Get Mystery Box with random crypto!

ራዚኤል ዘኢትዮጵያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ razielethiopia — ራዚኤል ዘኢትዮጵያ
የቴሌግራም ቻናል አርማ razielethiopia — ራዚኤል ዘኢትዮጵያ
የሰርጥ አድራሻ: @razielethiopia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.79K
የሰርጥ መግለጫ

#የህይወት_መፀሀፍ (መፀሀፈ ራዚኤል)
አባታችን አዳም ከገነት ከወጣ ቡሀላ ቅዱሳን መላእክት ያስተማሩት የሰማያተ ሰማይ ብሎም የምድራዊ ሰማያት ሚስጥራትን ጥበባትን ለልጆቹ #ለኢትዮጵያን ማስተማርያ ይሆን ዘንድ በ እግዜብሔር ፍቃድ በድንጋይ ላይ በግእዝ ቋንቋ ፅፎ አስቀመጠላቸው ይህ መፀሀፍ መፃፈ ራዚኤል ብለን የምንጠራው ነው።

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-01 16:32:30
581 viewsMikiyas, 13:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 16:31:53 የቅዱስ መርቆርዮስ ስዕል አድኖው ሲያሸበሽብ የሚያሳይ ምስል ነው።
@razielethiopia
@razielethiopia



583 viewsMikiyas, 13:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 16:31:53 #የቅዱስ_መርቆርዮስ_ታሪክና_ስዕሉ_ባጭሩ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ አገሩ ሮም አስሌጥስ ነው። አባት እናቱ አረማውያን ነበሩ። ቅዱስ መርቆሬዎስ ከተወለደ በኋላ መልአኩ የተናገረው ቃል ሁሉ እንደተፈጸመ ሲያውቅ አባቱ ከነቤተሰቡ አምነው ተጠምቀዋል። የመርቆሬዎስ ስመ ጥምቀቱ “ፕሉፖዴር” ነው፤ ገብረ
እግዚአብሔር ማለት ነው። በጥበብ በፈሪሀ እግዚአብሔር አድጎ አባቱ
ሲሞት የአባቱን ሹመት ወረሰ።
ንጉሱ ዳኬዎስ ይባላል። መምለኬ ጣዖት ነበር።

በርበሮች በጠላትነት ተነስተውበት እንደምን ላድርግ ብሎ የምክር ቃል ሲልክበት መልአኩ በአምሳለ ወሬዛ ቀይህ በሊህ ሰይፍ ይዞ በዚህ ጠላቶችህን ድል ትነሳለህ ደስ ብሎህ በተመለስክ ጊዜ ግን ጌታህ እግዚአብሔርን አስበው ሲለው ታይቶት ነበርና አትፍራ ጌታ ጠላቶቻችንን አሳልፎ ይሰጠናል ብሎት አጽናንቶት ዘመቱ።

መርቆሬዎስም ኃይል ተሰጥቶት ጠላቱን ድል ነስቶ ሲመለስ ከሃዲው ንጉስ ኡልያኖስ ወዲያው ኃይል ለሰጡን ለረዱን ለዓማልክቶቼ በዓል አድርጌአለሁና ፈጥነህ ና ብሎ ላከበት። ሄዶ ሹመት ሽልማትህ ላንተ ይሁን “አንሰ ኢይክህዶ ለአግዚአብሔር አምላኪየ /እኔ ጌታዬን አልክድም/ ላቆመው ጣኦት አልሰግድም በማለቱ የሰው ልጅ ሊሸከመው የማይችለውን መከራ ተቀበለ።

መርቆሬዎስ ከዕረፍቱም በኋላ ብዙ ተአምራትን አድርጓል፤ #ፈረሱ_ለሰባት_ዓመት ወንጌልን አስተምሯል፤ በኋላም አንገቱን ቆርጠው ገድለውታል እንዴት ብሎ የሚገረም የበልአምን አህያ ይጠይቃት፤ እኛስ እስመ አልቦ ነገር ዘይሳኣኖ ለእግዚያብሔር ብለን እንመልሳለን:: ዘኁልቁ 22፡28

በዚያን ዘመን ቅዱስ ባስሊዮስ ንጉሱን ይገስጸው ነበር ። ከዛ ባስሊዮስን አሰረው። ጳጳሱ በታሰሩበት እስር ቤት የቅዱስ መርቆርዮስ ስእል ነበር። ባስሊዪስም ስዕሉ ፊት ይፀልይ ነበር። ከዛም የመርቆርዮስ ስዕል ታጣ። ያ ስዕል ወደ ንጉሱ ኡልያኖስ ቤት ሄዶ በጦር ወግቶ ገደለው። በስዕሉ ላይ ያለው ጦር ጫፍ ላይ ደም ይንጠባጠብ ነበር።

የቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕልም በአዎንታ አንገቱን ዘንበል አድርጎ ምስክርነት ሰጥቷል። ይህም ሊታወቅ ዛሬ በሀገራችን #ኢትዮጵያ_በምድረ_ተጉለት
በስሙ ከታነጸ ቤተ ክርስቲያን ካህናት ደነነ ስዕሉ እያሉ ሲዘምሩ ጎንበስ
ቀና ሲሉ እንደሚታይ ይነገራል።
የሰማዕቱ የቅዱስ መርቆሬዎስ ረድኤቱ፣ በረከቱ፣ አማላጅነቱና ቃል ኪዳኑ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን።

join & share
@razielethiopia
@razielethiopia
511 viewsMikiyas, 13:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 19:35:21
774 viewsMikiyas, 16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 19:35:21 [ሐምሌ 19 የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤልና የቅዱስ ቂርቆስ በዓል]

ከመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ

❖ሐምሌ 19 ዕለት የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል አምላካቸው ክርስቶስን
አንክድም በማለታቸው የፈላ ጋን ውስጥ የተወረወሩት ቅዱስ ቂርቆስና እናቱን
ቅድስት ኢየሉጣ ተራድቶ ያዳነበት በዓል ነው።

❖ ይኸውም የቅድስት ኢየሉጣን ልጅ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ከሐዲው መኰንኑ
ይዞ “ስምኽ ማነው” ብሎ በጠየቀው ጊዜ “ነቅዕ ዘእምዐዘቅት ንጹሕ ወእማይ
ዘኢይማስን ክርስቲያን ስምየ” (ከንጹሕ ዐዘቅትና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውሃ
የተገኘ ስሜ ክርስቲያን ነው ሞክሼ ስም ከፈለግኽ ደግሞ እናቴ የሠየመችኝ
ቂርቆስ ነው) በማለት ክርስትናው መመኪያው የኾነው ይኽ ቅዱስ ሕፃን
መለሰለት፡፡

❖ መኰንኑም ለአማልክት ከሠዋኽ ስታድግ እሾምኻለኊ ክርስቶስን ካድ
ቢለው ቅዱስ ቂርቆስ ግን “የሰይጣን መልእክተኛ ለእውነትም ጠላቷ የኾንኽ
ከእኔ ራቅ” አለው፡፡ መኰንኑም ይኽነን ሰምቶ በመቈጣት የቅዱስ ቂርቆስ
ደሙ እንደ ውሃ እስኪፈስስ ድረስ እንዲጨምቁት እና ጨውና ሰናፍጭ በኹለቱ የአፍንጮቹ ቀዳዳዎች እንዲጨመሩ ቢያደርግበት፤ በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የጠነከረው ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን “ትእዛዝኽ ለጒረሮዬ ጣፋጭ ኾነ ከማርና ከሥኳርም ለአፌ ጣመኝ” እያለ አምላኩ ክርስቶስን አመሰገነ፡፡

❖ መኰንኑ በዚኽ ሳያበቃ እናትና ልጇ በክፉ አሟሟት እንዲሞቱ በማሰብ
የረዘሙና የተሳሉ በእሳትም እንደ ፍም የጋሉ ዐሥራ አራት የብረት ችንካሮች
እንዲመጡ አስደርጎ ሰባቱ በእናቱ አካላት፤ ሰባቱ በሕፃኑ ሰውነት ላይ
እንዲሰካ ቢያስደርግም በጌታችን ትእዛዝ ግለቱ ጠፍቶ እንደ በረዶ
በመቀዝቀዝ ምንም ምን ጒዳት ሳያደርስባቸው ቀረ፡፡

❖ ከዚያም ወደ ወኅኒ ቤት እንዲገቡና እንዲዘጋባቸው አደረገ፤ ከዚያም ሕፃኑና
እናቱ የሚሠቃዩበት ታላቅ መንኰራኲር ለ፵ ቀናት ተሠርቶ ካለቀ በኋላ
ኹለቱንም በደራቁ ራሳቸውን ላጭተው የእሳት ፍሕምን በላያቸው ላይ
ቢያደርጉም የእግዚአብሔር መልአክ ሥቃዮቹን ኹሉ ከእነርሱ አራቀላቸው፡፡

❖ የሕፃኑ ምላስ እንዲቈረጥ አዝዞ ቢያስቈርጠውም ጌታችን ምላሱን
መልሶለታል፡፡ “ወአዘዘ ካዕበ ያፍልሑ ማየ ውስተ ጽሕርት ዐቢይ ወይደይዎሙ
ለሕፃን ቂርቆስ ወለእሙ ኢየሉጣ” ይላል በታላቅ ጋን ውሃ አፍልተው ሕፃኑንና
እናቱን እንዲጨምሯቸው ሲያዝዝ ከሚፍለቀለቀው ውሃ ድምፅ የተነሣ ለጊዜው እናቱ ፍርሀት ሥጋዊ ቢያገኛትም ልጇም ወደ ጌታችን በጸለየላት ጊዜ ፍርሃቱ ርቆላት ከልጇ ጋር ስትገባ መልአከ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ውሃውን አቀዝቅዞ ሐምሌ ፲፱ አውጥቷቸዋል፡፡

❖ በመጨረሻም የሰማዕትነትን አክሊል የሚያገኝባት ጊዜ ሲደርስ ጌታችን
ተገልጾለት ስሙን ለሚጠራ ኹሉ ቃል ኪዳንን ከሰጠው በኋላ ሥጋኽን
በኤልያስ ሠረገላ ላይ አኖርልኻለኊ አለው፤ ይኽነን በሰማ ጊዜ በእጅጉ
ተደሰተ፤ ከዚኽም በኋላ ጥር ፲፭ በሌሊቱ እኲሌታ ከእናቱ ጋር አንገቱ ተቈረጠ
የሰማዕትነትን ክብር ተቀዳጅተዋል።

❖ ጥር ፲፮ ደግሞ የቅዱስ ቂርቆስ ማኅበር የኾኑ ዐሥራ አንድ ሺሕ አራት
በሰማዕትነት ዐልፈዋል፡፡
ሊቁ አርከ ሥሉስም የቅዱስ ቂርቆስን ተጋድሎ በማዘከር፡-

“እግዚአብሔር ሤመ ረድኤቶ ለንእስናከ ዐቃቤ ወስምዖ መጥበቤ ፍትወ ምግባር ቂርቆስ ወምዑዘ ኂሩት እምከርቤ ለዘተጽዕረ በምንዳቤ ወለዘቈስለ በጥብጣቤ ለአባልከ ሰላም እቤ”
(እግዚአብሔር ረድኤቱን ለታናሽነትኽ ጠባቂን አስቀመጠ፤ ብልኅ የሚያደርግ
ምስክርነቱንም፤ ምግባርኽ ያማረ በጎነትኽ ከከርቤ ይልቅ የሚሸት ቂርቆስ፤
በመከራ የተቸገረ በግርፊያ የቈሰለ ለኾነ ሰውነትኽ ሰላም እላለኊ) እያለ
ሕፃኑን ሰማዕት ያወድሳል፡፡

❖ #ሊቁ_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫም_በመጽሐፉ፦
“ሰላም ለቂርቆስ ወሬዛ በመንፈስ
በልደት ንዑስ፤ ንጹሕ ከመ ዕጣን
ወፍሡሕ ከመ ወይን”፡፡
(በልደተ ሥጋ ታናሽ በመንፈስ ጐልማሳ፤ እንደ ዕጣን ንጹሕ እንደ ወይንም
አስደሳች ለኾነ ለቂርቆስ ሰላምታ ይገባል)

❖“ሰላም ለሰማዕታት እለ ምስሌሁ ፭፼ ወ፬፻፤ ፬፼ ወ፪፻፲ወ፬”፡፡
(ከርሱ ጋር ያሉ ፭፼ ከ፬፻፤ ፬፼ከ፪፻፲፬ ሰማዕታት ሰላምታ ይገባቸዋል) በማለት
አመስግኗል፨

[የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት የቅዱስ ቂርቆስ የእናቱ
የኢየሉጣ፤ ስለአምላካቸው ስለ ክርስቶስ ፍቅር አንገታቸው በሰይፍ የተቆረጡት
የሰማዕታት በረከት ይደርብን፨
[ከመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ]
@razielethiopia
841 viewsMikiyas, 16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 20:59:24
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ሆይ ፡ በአርያም ፡ ባለው ፡ ጽሕራ ፡ መንግሥታችሁ ፡ እማፀናለሁ ፡ ስለዕዝራና ፡ ሄኖክም ፡ ሲባል ፡ ገነትን ፡ ስለጎበኛችሁ ፡ እኔን ፡ ባሪያችሁንም ፡ .....................በቸርነታችሁ ፡ ጎብኙኝ ፡
#ሰይፈ_ስላሴ_ቁጥር_፯
@razielethiopia
322 viewsMikiyas, 17:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 05:28:08 @razielethiopia
412 viewsMikiyas, 02:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 05:28:08
ለኢትዮጵያ 100 ዓመት በዝቋላ ባህር ውስጥ ተዘቅዝቀው ፀልየዋል ኢትዮጵያን ማርልኝ ካልማርክልኝ አልወጣም እያሉ። አሁንም ቢሆን የአቡነ ገብረ መፈስ ቅዱስ ፡ የጻድቃን ፡ የሰማዕታት ፡ የመነኮሳት የደናግላን.... ፀሎት ምልጃ ቃል ኪዳን ቅድስት ኢትዮጵያን ይጠብቅልን ከምንሰማው መጥፎ ነገር ፡ ከታዘዘው መቅሰፍት ይሰውረን።
#አሜን...
@razielethiopia
474 viewsMikiyas, 02:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 05:27:53 ሰላም የራዚኤል ዘኢትዮጵያ ቤተሰቦች
እንኳን አደረሳችሁ
377 viewsMikiyas, 02:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-05 14:14:25
ጥንተ ሰቅለት - መጋቢት 27 : 34 ዓ.ም
የዛሬ አንድ ሺሕ ዘጠኝ መቶ ሰባ ሦስት ዓመት በዕለተ አርብ ( 5534 ዓ.ም ) የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ስለ ዓለም ድህነት በስጋ የተሰቀለበት ቀን ነው።

እፎ ሰቀልኩ ካህናተ ይሁዳ ወሌዊ
መድኃኒአለም ናዝራዊ ናዝራዊ
#መልክዓ-መድኃኒአለም

@razielethiopia
1.4K viewsMikiyas, 11:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ