ይሁን
ብሎም ቃል ኪዳን ገብቶላት ነበር::
+ጊዜው በደረሰ ሰዓት ደብረ ምጥማቅ ተገድሞ የበርካታ
መነኮሳት ቤት ሆነ:: እመቤታችንም በልጇ ፈቃድ ግንቦት 21 ቀን
አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን አስከትላት መጣች::
+በዚያ ሕዝበ ክርስቲያንም: አሕዛብም ተሰብስበው ለ5 ቀናት
ከእመ ብርሃን ጋር ይሰነብታሉ::
+እመቤታችንን በአካል መመልከት አይደለም ስሟን መጥራት
ነፍስን ከሥጋ መለየት የሚችል ጣዕምና ደስታ አለው:: ባይሆን
ይሔ ለሚገባውና ላደለው ብቻ ነው::
+የደብረ ምጥማቅና የአካባቢዋ ሰዎች ከእመቤታችን ጋር
የሚቆዩባቸው ቀናት የዘለዓለም የሕይወት ስንቅ የሚይዙባቸው
ናቸው:: ፈልገው የሚያጡት: ጠይቀው የማይፈጸምላቸው ምንም
ነገር አልነበረም:: ነቢያት: ሐዋርያት: ጻድቃን: ሰማዕታት: ደናግል:
መነኮሳት: መላዕክትና ሊቃነ መላእክት ለድንግል ማርያም
ሲሰግዱ ይታዩ ነበርና:: እመ ብርሃንም እየመላለሰች ትባርካቸው
ነበር::
+እነዚያ እርሷን ያዩ ዐይኖች: በፊቷ የቆሙ እግሮች ክብር
ይገባቸዋል:: 5ቱ ዕለታት ሲፈጸሙ ሕዝቡ ከእመቤታችንን በዕንባ
ይሰናበቷታል:: እመ ብርሃንም በብርሃን መስቀል ባርካቸው
ከቅዱሳኑ ጋር ታርጋለች::
+"+ አባ መርትያኖስ +"+
=>አባ መርትያኖስ በበርሃ ከ68 ዓመታት በላይ በቅድስና የኖሩ
አባት ናቸው:: ሰይጣን እርሳቸውን ፊት ለፊት ተዋግቶ መጣል
ቢያቅተው በዝሙት በተለከፉ ሴቶች ያስቸግራቸው ነበር::
+አንድ ቀን አንዲትን ልጅ ከመሸ በእንግድነት ተቀብለዉ ሽቶ
አርከፍክፋ በዝሙት ልትጥላቸው ብትል እግራቸውን እሳት ውስጥ
ጨምረው እግራቸው እየተቃጠለ በሚወጣው ጠረን የቤቱን
ጠረን ቀይረዉ አጋንንትን አርቀዋል:: እሷንም በንስሃ መልሰው
ለቅድስና አብቅተዋታል:: ጻድቁ ከፈተና ለመራቅ በ108 ሃገራት
108 በዓቶች የነበሯቸው ብቸኛ አባት ናቸው::
=>ለአባት እናቶቻችን የተገለጠች እመቤታችን ለእኛም በረድኤት
ትገለጽልን:: ጣዕመ ስሟ በአንደበታችን: ጣዕመ ፍቅሯ በልባችን
ይደርብን::
=>ግንቦት 21 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅድስት ደብረ ምጥማቅ (የእመቤታችን መገለጥ)
2.አባ መርትያኖስ ጻድቅ (በዝሙት ላለመሰናከል እግራቸውን
በእሳት ያቃጠሉ አባት)
3.ቅዱስ አሮን ሶርያዊ
4.ቅዱስ አሞጽ ነቢይ
=>ወርኀዊ በዓላት
1.አበው ጎርጎርዮሳት
2.አቡነ ምዕመነ ድንግል
3.አቡነ አምደ ሥላሴ
=>+"+ የምድር ባለጠጐች አሕዛብ በፊትሽ ይማለላሉ::
ለሐሴቦን ንጉሥ ልጅ ሁሉ ክብሯ ነው::
ልብሷ የወርቅ መጐናጸፊያ ነው::
በሁዋላዋ ደናግሉን ለንጉሥ ይወስዳሉ . . .
በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ::
በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ::
ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ:: +"+ (መዝ. 44:12-17)
<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>
የሚቀበለው የልመናዋ ክብር ፍጹም የሆነ የረድኤትዋም ሀብት
ጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚመላ የተወደደ የልጅዋ ቸርነት ከሁላችን ጋር
በእዉነት ይሁን ከቅዱሳን እረዴት በረከት ያሳትፈን ለዘለዓለሙ
አጽሜን
https://www.facebook.com/100002926496363/posts/pfbid02dq6tSisM6Jp2S51DAMz3EbokBCiYGHCwFjb1r9WzQCycb8ezfKooaqvvFmdy6hWGl/?app=fbl
4.5K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 02:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 18:40:54 ገብርኤል ማርያምን አበሰራት/2/


3.0K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 15:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-22 16:10:01

3.6K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 13:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 17:00:13 አንቲ ዘበአማን


4.0K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 14:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-12 13:57:33

3.8K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 10:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-09 14:07:06 ​​እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

#መዝ. 86፥1
“መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን፡- መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮችናቸው”

ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም በእመቤታችን ልደት ምክንያትዛሬ ደስ ሆነ፡፡

በግንቦት 1 ቀን 5ሺ ከ5መቶ የመከራው ዘመን ሊያልቅ 15 ዓመታት ሲቀሩት/ ሊባኖስ በሚባል ተራራ ከፀሐይ  የምታበራ ሴት ልጅ ተወለደች፡፡

ይህቺውም ፍጥረት ሁሉ ደቂቀ አዳም ሁላቸው ተስፋ ሲያደርጓትና ሲጠባበቋት የነበረች የድኅነታቸው ምልክት እመቤታችን ናት፡፡

ሶሪያዊው ሊቅ ቅዱስ ኤፍሬምም 
“አክሊለ ምክሕነ ወቀዳሚተ መድኀኒትነ፡፡ወመሠረተ ንጽሕነ ኮነ በማርያም ድንግል:- የመመኪያችን ዘውድ የደኅንነታችን መጀመሪያ የንጽሕናችንም መሠረት በድንግል ማርያም ሆነልን” በማለት መናገሩ ስለዚህ ነው፡፡

አክሊል ምክሐነ አላት ይህም አክሊል የወዲህኛው፣ ምክሕ የወዲያኛው ነው። ከነገሥታት መካከል እንደ ዳዊት የከበረ የለም።

ምንም እንኳን ቅዱስ ዳዊት የከበረ ቢሆን የመመኪያችንን ዘውድ ማምጣት አልተቻለውም፡፡

ወቀዳሚተ መድኀኒትነ አላት፡- ቀዳሚተ የወዲህኛው መድኀኒት የወዲያኛው ነው፡፡ከመሳፍንት ወገን የሚሆን ኢያሱ ምንም የስሙ ትርጓሜ መድኃኒት ቢሆን የደኅንነታ መሆን አልተቻለውም፡፡

ወመሠረተ ንጽሕነ አላት:- መሠረት የወዲህኛው፤ ንጽሕ የወዲያኛው ከነቢያተ እግዚአብሔር ወገን የሚሆን ኤልያስ በድንግልና በንጽሕና መኖሩ የሚታወቅ ነው፡፡ 

ነገር ግን ምንም ንጹሕ ድንግል ቢባል የንጽሕናችንመሠረት መሆን አልተቻለው።

የመመኪያችን ዘውድ፣ የደኅንነታችን መጀመሪያ፤ የንጽሕናችን መሠረት ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፤” በማለት ተናግሯል።

በእርሷ ምክንያትነት መድኀኒዓለም  የሚፈጽምልንን ካሳነቢያትና የቀደሙ አበው ሁሉ 
የእርሷን መወለድ በናፍቆት ሲጠባበቁ ነበር።

ከነቢያት አንዱ የሆነ  ኢሳይያስም
“የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔርዘርን ባያስቀርልን 
ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንነ  እንደ ጎሞራም በመሰልነ ነበር፡፡” በማለት መናገሩ በእርሷ መገኘት  ከጥፋት መዳናችንን ሲገልጽ ነው፡፡ 
#ኢሳ 1፥9

#ሼር


4.3K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 11:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-09 14:01:28

2.6K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 11:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ