Get Mystery Box with random crypto!

ዓምደ-ሀገር ሼህ ዓሊ-ጎንደር ==== ✿❀ === ✿❀ ==== በዛሬው ዕለት ለንባብ ቀርቧል! | ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ

ዓምደ-ሀገር ሼህ ዓሊ-ጎንደር
==== ✿❀ === ✿❀ ====

በዛሬው ዕለት ለንባብ ቀርቧል!

መጽሐፉ የሼህ ዓሊ-ጎንደርን መዋዕለ-ሕይዎትና የኢትዮጵያን 18/19ኛ ክ/ዘመናትን ይቃኛል።
ሼህ ዓሊ-ጎንደር - ከ18ኛው አጋማሽ እስከ 19ኛው ክ/ዘመን አጋማሽ ነበር የኖሩ፡፡ ወሎ ተወልደው፣ ዓለምን ዙረው፣ በጎንደር ታጠሩ፡፡ በመማር ማስተማር፣ በሥነ-ጽሁፍ፣ በኪነ-ጥበብ፣ በንግድ፣ በሥነ-ምህንድስና፣ በፍልስፍና፣ በምንፍሥና፣ በሥነ-ምድር እና በሥነ-ተፈጥሮ ምርምር፣ በውትድርና እና በአስተዳደር፣ በሌሎች መስኮች ተጨባጭ ዓለማቀፋዊና ሀገራቀፋዊ ትሩፋት አበርክተዋል፡፡ መሠረታቸው ጠብቆ፣ ልህቀታቸው እርቆ ከ፬፻(አራት-መቶ) በላይ የዓለም መዲናዎችን ጎብኝተዋል፡፡ ከሱዳን፣ ከግብጽ፣ ከቱርክ ነገሥታት ጋር ግልጽ(ነጻ) ግንኙነት ፈጥረዋል፡፡ የእንግሊዝን ንግሥት፣ የህንድን መንግሥት፣ የሱዳንን ምስለኔ በአማካሪነት አግዘዋል፡፡ ፋናቸውን በከፊል የኤሮጳና የኤዥያ አህጉራዊ ግዛቶች አዝልቀው አነጥበዋል፡፡

ለኢትዮጵያ መሣፍንትና ንጉሦች ሥነ-መንግሥታዊ ትምህርት በመስጠት፣ ገንቢ ተሞክሮና ምክር፣ ድልብ ዕውቀትና ልምድ በማካፈል ክህሎታትን አበልጽገዋል፡፡ የእርስ-በርስ ግጭቶችን በዕርቅ በማቃለል ደሚቅ አሻራ አሳርፈዋል፡፡ በአጤ ዮሐንስ-፫ኛ፣ በእቴጌ መነን፣ በራስ ዓሊ(ትንሹ/አስጘር)፣ በደጃች ጎሹ እና በአጤ ቴወድሮስ ላይ በጎ አበርክቶ አትመዋል፡፡ በሐበሻ ክርስቲያኖች መካከል “የጸጋ ልጅ”፣ “ቅባት” እና “ተዋህዶ” ተሰኝተው የተከሰቱ ልዩነቶች የእርስ-በርስ እልቂት ከማስከተላቸው በፊት፣ ጣልቃ በመግባት አሸማግለዋል፡፡ የእሥልምና ሊቃውንትን ሕብረትና አስተሳሰብ በአግራሞታዊ የተሀድሶ ሥርዓት አበልጽገዋል፡፡

በአጠቃላይም የዚያንዬዋ ሐበሻ የፍቅር አጉራዋ ሲደርቅ፣ የጥል ካስማዋ ሲደምቅ በመታዘባቸው በትውልዱ ዘንድ ሠላምና አብሮነትን በዕውቀት በማስፋፋት፣ ሥልጣኔና ህብረትን በማስፀናት፣ ፍቅርና ሥርዓትን በጥበብ በመዝራት፣ ጸሎትና ተሲያታቸውን ለሀገር በማበርከት ህልውናዊ ስኬት አፈንጥቀዋል፡፡ ስዊዲናዊው የታሪክ ሊህቅ Sven Rubenson(d-2005) እንደገለፀውም በዘመኑ፦ ‹‹ሰላምና ሥርዓት አስጠባቂ!(Safeguard Peace and Order)›› ተሰኝተው ወላዊ ከበሬታ ተችረዋል፡፡ መጽሐፈ ዓምደ-ሀገር ይኽንን የሼህ ዓሊ-ጎንደርን መዋዕለ-ሕይዎት(በአመዛኙ ዓለማዊ ኑረት)፣ የዘመናቸውን ተዛማጅ ጭብጥ እና ሥነ-ኑረት(Ontology Of history) አጠንጥኖ ይቃኛል!

መጽሐፉ በአዲስ-አበባ፦
~ ጃዕፈር መጽሐፍት መደብር፣ ለገሀር
~ አልተውባ መጽሐፍት መደብር፣ ጎጃም በረንዳ - ይገኛል።
መልካም ንባብ!!!

Kedir Taju

https://t.me/sufiyahlesuna