2022-01-02 11:04:45
ታህሳስ 24 -
#የታላቁ_አባት_አቡነ_ተክለሃይማኖት_ልደት
ታህሳስ 24 በዚህች ቀን ታላቁ ጻድቅ አቡነ ተክላሃይማኖት የተወለደበት ቀን
ነው፡፡ የትወልድ ቦታቸው ሽዋ ፀላልሽ አወራጃ በዘረሬ ነው። የአባታቸው ሰም
ፀጋ ዘአብ የእናታችው ስም እግዚሐርያ ይባላሉ።
መካን ነበሩ ልጅ አንዲሰጣቸው ወደ እግዚአብሔር ዘወትር ይፀልዩ ነበር መጋቢት 12 ቀን እንዲህ ሆነ መቶሎሜ የተባለ ጣኦት አምላኪ ንጉስ አገራቸውን ወረር መንደሩንም አጠፋ ፀጋ ዘአብ ወንዝ ዉስጥ ገበቶ አመለጠ እግዚሐርያ ግን ተማርካ ሄደች፡፡ በጣም መልከ መልካም ሰለ ነበረች መቶሎሜ ሊያገባት አሰበ ታላቅ ድግስም ደገሰ አገር ምድሩ ተሰብስቦ ሲዘፍን ሲጨፍር ሳለ ቅዱስ ሚካኤል ታላቅ መብርቅ ነጎድጓድ አሰማ ብዙዎች ሞቱ እግዚሐርያን በክንፎ ተሸክሞ ዞረሬ ከቤተክርስቲያን ዉስጥ አስቀመጣት ከባለቤቷ ፀጋዘአብ ጋር ተገናኙ ተቃቅፈዉ ተላቀሱ ከሁለት ቀን በኋላ መጋቢት 24 ቀን አቡነ ተክለሃይማኖት ተፀነሱ በዛሬዋ ቀን ታህሳስ 24/ 1190 ዓ/ም ተወለዱ ቀኑ
አርብ ነበር።
በተወለዱ በ3ኛ ቀናቸዉ እሁዱ በ3 ስዓት "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ አብ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ" ብለዉ ስላሴን አመሰገኑ፡፡
አባታችን የእንድ ዓመት ከመንፈቅ ህፃን እያሉ በድፍን ሽዋ ረሃብ ተከስቶ ነበር
በተለይም በዞርሬ እግዚሐርያ አዘነች አለቀሰች እርቧት ነው ጠምቷት ነው ቢሉ
የለም እርቧትስ ጠምቷትስ አይደለም የቅዱስ ሚካኤል ዝክሩ ታጎለብኝ ብላ አንጂ፡፡ ህፀኑ ተክልዬ ከእናቱ ጭን ወርዶ እየዳኸ ወደ ጓዳ ሲሄድ እናቱ አቀፈችዉ እርሱ ግን አለቀስ፡፡ ዶቄት የተቀመጠበትን እንቅብ እንድትስጠው በእጁ ጠቆማት ሊጫወትበት መስሏት ስጠችው በትንንሽ እጀቹ እንቅቡ ላይ አማተበ ዶቄቱ ሞልቱ ፈሰሰ ዳግመኛ የቅቤ የዘይት ማስቀመጫ ማድጋዎች ላይ በተመሳሰይ አማተበ ሞልቶ ፈሰሰ ቤቱ በበርከት ተትረፈርፈ የቅዱስ ሚካኤልን ዝክሩን አዘከርች አገሬውን ጠርታ መገበች ለተቸገሩትም አብዝታ ስጠች ይህ በረከት ሁለቱም እስኪሞቱ ድርስ አላለቀም ይላል ገድላቸው፡፡
አባታችን በ 99 ዓመት ከ10 ወረ ከ10 ቀን በዚህ ምድር ኖረው ነሐሴ 24 ቀን
አረፈዋል፡፡
ከቅዱሱ አባታችን ረድኤት በረከት ያሳትፈን፡፡
አሜን , , ,
@razielethiopia
@razielethiopia
1.6K viewsMikiyas, 08:04