Get Mystery Box with random crypto!

ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ

የቴሌግራም ቻናል አርማ sufiyahlesuna — ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ
የቴሌግራም ቻናል አርማ sufiyahlesuna — ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ
የሰርጥ አድራሻ: @sufiyahlesuna
ምድቦች: መኪናዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.08K
የሰርጥ መግለጫ

╔════◈◉◈════╗
                     أهل السنة والجماعة
            ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⚪️አህለሱና ወልጀመዓህ ስንል የሰለፎችንና የኸለፎችን የግንዛቤ ዘይቤ የሚከተሉ ማለት ነው።
🔴ይህ መንገድ ሌሎች የኢስላም አስተሳሰብ ተከታዮችን አያከፍርም
🔎አመላካች የሰሪን ምንዳ ያገኛልና ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩልን
╚════◈◉◈════╝

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-25 15:28:29 #ሱፊዮች
■ ኢማም አብዱል ቃሂር አል በጝዳዲ (429 ሂጅራ ያረፉ)-

ታላቁ ኢማም ፣ የነገረ እምነት ምሁራን ማስረጃ ፣ አብዱል ቃሒር አል በጝዳዲ ፣ አላህ ይዘንላቸው ፣ በ“الفرق بين الفرق” በሚለው መጽሐፋቸው ውስጥ ((በዚህ ክፍል ምዕራፎች የመጀመሪያ ምዕራፍ የአህል አል-ሱና ወል-ጀማዓህ ምድቦችን ያብራራል) እንዲህ ይላሉ፦

አህሉ-ሱና ወል-ጀማዓህ-ስምንት ምድብ እንዳላቸው ሊታወቅ ይገባል! ስድስተኛው- መደብ ውስጥ እነዚያ (የዱንያ ምንነት)ተገልጦላቸው የተቆጠቡና ከዓለማዊ ህይወት የራቁ ሱፊዮች ናቸው እነርሱ፦ በተነገራቸው ጊዜ አገናዘቡ ፣ አላህ የወሰነውን ወደው ተቀበሉ ፣ በአነስተኛ ነገር የተብቃቁ ፥ መስሚያ ፣ ማያና ቀልብ እነዚህ ሁሉ(ባለቤታቸው) በበጎም በክፉ በነዚህ ተጠያቂ መሆኑን ያወቁና በብናኝ ክብደት ሚተሳሰቡ መሆኑን የተገነዘቡ ፣ ለቀጠሮውም ቀን መልካም መሰናዶን የተሰናዱ ፣ ንግግራቸው አታላይን ወሬ ከሚገዙ ሰዎች ፍፁም የራቀና በታማኝ ሰዎች የንግግር መስመር በውስጣዊ ገለፃ እና በዒሻራ መንገድ የሚገለፅ ፣ ለይዩልኝ ብለው መልካም ስራ አይሰሩም ፣ በይሉኝታም አይተውም ፣ ሃይማኖታቸው ተውሂድ(አሃዳዊነት) እና ተሽቢህ(ማመሳሰልን) ማስዋሸት ነው ፣ መዝሀባቸውም ወደ አላህ ማስጠጋት፣ በርሱ መመካት እና ለትእዛዙ ተገዢ መሆን ነው - በተሰጣቸው ነገር የረ'ኩና ከመቃወም የራቁ ናቸው 【ይህ የአላህ ችሮታ ነው፡፡ ለሚሻው ሰው ይሰጠዋል፡፡ አላህም የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው።】
1.1K viewsedited  12:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 06:16:52 ዓምደ-ሀገር ሼህ ዓሊ-ጎንደር
==== ✿❀ === ✿❀ ====

በዛሬው ዕለት ለንባብ ቀርቧል!

መጽሐፉ የሼህ ዓሊ-ጎንደርን መዋዕለ-ሕይዎትና የኢትዮጵያን 18/19ኛ ክ/ዘመናትን ይቃኛል።
ሼህ ዓሊ-ጎንደር - ከ18ኛው አጋማሽ እስከ 19ኛው ክ/ዘመን አጋማሽ ነበር የኖሩ፡፡ ወሎ ተወልደው፣ ዓለምን ዙረው፣ በጎንደር ታጠሩ፡፡ በመማር ማስተማር፣ በሥነ-ጽሁፍ፣ በኪነ-ጥበብ፣ በንግድ፣ በሥነ-ምህንድስና፣ በፍልስፍና፣ በምንፍሥና፣ በሥነ-ምድር እና በሥነ-ተፈጥሮ ምርምር፣ በውትድርና እና በአስተዳደር፣ በሌሎች መስኮች ተጨባጭ ዓለማቀፋዊና ሀገራቀፋዊ ትሩፋት አበርክተዋል፡፡ መሠረታቸው ጠብቆ፣ ልህቀታቸው እርቆ ከ፬፻(አራት-መቶ) በላይ የዓለም መዲናዎችን ጎብኝተዋል፡፡ ከሱዳን፣ ከግብጽ፣ ከቱርክ ነገሥታት ጋር ግልጽ(ነጻ) ግንኙነት ፈጥረዋል፡፡ የእንግሊዝን ንግሥት፣ የህንድን መንግሥት፣ የሱዳንን ምስለኔ በአማካሪነት አግዘዋል፡፡ ፋናቸውን በከፊል የኤሮጳና የኤዥያ አህጉራዊ ግዛቶች አዝልቀው አነጥበዋል፡፡

ለኢትዮጵያ መሣፍንትና ንጉሦች ሥነ-መንግሥታዊ ትምህርት በመስጠት፣ ገንቢ ተሞክሮና ምክር፣ ድልብ ዕውቀትና ልምድ በማካፈል ክህሎታትን አበልጽገዋል፡፡ የእርስ-በርስ ግጭቶችን በዕርቅ በማቃለል ደሚቅ አሻራ አሳርፈዋል፡፡ በአጤ ዮሐንስ-፫ኛ፣ በእቴጌ መነን፣ በራስ ዓሊ(ትንሹ/አስጘር)፣ በደጃች ጎሹ እና በአጤ ቴወድሮስ ላይ በጎ አበርክቶ አትመዋል፡፡ በሐበሻ ክርስቲያኖች መካከል “የጸጋ ልጅ”፣ “ቅባት” እና “ተዋህዶ” ተሰኝተው የተከሰቱ ልዩነቶች የእርስ-በርስ እልቂት ከማስከተላቸው በፊት፣ ጣልቃ በመግባት አሸማግለዋል፡፡ የእሥልምና ሊቃውንትን ሕብረትና አስተሳሰብ በአግራሞታዊ የተሀድሶ ሥርዓት አበልጽገዋል፡፡

በአጠቃላይም የዚያንዬዋ ሐበሻ የፍቅር አጉራዋ ሲደርቅ፣ የጥል ካስማዋ ሲደምቅ በመታዘባቸው በትውልዱ ዘንድ ሠላምና አብሮነትን በዕውቀት በማስፋፋት፣ ሥልጣኔና ህብረትን በማስፀናት፣ ፍቅርና ሥርዓትን በጥበብ በመዝራት፣ ጸሎትና ተሲያታቸውን ለሀገር በማበርከት ህልውናዊ ስኬት አፈንጥቀዋል፡፡ ስዊዲናዊው የታሪክ ሊህቅ Sven Rubenson(d-2005) እንደገለፀውም በዘመኑ፦ ‹‹ሰላምና ሥርዓት አስጠባቂ!(Safeguard Peace and Order)›› ተሰኝተው ወላዊ ከበሬታ ተችረዋል፡፡ መጽሐፈ ዓምደ-ሀገር ይኽንን የሼህ ዓሊ-ጎንደርን መዋዕለ-ሕይዎት(በአመዛኙ ዓለማዊ ኑረት)፣ የዘመናቸውን ተዛማጅ ጭብጥ እና ሥነ-ኑረት(Ontology Of history) አጠንጥኖ ይቃኛል!

መጽሐፉ በአዲስ-አበባ፦
~ ጃዕፈር መጽሐፍት መደብር፣ ለገሀር
~ አልተውባ መጽሐፍት መደብር፣ ጎጃም በረንዳ - ይገኛል።
መልካም ንባብ!!!

Kedir Taju

https://t.me/sufiyahlesuna
1.1K views03:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 06:16:19
1.0K views03:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 18:01:21 በአንድ ወቅት ሸይኽ አብዱልወሀብ (ረሂመሁሏህ) ከትላልቅ ኡለማች ጋር ሁነው ወደ ሂጃዝ ፊሰቢሊሏህ ይወጣሉ። ከሳቸውም ጋር ከነበሩት ዐሊም መካከል ሙፍቲ ዘይኑል ዓቢዲን (ረሂመሁሏህ) ይገኙበት ነበር።

እኝህም ሙፍቲ ሸይኽ አብዱልወሀብን እንዲህ በማለት ጠየቋቸው፦"ለምንድን ነው ግን ሰዎች አንተ ጋር ሚሰባሰቡትና የሚወዱክ አንተ ከትላልቅ ኡለሞች አይደለህም ምንድን ነው ሚስጥሩ" አሏቸው ሸይኽ አብዱልወሀብም በዛን ወቅት ምንም መልስ ሳይመልሱ ቀሩ።

ዳዕዋቸውን ጨርሰው ወደ ላሆር ሲመለሱ ኤርፓርቱ ውጭ እነሱን የሚጠብቁ ሁለት መኪኖች ቁመዋል ሙፍቲ ዘይኑል ዐቢዲን ወደ ቤታቸው ሚወስዳቸው መኪና ውስጥ ሲገቡ ሸይኽ አብዱልወሀብ ግን ወደ ራይዎንድ መርከዝ ሚወስዳቸው መኪና ውስጥ ገቡ። ሸይኽ አብዱልወሀብም በመስኮት በኩል ለሙፍቲ ዘይኑል ዐቢዲን እንዲህ አሏቸው፦"ወዴት ነው ምትሄደው" አሏቸው።? "ወደ ቤቴ" አሉ ሙፍቲ ዘይኑል ዐቢዲን
ሸይኽ አብዱልወሀብም "እኔስ ወዴት ነው የምሄደው"? አሏቸው ሙፍቲም ወደ ራይዎንድ መርከዝ አሏቸው በቃ ባለፈው በዳዕዋ የጠየቁኝ ጥያቄ መልስ ይህ ነው አሏቸው"።

https://t.me/sufiyahlesuna
1.3K viewsedited  15:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 19:17:02 ማንኛውም ነገር ላይ ፍርድ ስትሰጥ ከስሜታዊነት ወጥተህ ለመፍረድ ሞክር ፣ አንድን ተግባር በሃሳብ የሚቃረኑህ ወገኖች ስለተገበሩት ብቻ የምትቃወም ከሆነ ፍርድህ ጤነኛ አይደለም ።

* ትላንት የምትጠላቸው ሰዎች ስለሰሩት ስህተት ነው ያልከውን አካል አንተ ስትተገብረው ይህ ተግባር ትክክል ነው ብለህ መስበክ ትጀምራለህ ይህ ከመርህ መራቅ ነው።

* ወሃቢዮች ስልጣን ካገኙ በኋላ ትላንት ሺርክ ነው ሲሉት የነበሩትን የካፊር የበአል ማክበሪያ ቦታዎችን ማፅዳትን የመሳሰሉ ተግባራትን ሲተገብሩ ተመልክተናል ከሱፊዩም ወገን ትላንት ወሃቢዮች ሲሰሩት ስህተት ነው ብለው ዛሬ ያንን ተግባር የሚፈፅሙ አሉ ።
1.3K viewsedited  16:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 08:34:43
https://t.me/sufiyahlesuna
1.4K views05:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 16:00:28
1.5K views13:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 16:00:28 Anti madhabs part two

ጥያቄ ①① ስለ ሰላተተስቢህ አንድ በሉን ?

ኢብኑ ባዝ ⇢ ሰላተተስቢህ መስገድ አይፈቀድም
                       ለምን በዛ የመጡት ሁላ ሀዲሶች
                       የተፈበረኩ(መውዱዕ) ናቸው
ኢብኑ ኡሰይሚን ⇥ መስገድ ክልክል ነው
                                 ምክንያቱም ሀዲሶቹ ሰሂህ
                                 አይደሉም
አልባኒ ↣ ስለ ሰላተተስቢህ የመጡት ሀዲሶች
                   በሁሉም ጠሪቆች ሰሂህ ናቸው

ጥያቄ  ①②  አንድ ሰው ሙሳፊር ለመባል ምን
                      ምን ያክል ርቀት ነው መሄድ ያለበት?

  ኢብኑ ባዝ ⇢አብዛኛው ኡለማ የተስማሙበት
                         80 km ነው
ኡሰይሚን ⇥ ትክክለኛው ራዕይ በርቀት    
                        እንደማይገደብ ነው  ጉዞ ተብሎ
                        በተለምዶ ሚጠራ ሁሉ ሙሳፊር
                        ነው
  አልባኒ ↣ በተለምዶ ጉዞ ሚባል ሁላ የተጓዘ
                   ሙሳፊር  ነው

ጥያቄ  ①③ የጀምዐ ሰላት ለመቋቋም ስንተ ሰው
                       ሰው ነው ሚያስፈልገው ?

ኢብኑ ባዝ ⇢ ቢያንስ 3 ሰውና ከዛ በላይ መኖር
                        አለበት
ኡሰይሚን ⇥ በ3ና ከዛ በላይ ይቻላል
አልባኒ ↣ ለጀመዐ ሰላት የሚያስፈልገው ቁጥር
                  ያክል ለጁምዐም እንደዛ መሆን አለበት

ጥያቄ  ①④ በጁምዐ ቀን የረሱል ﷺ ስም ሲነሳ
                      ምን እናርግ?

ኢብኑ ባዝ ⇢ሳይጮኽ ሰላዋት ማረግ ይፈቀዳል
ኡሰይሚን ⇥ ሀራም የለውም ሳይጮኽ ከተረገ
አልባኒ ↣ ሰለዋት ማረግ ለግው የተባለው ውስጥ
                 ይገባል ( ለዛ ሰለዋት ማረግ አይቻልም)

ጥያቄ  ①⑤  ሰላተል ኹሱፍ መስገድ ሁክሙ
                       ምንድን ነው ?

ኢብኑ ባዝ ⇢ ሱና ሙዐከዳ ነው
ኡሰይሚን ⇥ ፈርዱ ኪፉያ (ከፊሉ ማህበረሰብ
                        ከሰራው በሌላው ላይ የሚወድቅ)
አልባኒ ↣ ግዴታ ነው (በሁሉም)

                        ፆም

ጥያቄ ①⑥ ለሞተ ሰው መፆም  እንዴት ይታያል ?

ኢብኑ ባዝ ⇢ከፉራ፣ ነዝርና የረመዳን ያለበት
                      መፆም ይቻላል
ኡሰይሚን ⇥ የነዝርና የረመዳን ነው ሚቻለው
አልባኒ ↣ የነዝር ብቻ ነው ሚቻለው ሌላ
                  ሌሎቹን መፆም አይበቃም

ጥያቄ ①⑦ አንድ ሰው ስራዬ ብሎ የረመዳን ወር  
                     ካሳለፈ ምን ማረግ አለበት?

ኢብኑ ባዝ ⇢ያለ ኡዙር ያሳለፈ ተውበት አርጎ
                      ቀዳ ማውጣት አለበት
ኡሰይሚን ⇥ ቀዳ ማውጣት አይወጅብበትም
አልባኒ ↣ ስራዬ ብሎ የፈታ ቀዳ ማውጣት
                 የለበትም ቀዳ ያለበት በግብረ ስጋ
                 ፆሙን የፈታ ብቻ ነው ግዴታ ሚሆንበት

                     ጂሀድ

ጥያቄ ①⑧ ካፊሮችን ለመዋጋት ሌላ ካፊርን
                     እገዛ መጠየቅ ይቻላል ወይ?

ኢብኑ ባዝ ⇢ ይቻላል
ኡሰይሚን ⇥ ይፈቀዳል
አልባኒ ↣ ክልክል ነው አይፈቀድም

                  ማል

ጥያቄ ①⑨  ቁርዐን የሚያስቀራ ሰው ገንዘብ
                       መቀበል ይፈቀድለታል?

ኢብኑ ባዝ ⇢ምንም ችግር የለውም
ኡሰይሚን ⇥ ይፈቀዳል
አልባኒ ↣ አይፈቀድም

                          ኒካህ
ጥያቄ ⑳ አንዲት ሴትን ጠሀራ ሳትሆን መፍታት
                 ይቻላል?

ኢብኑ ባዝ ⇢ እንደአብዛኛው እይታና ትክክለኛው
                      ቀውል አይቻልም
ኡሰይሚን ⇥ አይቻልም
አልባኒ ↣ ይቻላል


                     ማጠቃለያ
እሺ የየትኛውን ፈትዋ እንውሰድ? ይህኛው ትክክል ያኛው ስህተት ነው የምንልበት ሙስተዋ ላይ ደርሰናል?  ወይስ የአንዳቸውን እውቀት በመተማመን የሱን እንከተል? እንደዛ ካረግን 5ተኛ መዝሀብ አይሆንም? ታዲያ ከ 4ቱ አኢማዎች አንዱን ከመከተል ጋር ምን አለያየው(እቺ ተቅሊድ ሀራም ለሚሉት ነው እንጂ እነዛ ጋር አይወዳደሩም) ? 

              .......መልሱን ለናንተ.........
Reference
who is Right
According to the quran and sunnah
Ibn baaz, Ibn utaymeen or albani ?

Translated the portion of a book called al- Eejaaz fi badi ......by Dr. Saed bin abdullah al- bareek by Dr. S. Kose  2016

https://t.me/sufiyahlesuna
1.5K viewsedited  13:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 07:36:56 ኡለሞችን መከተል ግዴታ ነው


ማንኛውም ሙስሊም የኢጅቲሃድ ደረጃ እስካልደረሰ ኡለሞችን የመከተልና የመጠየቅ ግዴታ አለበት ፣ ኡለሞችን ፈትዋ ሲጠይቅ በቅድሚያ በኢልማቸውና በተቅዋቸው እስከተማመነ ድረስ እነርሱ ፈትዋቸውን የገነቡበትን " ማስረጃ " የመጥቀስ ግዴታ የለባቸውም ምክንያቱም አንድ ሸሪአን በጥልቀት ያልተማረ ሰው ማስረጃ ሰጠነውም አልሰጠነውም ምንም ለውጥ የለውም ። እርሱ ዘንድ የግንዛቤ መርጃ እውቀቶች ስለሌሉ ማስረጃ ምንም አያደርግለትም ፣ ሰሂህ ሀዲስን ከደካማው ለይቶ የማያውቅ ሰው በሀዲስ እንዲህ ተብሏል ተብሎ ማስረጃ ቢቀርብለት ምን ይጠቅመዋል ምናልባት ማስረጃ አቅራቢው ሰሂህነቱን ደዒፍነቱን ሊያብራራለት ይገባል ልንል እንችላለን ነገር ግን ጥያቄያችን ይህ ማስረጃ አቅራቢ ደካማውን ሃዲስ ሰሂህ ነው ብሎ ቢያቀርብለትስ ይህ ሸሪአ ያልተማረ ሰው መለየት ይችላልን የሚል ነው ስለዚህ ለዚህ ሰው ማስረጃ ማቅረብ ፋይዳ የለውም።

አሏህም ሱብሃነሁ ወተአላ ተራው ህዝብ ላይ ኡለሞችን ፈትዋ መጠየቅን ነው ግዴታ ያደረገው
وَمَآ أَرْسَلْنَا قَبْلَكَ إِلَّا رِجَالًۭا نُّوحِىٓ إِلَيْهِمْ ۖ فَسْـَٔلُوٓا۟ أَهْلَ ٱلذِّكْرِ إِن كُنتُمْ لَا تَعْلَمُونَ
ከአንተም በፊት ወደእነሱ የምናወርድላቸው የኾነን ሰዎችን እንጂ ሌላን አላክንም፡፡ የማታውቁም ብትኾኑ የመጽሐፉን ባለቤቶች ጠይቁ፡፡

አልአንቢያእ

https://t.me/sufiyahlesuna
1.4K views04:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 18:03:25
✧ነብያችን ﷺ ከ1400 አመት በፊት እንዲህ ብለውን ነበር፦

 (( وَالَّذِي نَفْسُ مُحَمَّدٍ بِيَدِهِ، إِنَّ مَا بَيْنَ الْمِصْرَاعَيْنِ مِنْ مَصَارِيعِ الْجَنَّةِ لَكَمَا بَيْنَ مَكَّةَ وَهَجَرٍ، أَوْ كَمَا بَيْنَ مَكَّةَ وَبُصْرَى .))
"ነፍሴ በቁጥጥሩ በሆነችው እምልለሁ በሁለቱ የጀነት በሮች መካከል ያለው ርቀት ልክ በመካና በሐጀር ወይም በመካና በበስራ እንዳለው ርቀት ነው"።

✧በአሁን ሰዐት የሳተላይት ኢሜጂንግ ቴክኖሎጂ እንዳረጋገጠው በሁለቱ ርቀቶች መካከል ማለትም ከመካ እስከ ሀጀርና ከመካ እስከ በስራ ያለው ርቀት ተመሳሳይ ነው።

https://t.me/sufiyahlesuna
1.4K views15:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ