Get Mystery Box with random crypto!

መርጌታ ጥላሁን

የቴሌግራም ቻናል አርማ timhrtministers — መርጌታ ጥላሁን
የቴሌግራም ቻናል አርማ timhrtministers — መርጌታ ጥላሁን
የሰርጥ አድራሻ: @timhrtministers
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.21K
የሰርጥ መግለጫ

ለተማሪዎች በቀላሉ የትምህርት መረጃዎችን, መፅሀፎችን, ኖቶችን, ትምህርታዊ ቪዲዮዎችን ሁሉንም በቀላሉ እንዲያገኙ ታስቦ የተዘጋጀ ቻናል ነው::
ለማንኛውም መልዕክት
@Nextmis
@Nextmis

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-27 12:49:14 የደቡብ ክልል እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።

በሁለቱ ክልሎች ውሳኔ መሰረት የማለፊያ ነጥብ ፦

ለወንዶች 41፣
ለሴቶች 40 እና
ለአይነ ስውራን 39 ሆኖ ተወስኗል።

በዚህ መሰረት ፦ በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሁለቱም ክልሎች ለፈተና ከተቀመጡ ከ257 ሺህ በላይ ተማሪዎች 187 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎች ወደቀጣይ ክፍል የሚያሳልፋቸውን ውጤት አምጥተዋል።

ለፈተና ከተቀመጠው አጠቃላይ ተማሪ ቁጥር ሲታይ ከ73 በመቶ በላይ ተማሪዎች አልፈዋል።

በተለየ መልኩ ከጸጥታ ጋር በተያያዘ በአሉታዊ ጫና ውስጥ ሆነው የተማሩና ለፈተና የተቀመጡ የደራሼ ልዩ ወረዳ ተማሪዎችን ውጤት በተለየ መልኩ ታይቷታ።

በዚህም መሰረት ፦

ለወንዶች 39፣
ለሴቶች 38 እና
ለአይነ ስውራን 37 ሆኖ ተወስኗል።

የሁለቱ ክልሎች ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ጀምሮ መውሰድ ይችላሉ ተብሏል።

የደራሼ ልዩ ወረዳ ተማሪዎች ግን ውጤታቸው በእጅ የሚሰራ በመሆኑ የ1 ሳምንት ጊዜ ዘግይቶ ይደርሳል እስከዛው በትዕግስት እንዲጠባበቁ መልዕክት ተላልፏል።
https://t.me/Timhrtministers
765 viewsedited  09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 10:53:15
#Update

የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 11/2015 ዓ.ም በሁለት ዙር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

በሁለት ዙር በሚሰጠው ፈተና ከ984 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ የአገልግሎቱ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ረዲ ሽፋ ለኦቢኤን ተናግረዋል።

ፈተናውን ከሚወስዱት ውስጥ 622,739 የሚሆኑት የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ሲሆኑ ቀሪዎቹ 361,279 ፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች መሆናቸውን ገልጸዋል።

የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በመጀመሪያው ዙር ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 03/2015 ዓ.ም ፈተናው እንደሚሰጣቸው ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሁለተኛው ዙር ከጥቅምት 08 እስከ 11/2015 ዓ.ም ፈተናውን እንደሚወስዱ አስረድተዋል።

የዘንድሮው ፈተና በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጥ ሲሆን ፈታኞቹም የዩኒቨርሲቲ መምህራን መሆናቸው ተገልጿል።

ፈተናው ከዚህ በፊት ይሰጥ የነበረበትን አራት ኮድ እንዲጨምር መደረጉን የገለጹት ዳይሬክተሩ፤ ፈተናው ተዘጋጅቶ እየታተመ መሆኑን ጠቁመዋል።

https://t.me/Timhrtministers
1.8K views07:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 09:40:29
#MoE

የትምህርት ሚኒስቴር "የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ፕሮግራሞችና ሥርዓተ ትምህርት ቀረፃ፣ ክለሳና ማፅደቂያ መመሪያ"ን አጽድቋል።

መመሪያው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ፕሮግራሞችና ሥርዓተ ትምህርቶች ከዓለም አቀፍ፣ ከቀጠናዊ እና ከአካባቢያዊ የልማት አጀንዳዎች ጋር ተጣጥመው እንዲሄዱ ለማድረግ ያስችላል ተብሏል።

ሚኒስቴሩ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚከፍቷቸውን ፕሮግራሞች ከሀገሪቱ የልማት ቀረፃና አስፈላጊነት አንፃር ተጠንተው ሲቀርቡለት አግባብነታቸውን አረጋግጦ የማጽደቅ ስልጣን እንዳለው በአዋጅ ተደንግጓል።

መመሪያ ቁጥር 917/2014 ሆኖ በፍትህ ሚኒስቴር የጸደቀውን አዲሱን መመሪያ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተግባራዊ እንዲያደርጉ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተፈርሞ መሰራጨቱ ታውቋል።

አምስት ክፍሎች እና 22 አንቀጾች ያሉት አዲሱ መመሪያ፤ ከነሐሴ 01/2014 ዓ.ም ጀምሮ የጸና እንደሆነ ተደንግጓል።

(መመሪያው ከላይ ተያይዟል)
https://t.me/Timhrtministers
2.0K views06:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 23:03:00 ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ የመውጫ ፈተና መሰጠት እንደሚጀመር ይታወቃል።

ለመሆኑ ፈተና በመፈተን ብቻ የትምህርት ጥራት ማምጣት ይቻላል ? ትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ጉዳይ ምላሽ አለው።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ለብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ (ኢቲቪ) የተናገሩት ፦

" የትምህርት ጥራት ፈተና ብቻ በመስጠት የሚሳካ ፤ የሚረጋገጥ ነገር አይደለም።

በአጠቃላይ ግን በትምህርት እና ስልጠና ዘርፉ በተለይም በትምህርቱ ዋና ችግር አለ ተብሎ የተለየው ዋና የትምህርት ሴክተሩ ስብራት ነው ተብሎ የተለየው ትምህርታችን ጥራትም ተገቢነትም ጎሎታል።

ስለዚህ አስመርቀን የምናስወጣው በሙሉ ባይባልም የጥራት ፣ የብቃት ችግር አለበት ይሄንን መፍታት ያስፈልጋል።

ለዚህ የሚሆን በሁሉም ደረጃ ከግብዓትም ጋር ከሂደቱም ጋር የሚያያዝ እንደዚሁም ውጤቱን ከማረጋገጥ ጋር የሚያያዝ ስራዎች መሰራት አለባቸው ተብሎ በመንግስት ቁልፍ የሪፎርሞች ተጀምረዋል አንደኛው ከመውጫ ፈተና ጋር የሚያያዝ ነው።

ይሄ የመውጫ ፈተና በዋናነት የሚመለከተው የመጀመሪያ ዲግሪ ምሩቃንን ነው ሁለተኛ ዲግሪ እና ሌሎችን አይመለከትም የሚጀምረው በ2015 ሰፋ ብሎ ነው እንጂ ከዚህ በፊትም የተጀማመሩ ስራዎች አሉ የተጀመሩ ፕሮግራሞች አሉ።

ዋናው ቁም ነገሩ በግብአት ደረጃ ጥራቱን ማረጋገጥ ያስፈልጋል የምሩቁን ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባውን የመማር ማስተማር ሂደቱ ጥራትን በሚያረጋግጥ መልኩ መምራት እና መስጠት ያስፈልጋል።

በጥሩ ግብዓት ከተደገፈ እና ጥሩ ሂደት ካለው በውጤቱ ማረጋገጥ ይገባል ከሚል መነሻ የተጀመረ የሪፎርም ስራ ነው።
https://t.me/Timhrtministers
https://t.me/Timhrtministers
2.6K viewsedited  20:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 11:40:12 በአዲስ አበባ ትምህርት መስከረም 9 ይጀምራል

በ2015 የትምህርት ዘመን 8ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሆኖ ይሰጣል።

የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ የሚኒስትሪ ፈተና እና የ8ኛ ክፍል ፈተና ሀገር አቀፍ ሆኖ ይሰጣል።

የ2015 ዓመት መደበኛ የትምህርት ዘመን መስከረም 9 ቀን እንደሚጀመር የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።

በ2015 የትምህርት ዘመን አዲሱ ስርዓተ ትምህርት ወደ ሙሉ ትግበራ እንደሚገባ የቢሮው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አበበ ቸርነት ተናግረዋል።
በአንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ተቋማት ላይ በተመረጡ ትምህርት ቤቶች የሙከራ ትግበራ በ2014 የትምህርት ዘመን ላይ የተከናወነ ሲሆን አዲሱ ስረዓተ ትምህርት በ2015 የትምህርት ዘመን ሙሉ በሙሉ በሁሉም የመንግስትም ሆነ የግል ትምህርት ቤቶች ተግበራዊ ይሆናል።

በሌላ በኩል በቅድመ አንደኛ ደረጃ እና በአጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ እንዲሁም በከፊል በተወሰኑ ትምህርት ቤቶች ላይ በ2015 የትምህርት ዘመን የሙከራ ትግበራ ከተከናወነ በኃላ በ2016 ዓ.ም ወደ ሙሉ ትግበራ እንዲገባ ይደረገል።

በ2015 ዓመት የትምህርት ዘመን 6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፣የ8ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ እንዲሁም 12ኛ ክፍል የሁለተኛ ደረጃ የማጠቃለያ ፈተና ይሰጣል ፡፡በ2015 የትምህርት ዘመን ላይ ወደ ሙሉ ትግበራ የሚገባው አዲሱ ስርዓተ ትምህርት የጥራት ደረጃውን ጠብቆ እንዲተገበር በተለይ የግል እና መንግስታዊ ያልሆኑ ትምህርት ተቋማት ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ ለማድረግ እና ከዚህ ቀደም በስርዓተ ትምህርት ትግበራ ላይ የነበሩ ጉድለቶችን ለማረም በጋራ መሰራት እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

የመጽሀፍ ስርጭትን በተመለከተ ትምህርት ከመጀመሩ በፊት በተማሪዎች እጅ እንዲደርስ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አቶ አበበ ቸርነት ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
https://t.me/Timhrtministers
2.5K viewsedited  08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 13:57:49
#መውጫ_ፈተና

ትምህርት ሚኒስቴር በሚቀጥለው ዓመት 2015 ትምህርት ዘመን የሚጀምረውን የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና የአፈፃፀም መመሪያን በማጸደቅ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማሰራጩት ይታወቃል።

ለመሆኑ መመሪያው ምን ይላል ?

- የመውጫ ፈተናው የመጀመሪያ ዲግሪ የመንግስት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ይመለከታል።

- መመሪያው የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ እና ሀገሪቱ የምትፈልገውን የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት ከሚከወኑ የማስፈፀሚያ ስልቶች አንዱ ነው።

- የመውጫ ፈተናውን ወስዶ 50 በመቶ ውጤት ማምጣት ያልቻለ ተማሪ መመረቅም ሆነ ከተማረበት ዩኒቨርሲቲ የዲግሪ ሰርተፊኬት ማግኘት አይችልም።

- በመውጫ ፈተና 50 በመቶ ማምጣት ያልቻለ ተጨማሪ ጊዜ ወስዶ በአግባቡ አጥንቶ ፈተናውን 50 በመቶ እና ከዛ በላይ አምጥቶ ማለፍ እንዲችል ለሁለት ተጨማሪ ጊዜ የመፈተን እድል ይሰጠዋል። ተፈታኙ እድሉን መጠቀም ያለበት የመጀመሪያውን ፈተና ከወሰደ በ3 ዓመታት ጊዜ ውስጥ ብቻ ነው።

- አንድ ተማሪ ለምርቃት ብቁ የሚሆነው የመውጫ ፈተናውን ካለፈ ብቻ ሲሆን 3 ጊዜ ተፈትኖ የማለፊያ ነጥብ ያላገኘ ተፈታኝ ከብሄራዊ የብቃት ማዕቀፍ ተገቢው ማስረጃ ይሰጠዋል።

- የቅድመ ምረቃ የመውጫ ፈተና እንደየትምህርት ፕሮግራሙ ባህሪ በዓመት ሁለቴ እና ከዛም በላይ ሊሰጥ ይችላል።

- የመውጫ ፈተና የሞያ ማህበራት ተጠናክረው የሞያ ፍቃድ ፈተና መስጠት እስከሚጀምሩ በትምህርት ሚኒስቴር ወይም ውክልና በሚሰጠው ተቋም ይዘጋጃል።

መውጫ ፈተና ላይ ሚካተቱ ኮርሶችን በተመለከተ በመጪው ጊዜ በየትምህርት መስኩ በሚዘጋጁ የማስፈፀሚያ ዝርዝር መመሪያዎች ይለያል መባሉን ሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ ትምህርት ሚኒስቴርን ዋቢ አድርጎ ካሰራጨመው ዘገባ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
2.7K viewsedited  10:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 22:33:47
ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመስጠት የሚያስችላቸውን ዝግጅት እንዲያደርጉ የትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል፡፡

የዩኒቨርሲቲዎች የ2015 ዓ.ም የትምህርት ካላንደር ከመስከረም 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጠውን የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ታሳቢ ያደረገ መሆን እንደሚገባው ተገልጿል።

ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 17/2015 ዓ.ም በሁሉም የዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ምንም አይነት መደበኛ ተማሪ እንዳይገኝ እና ለፈተና ማቆያ ቦታ እና የምግብ አቅርቦት ዝግጅት እንዲደረግም ትእዛዝ ተላልፏል።

ከፈተና ደህንነት እና አቅርቦት ጋር በተያያዘ የፈተናውን አሰጣጥና ደህንነት የሚቆጣጠር በዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የሚመራ ዋና ግብረ ኃይል እንዲሁም በካምፓስ ኃላፊ የሚመራ ንዑስ ግብረ ኃይል እንዲደራጅም ሚኒስቴሩ መመሪያ አስተላልፏል፡፡

የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ከመስከረም 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ መገለጹ ይታወሳል።

https://t.me/Timhrtministers
2.4K viewsedited  19:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 10:19:13
የዩንቨርሲቲ መግቢያ ፈተናው ለሚሰጥባቸው የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትምህርት ሚኒስቴር የላከው ደብዳቤ

ተፈታኝ ተማሪዎች በሁለት ዙር ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ በመግባት ፈተናቸውን የሚወስዱ ሲሆን ሁሉም የመንግስት ዩንቨርሲቲዎች የመጀመሪያው ዙር ፈተና ከሚጀመርበት ቀን አንስቶ እስከ ሁለተኛው ዙር ፈተና ማለቂያ ማለትም ጥቅምት 17/2015 ድረስ መደበኛ ተማሪዎቻቸውን አያስተናግደም።
https://t.me/Timhrtministers
https://t.me/Timhrtministers
2.4K viewsedited  07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 10:19:13
በአዲሱ ረቂቅ የትምህርት ፖሊሲ ከቅድመ አንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል ትምህርት ነፃ እና አስገዳጅ ይሆናል፡- የትምህርት ሚኒስቴር
****

በአዲሱ ረቂቅ የትምህርት እና ጥናት ፖሊሲ ከቅድመ አንደኛ እስከ ስምንተኛ ከፍል የሚሰጥ ትምህርት ነፃ እና አስገዳጅ እንደሚሆን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

በአዲሱ የትምህርት ፍኖታ ካርታ ግኝት መሰረት ዜጎች ከቅድመ አንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል በግዴታ እንዲማሩ ለማስቻልና የትምህርት አሰጣጥ ሂደቱን የተሳለጠ ለማድረግ አጠቃላይ የትምህርት ረቂቅ አዋጅ ተግባራዊ እንደሚደረግ በሚኒስቴሩ የስርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ ክፍል ኃላፊ ዶ/ር ቴዎድሮስ ሸዋረገድ በተለይ ለኢቢሲ ሳይበር ሚዲያ ገልጸዋል።

ፍኖተ ካርታውን ለማዘጋጀት ሲሞከር የትምህርት ዘርፉ ያለበትን ሁኔታ ሊያሳይ የሚያስችል ጥናት መደረጉን የተናገሩት ኃላፊው፤ መንግስት ለትምህርት ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና ጥራት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት በአዲስ መልክ ፍኖተ ካርታ አዘጋጅቶ ወደ ትግበራ መግባቱን ገልፀዋል።
https://t.me/Timhrtministers
https://t.me/Timhrtministers
2.2K viewsedited  07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 11:18:27
የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከመስከረም 30 2015 ዓ.ም ጀምሮ በ2 ዙር እንዲሰጥ መታቀዱን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

የ2ዐ14 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲዎች እንዲሰጥ መወሰኑ ይታወቃል፡፡

ፈተናው ከመስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በሁለት_ዙር እንዲሰጥ መታቀዱን በትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ተፈርሞ ለ42 ዩኒቨርሲቲዎች በተላከውን እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ ትክክለኛነቱን ባረጋገጠው ደብዳቤ መመልከት ችለናል።

በዚሁ መሠረት ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ዩኒቨርስቲዎች ፦

1. ምንም አይነት የመደበኛ ተማሪ በግቢ እንዳይኖር እንዲያደርጉ፤

2. በቀጣይ በሚገለጸው ተማሪ ቁጥር ልክ ምግብ እንዲቀርብ ዝግጅት እንዲያደርጉ፤

3. ለፈተናዎች ማቆያ ቦታ እንዲዘጋጅ እና

4. የፈተናውን አሰጣጥና ደህንነት የሚቆጣጠር በፕሬዚዳንት የሚመራ ዋና ግብረ-ኃይልና በየካምፓሶቹ በዲን /ካምፓስ ኃላፊ የሚመራ ንዑስ ግብረ-ኃይል እንዲያደራጁ መልዕክት ተላልፎላቸዋል።

ዩኒቨርሲቲዎች የ2ዐ15 የአካዳሚክ ካላንደር የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና ወቅት (ከመስከረም 28 - ጥቅምት 17) ታሳቢ በማድረግ እንዲያዘጋጁ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ አሳስበዋል።
https://t.me/Timhrtministers
https://t.me/Timhrtministers
2.3K viewsedited  08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ