Get Mystery Box with random crypto!

ውዳሴ ማርያም/wdasemaryam

የቴሌግራም ቻናል አርማ wdasemaryam — ውዳሴ ማርያም/wdasemaryam
የቴሌግራም ቻናል አርማ wdasemaryam — ውዳሴ ማርያም/wdasemaryam
የሰርጥ አድራሻ: @wdasemaryam
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18
የሰርጥ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን።
በዝህ ቻናል የተለያዩ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙሮች የሚያገኙበት ቻናል ነው።
መራግብራችን👇👇
✅የበገና መዝሙሮች
✅ የንስሐ መዝሙሮች
✅ ያሬዳዊ ዜማ
✅ ስብከቶች
✅ መፅሐፍ ሀይማኖት....የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን
አስተምህሮትን በተመለከተ፤ ስለ መላእክት፤ስለ ቅዱሳን፤ ያገኙበታል።

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 15

2021-12-17 05:52:00
የ️ አቡነ ኪሮስ ታሪክ ባጭሩ

️ በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አሞላክ አሜን እንኻን አደረሳቹ ለአቡነ ኪሮስ

አባ ኪሮስ አባቱ ንጉስ ዮናስ እናቱ አንስራ ይባላሉ፡፡ ሀገሩ ሮም ነው፡፡ ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ደጋግ ቅዱሳን ነበሩና አቡነ ኪሮስ በታህሳስ 8 ወለዱ፡፡ አቡነ ኪሮስ የመጀመሪያ ስሙ ዲላሶር ይባል ነበር፡፡ በኋላ አባቱ ከሞተ በኋላ ሀብቱን ከወንድሙ ተካፍሎ ለድሆች መጽውቶ ዓለምን ንቆ መንኖ ሄደ፡፡ ከአባ በቡነዳ ገዳም ገባ፡፡
በ17 ዓመቱ ሥርዓተ ምነኩስናን ተማረ፡፡ በአባ በቡነዳ እጅ መነኮሰ፡፡ ከዚህ በኋላ በጾም በጸሎት ተወስኖ ኖረ፡፡ስለ ዓለም መከራ ለ40 ዘመን ተኝተው ሲጸልዩ እላያቸው ላይ ሳር በቅሎባቸው ሳለ መላእክት መጥተው ተነስ ቢሉት አዳም የፍጡር ቃል ሰምቶ ወድቀዋል ጌታዬ ድምጹን ያሰማኝ አላቸው በኋላ ኪሩቤል አንስቶ ወስዶ ገነት አሳይተውት ጌታችንም ቃል ኪዳን ሰቷቸዋል።

ቃል ኪዳናቸውም ፡- መካኖች ልጀ የሌላቸው ገድሉን አቅፈው ቢያለቅሱ ጸበሉን ቢጠጡ ስምህን ቢጠሩ፤ የመካኒቱን ማህጸን እከፍታለሁ፡፡ የሚሞትባቸውን እንዳይሞተባቸው አደርጋለሁ፡ በንጹ ገንዘቡ ቂምና በቀል ሳይዝ በህግ በስጋውና በደሙ የጸና ሰው በስምህም በተሠራው ቤተክርስቲያን ጧፍ ዘይት ያበራ መገበሪያ ያመጣውን ልጅ አሰጠዋለሁ፡፡ ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ከዚም በኋላ በተወለዱ 270 ዓመታቸው ሐምሌ 8 አርፈዋል።
ረድኤት በረከታቸው አማላጅነታቸው ከሁላችን ጋር ይሁን ✥አሜን✥

T.me/wdasemaryam





ወስብሓት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክብር ✥አሜን✥
553 viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 02:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-15 08:47:38
846 viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 05:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-15 08:47:18 በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡⇡
☞ታኀሳስ (፮) በዚህች ቀን ታላቋ ሰማዕት የቅድስት አርሴማ ዓመታዊ በዓሏ ነው፤ ይህም ቅዳሴ ቤቷ የተከበረበት ነው

በዚህም ቀን ታላላቅ ተአምራቶች ተደርገዋል፤ በተለይም ይህ ቀን በአገረ አርማንያ ልዩ ስፍራ አለው፤ በመዲናችን አዲስ አበባ አስኮ ቃሎ ተራራ ላይ ግሩም ቤተክርስቲያን አላት ታዋቂው ገዳሟ ግን ወሎ ሲሪንቃ ይገኛል።

መስከረም 29 በሰማዕትነት ያረፈችበት ነው፤ እነዚህን ሁለቱን ቀናት ቤተክርስቲያን በደማቁ ታከብራቸዋለች፤ሌላው በዛሬው ቀን ታላቁ አባት አብርሃም ሶርያዊው ያረፈበት ቀን ነው፤ ይህ አባት ተራራን ያፈለሰ ነው፤

ታሪኩ ወዲህ ነው አባ አብርሃም የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ በነበረበት ወራት አንድ አይሁዳዊ ወደ ንጉሱ ገብቶ እንዲህ ይለዋል “እነዚህ ክርስቲያኖች የሚገርሙ ናቸው በወንጌላቸው ላይ የሰናፍጭ ቅንጣት እምነት ካላችሁ ይህንን ተራራ ተነቅለህ ወደዚያ ሂድ ብትሉት ይሆንላቹዋል ይላል፤” ይህ የሐሰት ወንጌል ነው፤ከመካከላቸው ይህን የሚያደርግ አንድስ እንኳን የለም ይለዋል”

ንጉሱም አባ አብርሃምን አስጠርቶ “በእርግጥ ወንጌላችሁ እንዲህ ይላልን ?” ይለዋል አዋን ንጉስ ሆይ ብሎ ይመልስለታል፤ ታዲያ የክርስቲያኖች ሁሉ አባታቸው አለቃቸው አንተ ነህ እስኪ አድርግና አሳየኝ ይለዋል፤ እሺ ግን 3 ቀን ብቻ ይስጡኝ ብሎ ወጣ፤

ጨነቀው ወደ እምቤታችን ቤተክርስቲያን ገብቶ 3 ቀን 3 ሌሊት እህል ሳይበላ ውኃ ሳይጠጣ አለቀሰ፤ እመቤቴ አታሳፍሪኝ አላት፤ ተገለጸችለት ይህ ላንተ አይሆንም ግን ወደ ከተማ ውጣ በእንስራ ውሃ ተሸክሞ የሚሄድ ሰው ታገኛለህ፤ ስሙ ስምዖን ጫማ ሰፊ ነው፤ አንድ አይና ነው፤ አንዱን አይኑን ያጠፋው የልጄን ትዕዛዝ ለማክበር ብሎ ነው፤ ለእርሱ ይቻለዋል እርሱ የሚልህን አድርግ ትለዋለች፤

እንደተባለውም ስምዖንን ያገኘዋል፤ ነገሩን ሁሉ ይገልጽለታል፤ እሺ ለማንም ስሜንም ስራዬንም እንዳትገልጽቢኝ፤ ህዝቡን ሰብስብ እኔ በተሰወረ ቦታ ሆኜ የማሳይህን እየተመለከትክ አድርግ አንተ የምታደርገውን ደግሞ ህዝቡ ያድርግ አለው፤ ንጉሱም ሰራዊቱም ህዝቡም ይህንን ታአምር ለማየት ተሰበሰበ፤

41 ጊዜ ኪራላይሶን ብለው ሶስት ጊዜ ሰገዱ፤ ከዚያም አባ አብርሃ ስምዖን የሚያሳየውን እየተከተለ መስቀሉን አውጥቶ ወደ ተራራው አማተበ፤ ተራራው ወደ ላይ ተነሰ፤ ታላቅ ፍርሃት ሆነ፤ ሶስት ጊዜ ተራራው ወደ ላይ እየተነሳ ይቀመጣል በተራራው ስር ከወዲያ ማዶና ከወዲህ ያሉ ሰዎች ይተያዩ ነበር ይላይ፤

ንጉሱም ህዝቡም እጹብ እጹብ አሉ ምስጉን እግዚያብሔርንም አመሰገኑ፤ ንጉሱ ክርስቲያን ሆኖ ተጠምቋል ብዙ አብያተክርስቲያናትንም አንጿል። አባ እብርሃምም ተፈርቶና ተከብሮ በቅድስናም ኖሮ በዛሬዋ እለት አርፏል። ከቅድስት አርሴማ፤ ከአባ አብርሃምና ከስምዖን ጫማ ሰፊ በረከታቸውን ያድለን። አሜን
ወስበሐት ለእግዚአብሔር
ወወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
✥የኦርቶዶክስ ተዋህዶ የምልክት ቋንቋ መዝሙር✥


853 viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 05:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-12 05:45:05
እንኳን ለቅድስት ባዕታ ማርያም አመታዊ ክብረ በዓል አደረሳቹ አደረሰን ባዕታ-ለማርያም እመቤታችን በሶስት እመቱ ቤተመቀደስ የገባችበት ታህሳስ 3 ነው።

እመቤታችን 3 ዓመት ሲሆናት ጡት ኣቆመች ኣባባ እማማ እያለችም መጫወት ጀመረች በዚህን ጊዜ ቅድሰት ሓና ለባልዋ ጌታየ ልጃችን ኣድጋለች በተሳልነው መሰረት ለቤት እግዚኣብሔር እንስጣት ኣለችው:
ይዘዋት ወደ ቤተ መቀደሰ ሲሄድ ካህኑ ዘካረያስ ጉባዪ ዘርግቶ ህዝቡን ሰብስባ እያስተማራቸው ነበር፡እመቤታችን ቢያያት ከፀሓይ ኣብርታ ከመብረቅ ኣስፍርታ ታየችው፡ይህችን የመሰለች ፍጡር ምን ልንመግባት ነው ብለው ተጨነቁ ፡በዚህ ጊዜ መልእኩ ቅድስ ፋኑኤል ህብስት ሰምያዊ ፃዋ ሰምያዊ ይዞ ተገለፀ እንድ ክንፍን ጋርዶ ኣንድ ክንፍን ኣጎናፁፎ ከመሬት ኣንድ ክንድ ከስንዝር ከፋ ኣድርጎ ህብስቱን ኣብልቶ ወይኑን ኣጠጥቶ እመቤቴ መንገድ ባስመታሁሽ ማሪኝ ብሎ ኣርጒል ይህ የሆነው በታህሳስ 3 ነው።
✥የእመቤታች በረከታ አማላጅነታ አይለየን✥
@wdasemaryam


1.2K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 02:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-11 05:24:57 ✥የኦርቶዶክስ ተዋህዶ የምልክት ቋንቋ መዝሙር✥


1.7K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 02:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-10 18:10:44 ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ኤልያስ
ታህሳስ 1 ቀን የዚህ ታላቅ ነቢይ የተወለደበት ነው፡፡ ትውልዱ
እሥራኤላዊ ሲሆን አባቱ ኢያስኑዩ እናቱ ደግሞ ቶና ይባላሉ፡፡
የተወለደውም ከክርስቶስ ልደት 900 ዓመት በፊት ነበር፡፡
በተወለደበት ቀን በቤታቸው ብርሃን ተሞልቶ ታይቷል፡፡ ብርሃን
የለበሱ 4 መላእክት በእሳት መጐናጸፊያ ሲጠቀልሉት ወላጆቹ
በማየታቸው ደንግጠው ለነቢያትና ለካህናት ነገሯቸው፡፡ ካህናቱ
ግን ነገሩ ቢረቅባቸው "ምን ዓይነት ፍጥረት ይሆን? በእሥራኤል
ይነግሥ ይሆን? ወይስ ነቢይ ይሆን?" ብለውም አድንቀዋል፡፡
ቅዱስ ኤልያስ የተወለደበት ወቅቱ ሕዝቡና ነገሥታቱ የከፉበት
እግዚአብሔር ተክዶ ጣዖት የሚመለክበት በኢሎፍላውያን እጅ
የነበሩት ጣዖታት ዳጐንና በአል በዚያ ዘመን ወደ እሥራኤል
ገብተው ነበር፡፡ ቅዱስ ኤልያስ ግን በዚህ ክፉ ትውልድ መካከል
ሆኖም ሥርዓተ ኦሪትን ጠንቅቆ ያወቀ የንጽሕናና የአምልኮ ሰው
ነበር፡፡ በዚያ ወራትም እግዚአብሔር ለነቢይነት ጠራው፡፡
የእግዚአብሔርን የጸጋ ጥሪ ተቀበለ፡፡ ቅዱሱ አብዛኛውን ጊዜ
መኖሪያው በተራሮችና በዱር ነበር፡፡ በተለይ ደብረ ቀርሜሎስ
ለእርሱ ቤቱ ነበር፡፡ በዚህ ሕይወቱም ከመልከ ጼዴቅ ቀጥሎ
ለድንግልና (ድንግል ነበርና)፣ ለብሕትውና (ብቸኛ ነበርና) እና
ለምንኩስና (ተሐራሚ ነበርና) በብሉይ ኪዳን መሠረትን የጣለ
ነቢይ ነው፡፡
አክአብና ኤልዛቤል ምሰኪኑን ናቡቴ ከአባቶቹ እርስት አፈናቅለው
በግፍ በገደሉት ጊዜ፤ ንጉሱንና ንግስቲቱን ሳይፈራና ሳያፍር
በግልጽ የዘለፈ ነብይ ነው፤ ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይንም
የለጎመ ነው፡፡ ሕዝቡ በኃጢአቱ ምክንያት ተጐዳ፡፡ እርሱን ግን
በቀርሜሎስ ተራራ ቁራ ይመግበው ምንጭ ፈልቆለት ይጠጣ
ነበር ይሔው ቢቀርበት ጸለየ እግዚአብሔርም ከኮራት ወደ ሰራፕታ
እንዲወርድ አዘዘው በዚያም የነቢዩ ዮናስ እናት እንጐቻ ጋግራ
ብታበላው ቤቷ በበረከት ተሞላ፡፡ ልጇ ሕጻኑ ዮናስ ቢሞትም
በጸሎቱ አስነሳላት፡፡ ቀጥሎም በጸሎት ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት
የዘጋውን ሰማይ ከፍቶታል ሕዝቡም፡፡ ይህንንም ያዕቆብ
በመልእክቱ እንዲህ ሲል መስክሯል ያዕ 5 ÷16 "የጻድቅ ሰው
ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች። ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ
ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ
ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥
ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች"
ነቢዩ ከኤልዛቤል 850 ነቢያተ ሐሰትና ካህናተ ጣዖት ጋር
ተወዳድሮ አሸንፏቸዋል፡፡ መስዋዕት ሰውተው የእርሱን ብቻ እሳት
ከሰማይ ወርዳ በልታለታለችና ሕዝቡ ሐሰተኛ ነቢያትን በወንዝ
ዳር በሰይፍ መትተዋቸዋል:: ይሕንን የሰማች ኤልዛቤልም
ትገድለው ዘንድ አሳደደችው፡፡ "አቤቱ ከአባቶቼ አልበልጥምና
ውሰደኝ! ብቻየን ቀርቻለሁና" ብሎ ቢጸልይ እግዚአብሔር ለጣዖት
ያልሰገዱ ሰባት ሺህ ሰዎችን እንዳተረፈ እርሱንም ወደ ብሔረ
ሕያዋን እንደሚወስደው ብሥራትን ነገረው፡፡
እግዚአብሔር አክአብና ኤልዛቤልን ከተበቀላቸው በኋላም ቅዱስ
ኤልያስ በክፋተኞች ላይ 2 ጊዜ እሳትን አዝንሟል::
የሚያርግበት ጊዜ ሲደርስም ደቀ መዝሙሩን ኤልሳዕን
"የምትሻውን ለምነኝ" ቢለው "እጥፍ መንፈስህን" አለ፡፡ 3 ጊዜ
ሊያስመልሰው ሞከረ፡፡ ቅዱስ ኤልሳዕ ግን በብርታት ተከተለው፡፡
ዮርዳኖስን ከፍለው ከተሻገሩ በኋላ ግን ቅዱስ ኤልያስን ሠረገላ
እሳት ወርዶ ነጠቀው ለኤልሳዕም መጎናጸፊያውን ጣለለትና
አረገ፡፡
(1ኛ ነገስት ምዕራፍ 17 እስከ 2ኛ ነገስት ምዕራፍ 2 ታሪኩን
በስፋት ያንብቡ )
የቅዱሳን ነቢያት ረድኤት በረከት አይለየን፡፡
@wdasemaryam
1.2K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 15:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-10 18:10:05 ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ኤልያስ
ታህሳስ 1 ቀን የዚህ ታላቅ ነቢይ የተወለደበት ነው፡፡ ትውልዱ
እሥራኤላዊ ሲሆን አባቱ ኢያስኑዩ እናቱ ደግሞ ቶና ይባላሉ፡፡
የተወለደውም ከክርስቶስ ልደት 900 ዓመት በፊት ነበር፡፡
በተወለደበት ቀን በቤታቸው ብርሃን ተሞልቶ ታይቷል፡፡ ብርሃን
የለበሱ 4 መላእክት በእሳት መጐናጸፊያ ሲጠቀልሉት ወላጆቹ
በማየታቸው ደንግጠው ለነቢያትና ለካህናት ነገሯቸው፡፡ ካህናቱ
ግን ነገሩ ቢረቅባቸው "ምን ዓይነት ፍጥረት ይሆን? በእሥራኤል
ይነግሥ ይሆን? ወይስ ነቢይ ይሆን?" ብለውም አድንቀዋል፡፡
ቅዱስ ኤልያስ የተወለደበት ወቅቱ ሕዝቡና ነገሥታቱ የከፉበት
እግዚአብሔር ተክዶ ጣዖት የሚመለክበት በኢሎፍላውያን እጅ
የነበሩት ጣዖታት ዳጐንና በአል በዚያ ዘመን ወደ እሥራኤል
ገብተው ነበር፡፡ ቅዱስ ኤልያስ ግን በዚህ ክፉ ትውልድ መካከል
ሆኖም ሥርዓተ ኦሪትን ጠንቅቆ ያወቀ የንጽሕናና የአምልኮ ሰው
ነበር፡፡ በዚያ ወራትም እግዚአብሔር ለነቢይነት ጠራው፡፡
የእግዚአብሔርን የጸጋ ጥሪ ተቀበለ፡፡ ቅዱሱ አብዛኛውን ጊዜ
መኖሪያው በተራሮችና በዱር ነበር፡፡ በተለይ ደብረ ቀርሜሎስ
ለእርሱ ቤቱ ነበር፡፡ በዚህ ሕይወቱም ከመልከ ጼዴቅ ቀጥሎ
ለድንግልና (ድንግል ነበርና)፣ ለብሕትውና (ብቸኛ ነበርና) እና
ለምንኩስና (ተሐራሚ ነበርና) በብሉይ ኪዳን መሠረትን የጣለ
ነቢይ ነው፡፡
አክአብና ኤልዛቤል ምሰኪኑን ናቡቴ ከአባቶቹ እርስት አፈናቅለው
በግፍ በገደሉት ጊዜ፤ ንጉሱንና ንግስቲቱን ሳይፈራና ሳያፍር
በግልጽ የዘለፈ ነብይ ነው፤ ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይንም
የለጎመ ነው፡፡ ሕዝቡ በኃጢአቱ ምክንያት ተጐዳ፡፡ እርሱን ግን
በቀርሜሎስ ተራራ ቁራ ይመግበው ምንጭ ፈልቆለት ይጠጣ
ነበር ይሔው ቢቀርበት ጸለየ እግዚአብሔርም ከኮራት ወደ ሰራፕታ
እንዲወርድ አዘዘው በዚያም የነቢዩ ዮናስ እናት እንጐቻ ጋግራ
ብታበላው ቤቷ በበረከት ተሞላ፡፡ ልጇ ሕጻኑ ዮናስ ቢሞትም
በጸሎቱ አስነሳላት፡፡ ቀጥሎም በጸሎት ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት
የዘጋውን ሰማይ ከፍቶታል ሕዝቡም፡፡ ይህንንም ያዕቆብ
በመልእክቱ እንዲህ ሲል መስክሯል ያዕ 5 ÷16 "የጻድቅ ሰው
ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች። ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ
ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ
ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥
ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች"
ነቢዩ ከኤልዛቤል 850 ነቢያተ ሐሰትና ካህናተ ጣዖት ጋር
ተወዳድሮ አሸንፏቸዋል፡፡ መስዋዕት ሰውተው የእርሱን ብቻ እሳት
ከሰማይ ወርዳ በልታለታለችና ሕዝቡ ሐሰተኛ ነቢያትን በወንዝ
ዳር በሰይፍ መትተዋቸዋል:: ይሕንን የሰማች ኤልዛቤልም
ትገድለው ዘንድ አሳደደችው፡፡ "አቤቱ ከአባቶቼ አልበልጥምና
ውሰደኝ! ብቻየን ቀርቻለሁና" ብሎ ቢጸልይ እግዚአብሔር ለጣዖት
ያልሰገዱ ሰባት ሺህ ሰዎችን እንዳተረፈ እርሱንም ወደ ብሔረ
ሕያዋን እንደሚወስደው ብሥራትን ነገረው፡፡
እግዚአብሔር አክአብና ኤልዛቤልን ከተበቀላቸው በኋላም ቅዱስ
ኤልያስ በክፋተኞች ላይ 2 ጊዜ እሳትን አዝንሟል::
የሚያርግበት ጊዜ ሲደርስም ደቀ መዝሙሩን ኤልሳዕን
"የምትሻውን ለምነኝ" ቢለው "እጥፍ መንፈስህን" አለ፡፡ 3 ጊዜ
ሊያስመልሰው ሞከረ፡፡ ቅዱስ ኤልሳዕ ግን በብርታት ተከተለው፡፡
ዮርዳኖስን ከፍለው ከተሻገሩ በኋላ ግን ቅዱስ ኤልያስን ሠረገላ
እሳት ወርዶ ነጠቀው ለኤልሳዕም መጎናጸፊያውን ጣለለትና
አረገ፡፡
(1ኛ ነገስት ምዕራፍ 17 እስከ 2ኛ ነገስት ምዕራፍ 2 ታሪኩን
በስፋት ያንብቡ )
የቅዱሳን ነቢያት ረድኤት በረከት አይለየን፡፡
@wdasemaryam
1.1K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 15:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-10 18:09:54
1.1K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 15:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-03 18:11:28
1.0K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, 15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-03 14:24:20
@wdasemaryam
1.3K viewsDesalegn Dagne ✥ድንግል ሆይ ሁሉን ከሚያስብ ሁሉን ከማይዘነጋ ከልጅሽ አሳስቢ✥, edited  11:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ