2022-12-29 08:55:54
❥:::::::::በትዳር ዉስጥ::::::::❥
አንዲት ሴት ባል አግብታ ከባልዋ እናት ጋር ትኖር ነበር. በአጭር ግዜውስጥ የባልየው እናት እና ሚስትዮው በሆነው ባልሆነው መጣላት ጀመሩ.
በሀገሪቱ ህግ መሰረት ደግሞ ማነኛዋም ሚስት ለ ባልዋ እናት የመታዘዝ እና የመገዛት ግዴታ አለባት. የባልየው እናትየባህል አጋጣሚ ተጠቅመው ያስቃይዋት ጀመሩ. በዚ ምክንያትም ባልየው ስላም አጣ እቤታቸውም ሰላም ያጣ ሆነ. ይሄንን መቃቃም ያቃታት ሚስትም የባህል መድሃኒት የሚሸጥ የአባትዋ ጋደኛ ጋር እርዳታ ፍለጋ ሄደች.
የለችበትን ከባድ ሁኔታ አስረድታም መርዝ እንዲስጣት እናስትሞት ካለችበት ስቃይ እንዲገላግላት እያለቀሰች ለመነቺው.
ሰውየውም ካዳመጣት ቦሃላ ስላሳዘነቺው ሊረዳት ፍቃደኛ ሆነ. ´እንዲህም አላት´ የባልሽ እናት ሰው እንዳይጠረጥር መድሃኒቱ ከረጂም ግዜ ቦሃላ ነው ሚገላት. ´በነዚ ወራቶች ውስጥ አንቺ ጥሩ ጥሩ ምግብ እያበስልሽ እዛ ውስጥ እየጨመርሽ ስጫት, የፈለገችውን እርጊላት ታዘዥያት እንደ እናትሽ ተንከባክብያት. ቁታሽንምእናትዋ ተቆጣጣሪ ብሎ እስጠንቅቆ መክራት, ሳምንታት አለፉ ሚስትየውም ጥሩ ምግብ ማብሰል እና እንደ መንከባከብ ጀመረች, ባለ መድኃኒቱ ሰውየ ያላትን እያስታወስች ንዴትዋን መቆጣጠር ቻለች, በሆነው ባልሆነው መቆጣትም አቆመች .የባልየው እናትም።
ለሚስትየው ያላቸው አመለካከት ተቀይሮ እንደልጃቸው ማየት ጀመሩ. ለጋደኘቻቸውን እና ለዘመዶቻቸው ጥሩ ምራት እንደ አገኙ መናገር ጀመሩ ለ 7 ወራትም እቤታቸው በፍጹም ደስታ ተሞልቶ አለፈ. አንድ ቀን ሚስትዮ ባለ መድኃኒት ሰውየው ጋር ሂዳ እንደ መጀመሪያ ግዜው እያለቀሰች መርዙን ማክሸፍያ መድኃኒት እንዲሰጣት ለመነቺው እንዲህም አለቺው"
የባሌ እናት እኔ እንዳሰብካት ሴት አልነበረችም ልክ እንደልጅዋ ነው ምታየኝ አሁን በጣም ተቀይራለች እንድትሞትብኝ አልፈልግም ታስፈልገኛለች" መድኃኒት ቀማሚው እንዲህ አላት" ምንም የማያሳስብሽ ነገር የለም የሰጠሁሽ መርዝ ሳይሆን ጤናዋን የሚያሻሽል ቢታሚን ነው, መርዙ ያለው አእምሮሽ ውስጥ ነበር እሱም በስጠሻት ፍቅር ከሽፍዋል አላት.
ጥላቻን #ፍቅር ነው ሚያሸንፈው, ለፍቅር ደግሞ መስዋዕት መክፈል እድለኝነት ነው አላት።..
ከፁሁፉ መልካም ነገር እንደተረዳቹ ተስፍ አለኝ ። በዚዉ አጋጣሚ እህቶቼ ለባሏቻቹ እናት መልካም ሰዉ እና መልካም ፍቅር እድኖራቹ መልክቴን መስተላለፍ እወደለዉ። بارك الله فيكم
#ሼር በማድረግ አስተላልፉ
:::::::ቴሌግራማችን:::::::
╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ❞
╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ❞
748 views05:55