Get Mystery Box with random crypto!

ትምህርት በቤቴ🔝

የቴሌግራም ቻናል አርማ temhert_bebete — ትምህርት በቤቴ🔝
የቴሌግራም ቻናል አርማ temhert_bebete — ትምህርት በቤቴ🔝
የሰርጥ አድራሻ: @temhert_bebete
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.20K
የሰርጥ መግለጫ

A channel created for sharing
🔺study tips,
🔺short notes,
🔺tutorials,
🔺educational news,
🔺life tips and some motivational quotes ...
For comment @Tmhert_bebete_info_bot
Buy ads: https://telega.io/c/temhert_bebete

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2022-10-03 11:53:29
ዘንድሮ ከ900,000 በላይ ተማሪዎች ለፈተና ይቀመጣሉ

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ባለፉት 6 ዓመታት ከፈተና ስርቆትና የተዛቡ መረጃዎች ስርጭት ጋር ተያይዞ ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ችግር ገጥሞት የነበረ መሆኑን ገልጾ ዘንድሮ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ተፈታኞች ከቀጣይ ሰኞ ጀምሮ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲፈተኑ እንደሚደረግ ገልጿል።

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ብሏል።

የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተናን ለመስጠት ዝግጅት #መጠናቀቁንም ሚ/ሩ አስታውቋል።

ይሁን እንጂ ዘንድሮ ከ900,000 በላይ ተማሪዎች ለፈተና የሚቀመጡ በመሆኑ ይህንን ቁጥር በአንድ ጊዜ ማስተናገድ ባለመቻሉ በሁለት ዙር ፈተናው እንደሚሰጥ አስረድቷል።

የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ከመስከረም 26-28 ወደሚፈተኑባቸው ዩንቨርሲቲዎች የሚገቡ ሲሆን ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 02 ፈተና ወስደው ከጥቅምት 03 ጀምሮ ወደመጡበት እንደሚመለሱ ተጠቅሷል።

በ2ኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከጥቅምት 5 አስከ ጥቅምት 6 ወደ ዩንቨርሲቲዎች የሚገቡ ሲሆን ከጥቅምት 8 እስከ ጥቅምት 11 ፈተና የሚወስዱ ይሆናል።

ተማሪዎች ለፈተና ሲመጡ ተንቀሳቃሽ ስልኮችን እና ሌሎችም ስጋት ሊፈጥሩ የሚችሉ ቁሶችን መያዝ እንደማይችሉ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

በተለያዩ አካባቢዎች ከሰላምና ፀጥታ ጋር ተያይዞ መፈተን የማይችሉና ከሀገር የወጡ የኮሚኒቲ ተማሪዎች በአጠቃላይ 56,000 ተማሪዎች ሲሆኑ በቀጣይ ሁለተኛ ዙር ፈተና እንደሚዘጋጅላቸው ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁን ኢብኮ ዘግቧል።

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
6.0K views08:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 18:23:42
በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የኦንላይን ትምህርት ሊሰጥ ነው።

የትምህርት ሚኒስቴር በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የኦንላይን ትምህርት ለመስጠት የዕውቅና ፍቃድ ጥያቄን ጨምሮ የተለያዩ ዝግጅቶች ማድረጉ ተገለጸ፡፡

የት/ት ሚኒስቴር ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመነጋገር ኢ-ለርኒንግን ለማስፋፋት ፕሮጀክት ቀርጾ የ22 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ማግኘቱንና በአሜሪካው አሪዞና ዩኒቨርሲቲ አማካይነት መርሃ ግብሩን ዕውን ለማድረግ ሥራዎች መጀመራቸው ታውቋል፡፡

በኢትዮጵያ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በርቀት የትምህርት መደብ የተወሰኑ ት/ቶችን ቢሰጡም በመደበኛነት የኦንላይን ትምህርት ለመስጠት የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ፈቃድ የሰጠው የትምህርት ተቋም የለም።

ትምህርት ሚኒስቴር በተያዘው ዓመት አምስት ዩኒቨርሲቲዎች በኦንላይን ት/ት ለመስጠት ፈቃድ እንዲያገኙ ለማድረግ ማቀዱን የገለጸ ሲሆን ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ደረጃ በደረጃ የኦንላይን ትምህርት እንዲሰጡ መታቀዱ ተገልጿል፡፡

የኦንላይን/E-Learning ት/ቱ ዋነኛ ትኩረቶች፦

• ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች የሚጠቀሙበት የትምህርት አማራጭ በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ማቅረብ።

• ሁሉም መምህራን በኦንላይን የመማር ማስተማር የትምህርት ዘዴ ተጨማሪ ስልጠና ይወስዳሉ።

• የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በኦንላይን ለመማር የሚችሉበት ሰልጠና ይሰጣቸዋል፡፡

የኦንላይን ትምህርትን ለማስፋፋት የት/ት ሥልጠና ባለስልጣን ከዚህ ቀደም ባወጣው መመርያ ፈቃድ የወሰዱ ውስን የግል ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ እንደነበሩ ተገልጿል፡፡

የትምህርት ተደራሽነትን ለማስፋት ዩኒቨርሲቲዎች ቴክኖሎጂን ተጠቅመው የኦንላይንን ትምህርትን ለማጠናከር የመሠረተ ልማቶችንና ፋሲሊቲዎችን የማሟላት ሥራዎች መጀመራቸው ተገልጿል።

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
3.7K views15:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 18:01:49
Get your Spouse VISA for , UK , Netherlands and AMERICA

Programs

spouses
Study
visit
work

No exam required for students
Skype interview for work seek program
Limited seats available
no need of pre-payment

Office - A.A 22 golagol segen building off.No. 24
- Hawasa Piyasa London cafe mall building Off.No. 302/300

Call us +251468979 676/ +251904125320
+251 468 219 651/ +251904125120
WhatsApp +251904125320
+251924007162


24/7 WhatsApp service &
8 hour hotline call service
@Novatr3
@Arewether

www.novatravelet.net

Finding your destination
3.5K views15:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 16:02:01
የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈታኞች በፈተና ወቅት ሊያሟሏቸው የሚገቡ ተግባራት

@Temhert_Minister
@Temhert_Minister
3.7K views13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 07:00:30 መታገስ!

ታላቅነት በአንድ ቀን አይገነባም! በአንድ ቅፅበት ሊፈርስ ግን ይችላል። የባቢሎን ግንብን ለመገንባት አንድ ትውልድ ፈጅቷል፤ ለማፍረስ ግን ቀናት አልፈጀም።

እስከዛሬ የገነባኸውን ምርጥ ስብዕና እንድታጣ የሚያደርጉ ብዙ የሚያናድዱ፣ ራስህን እንድትጠላ፣ ተስፋ እንድትቆርጥ የሚያደርጉ ፈታኝ ነገሮች በየጊዜው ይገጥሙሀል። ማንነትህን የምታሳየው በሰላሙ ጊዜ አይደለም ከባዱን ወቅት ታግሰህ በማለፍ ነው እንጂ። አለበለዚያ ከዜሮ ትጀምራለህ!

inspire_ethiopia

@temhert_bebete
@temhert_bebete
5.5K views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-01 18:01:14
Get your Spouse VISA for , UK , Netherlands and AMERICA

Programs

spouses
Study
visit
work

No exam required for students
Skype interview for work seek program
Limited seats available
no need of pre-payment

Office - A.A 22 golagol segen building off.No. 24
- Hawasa Piyasa London cafe mall building Off.No. 302/300

Call us +251468979 676/ +251904125320
+251 468 219 651/ +251904125120
WhatsApp +251904125320
+251924007162


24/7 WhatsApp service &
8 hour hotline call service
@Novatr3
@Arewether

www.novatravelet.net

Finding your destination
6.5K views15:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-01 13:47:57
ትምህርት ሚኒስቴር በሁለት ዙር የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል።

ፈተናው ከመስከረም 26 እስከ ጥቅምት 13/2015 ዓ.ም ቆይታ ይኖረዋል።

የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ከመስከረም 26 እስከ ጥቅምት 04/2015 ዓ.ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ከጥቅምት 05/2015 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 14/2015 ዓ.ም ፈተናውን ይወስዳሉ።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
7.3K views10:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-01 12:09:33
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሚሰጥበት ወቅት በዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙ ተማሪዎች ተቋማቱን ለቀው እንዲወጡ የትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስቀምጧል

ይሁን እንጂ ጦርነትና የፀጥታ ችግር ካለባቸው የትግራይ፣ አማራ እና ኦሮሚያ አካባቢዎች የመጡ ተማሪዎች ወደ ቤተሰብ ለመሄድ እንደማይችሉ እና ውጪ ለመቆየት አቅም እንደሌላቸው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች ህብረት ገልጿል።

ፈተና እስከሚጠናቀቅ ተማሪዎቹ የሚቀመጡበት ቦታ እንዲመቻችላቸው ህብረቱ ለትምህርት ሚኒስቴር ጥያቄ ማቅረቡን የህብረቱ ፕሬዝዳንት ሚካኤል ያቦነሽ ለቲክቫህ ተናግሯል።

ህብረቱ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመሆን ተማሪዎቹ ብሔራዊ አደጋና ስጋት ኮሚሽን ማዕከላት እንዲቆዩ ጥያቄ ቢያቀርቡም ኮሚሽኑ እንደማይችል ገልጿል።

በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲዎች የቴሌቪዥን ማሳያ ክፍሎችና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ተማሪዎቹ የሚቆዩበት መመሪያ እንዲሰጥ ህብረቱ ጠይቋል።

ተማሪዎቹ ለፈተና አሰጣጡ ስጋት እንዳይሆኑ ፈተናው በሚሰጥበት ወቅት ከማደሪያቸው እንዳይወጡና ምግብም ከተፈታኞቹ በኋላ እንዲመገቡ በማድረግ ችግር እንዳይፈጠር ህብረቱ እንደሚሰራ የህብረቱ ፕሬዜዳንት ለቲክቫህ ገልጿል።

ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 17/2015 ዓ.ም በሁሉም የዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ምንም አይነት መደበኛ ተማሪ እንዳይገኝ የትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ ማስቀመጡ ይታወሳል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
6.9K views09:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-30 20:38:15 12ተኞች ግቢ ሳትገቡ ማወቅ ያለባችሁ እያንዳንዱ የፈተና አፈፃፀም

መንግስት ለአተገባበር የነደፈው ፕላን ይሄንን ይመስላል

ለፈተና አስተዳደር ሥራ ያግዝ ዘንድ የተለያዩ የግብረ ኃይል አደረጃጀቶችን፣ የተፈታኞችና የፈተና አስፈጻሚዎች መብት፣ ግዴታ፣ የተፈቀዱና የተከለከሉ ነገሮች የያዘ ማኑዋል ነው፡፡

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት


መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
8.4K views17:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 19:30:29
የስራ እድል

የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ፦በልዩ ሁኔታ የስራ ቅጥር ለመፈፀም መሰረታዊ መረጃ መሰብሰቢያ ቅፅ

ከ 2013 ዓ.ም ጀምሮ

በኮምፒውተር ሳይንስ

ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ

ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ

ማኔጅመንት ኢንፎርሜሽን ሲስተም

እና ተዛማጅ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቁ ተማሪዎች፡፡

በሶፍትዌር ልማት ልዩ ተሰጥኦ ወይም አቅም ያላቸሁ ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ (Link) በመጫን መሰረታዊ መረጃችህን የያዘ ሲቪ ከሁለት/2/ ገፅ ያልበለጠ እስከ መስከረም 30/2015 እንድታያይዙ እንጠይቃለን (pdf ፋይል)

ማስታወሻ፡- የትምህርት ማስረጃችሁን ማያያዝ አይጠበቅባቹህም
የማመልከቻ ሊንኩ

https://www.insa.gov.et/web/guest/vacancy

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete
8.8K views16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ